Friday, September 30, 2016

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና አስተዳደር ሰራተኞች ስብሰባ በከፍተኛ የአመፅ ስሜት ተበተነ፡፡



Image result for gondar university



የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና አስተዳደር ሰራተኞች ስብሰባ በከፍተኛ የአመፅ ስሜት ተበተነ፡፡
ከዚህ በፊት እንደሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ሳይካሄድ የቆየዉ እና በዛሬዉ እለት በወያኔ ቡችላ በሆነዉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ስብሳቢ በሆነዉ በ ደ/ር ሽንታየሁ ወልደ ሚካኤል የተጀመረዉ እና በሁለት ታላላቅ አዳራሽ ከ2ሺህ በላይ የሚሆነዉ የዩኒቨርሲቲዉ ሰራተኛ የቀረበለትን ሻይ እና መስተንግዶ 95 በመቶ የሚሆነዉ የወንድሜ ደም እና ስጋ ይሁንብኝ ብሎ ምንም ያልቀመሰ ሲሆን በአንፃሩ እጅግ ጥቂት የሆኑ ባንዳዎች እና የህዋት ሆዳም አባላት ሲጠቀሙ ታይተዋል፡፡
በመጨረሻም ምንም ነገር ለእናንተ አፋችን አንከፍትም ብሎ ከቆየ በኋላ ሲጨንቃቸዉ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ምክትል ዲን የሆነዉ እና ያለብቃቱ በወያኔነቱ ስንት ፕሮፌሰሮች እና ዶክተሮች ባሉበት ዩኒቨርሲቲ ምክትል ዲን እንዲሆን የተደረገዉ ለመናገር ሲዉተፈተፍ ሁሉም በአንድ ላይ አንተ ባንዳ እረፍ ወንድሞቻችን እየተሰቃዩ ባለበት ወቅት አትናገርም በማለት በጩኸት ዝም እንዲል ያደረገዉ ሲሆን አንድ የመረረዉ መምህርም ወያኔን እስከመጨረሻዉ ተናግሮ ከተጨበጨበ በኋላ ሰብሳቢዎቹ ሲጨንቃቸዉ ለመበተን ተገደዋል፡፡

source mereja..com

No comments:

Post a Comment