Tuesday, January 31, 2017

ጉደኛውን ተራራ (Tullu Gudo) አየነው! BefeQadu Z Hailu


ዝዋይ ሐይቅ፣ በተለምዶ ዝዋይ በምትባለው ባቱ ከተማ ዳርቻ ላይ፣ በታላቁ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ፣ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 100 ማይሎች ርቆ የሚገኝ፣ 440 ስኵዌር ኪሎ ሜትር የሚሰፋ፣ ብዙም የማይወራለት፣ ብዙም ያልለማ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ፋይዳው የላቀ፣ ትልቅ ሐይቅ ነው። ሐይቁ 5 ደሴቶች

በኔ እምነት በማህበራዊ ሜድያው እጅግ ተሸንፈናል። Wondemagegnehu Addis


Wondemagegnehu Addis
ኢትዮጲያ እንድትበታተን እንቅልፍ አጥተው ከሚያድሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ምን እንጠብቅ እንደነበር አልገባኝም? አንዳች በጎ ነገር? ምን እንደምንጠብቅ ባለማወቃችን ሽንፈታችን በመደበኛነት እየታየ መጥቷል። እኛ ሳናውቃቸው እነሱ ግን ልባችንን በርብረው ስላወቁት አጠቃላይ አካሄዳችንን ተቆጣጥረውታል።
አንድ ሁለት አረረፍተ ነገር ወርወር ያደርጉና 1ወር ያንጫጩናል። እኛ ለነሱ መልስ ስንሰጥ በመንጋ ተከታዮቻቸው እንወረራለን። አንዳንዶቻችን አፀፋችንን ተመጣጣኝ ያደረግን እየመሰለን እነሱ በሄዱበት መንገድ ምላሽ ስንሰጥ ወጥመዳቸው ውስጥ እንገባላቸዋለን። እነሱም ሲጀመርም ይሄንን ትርፍ አስልተው ነው የሚያደርጉትን የሚያደርጉት። እሰጥ አገባው በርካታ ቁስሎችን በማህበረሰቦቻችን መሀል ፈጥሮ ያልፋል።
ትንሽ አረፍ ስንል ሌላው ደሞ በሆነች ሀረግ ጠቅ ያደርገንና ዞር ይላል። እኛም ወደተለመደው ተግባራችን እንመለሳለን። ለኛ የቤት ስራ ሰጥቶን እሱ ስራውን ይሰራል።
እስኪ እናስተውል ከንዲህ አይነት ድግግሞሽ እስካሁን ያተረፍነው ነገር ምንድነው? ድንገት ብቅ እያሉ እንደፈለጋቸው ሲያንጋጉን፣ ወዲያና ወዲህ ሲያመላልሱን እንዴት መንቃት ተሳነን? ሁሌ መከላከል አይበቃንም ወይ?ከነሱ ምንም አይነት ሀላፊነት የተሞላው ድርጊት መጠበቅ የለብንም። ከሚነሳው አቧራ እነሱ የሚያጋብሱት ፋይዳ እንጂ የሚያጎሉት ምንም የለም። እኛ ግን ብዙ እናጎላለን። ጠላትን ማበሳጨትና ማሳሳት የሚለውን ስሌት በሚገባ እየተገበሩት ነው። አሁን ለኛ የሚጠቅመን ትግሉ ላይ ማተኮር ብቻ ነው። እዚያ ላይ ጊዜያችንን እና አቅማችንን ልናውል ይገባል። ወቅታዊ ከሆኑት እንኩዋን የቅማንት ፣ የቴድሮው አድሀኖም አረ መአት ጉዳዮች ጉዳዮች አሉን።

በኢትዮጲያ አንድነት እናምናለን የምንል ወገኖች መጀመሪያ በመሀከላችን ያለውን ቀዳዳ እንድፈን። ያልሰራናቸው በርካታ የቤት ስራዎች አሉን። እንደ ኢትዮጲያዊ ጠንክረን ስንወጣና በልዩነቶቻችን ተከባብረን መታየት ስንችል ትርጉም ያለው ተፅእኖ ልንፈጥር እንችላለን። በቀላሉ የማንደፈርና የማንገሰስ እንሆናለን። እንከበራለን እንታፈራለንም። ያን ጊዜ የምንለው ይሰማል። አጀንዳ መስጠት የኛ ተራ ይሆናል።
ስለዚህ ትኩረት የምንሰጣቸውን ጉዳዮች እንለይ። አላስፈላጊ በሆነ ጉዳይ ተጠምደን አስፈላጊውን ጉዳይ እያሳደርን ለአፍራሾች ኢላማ አንመቻች።


Monday, January 30, 2017

ዶ/ር መረራ ጉዲና ለሦስተኛ ጊዜ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተጠየቀባቸው – ታምሩ ጽጌ

ዶ/ር መረራ ጉዲና
በሽብር ተግባር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ በሚገኙት ዶ/ር መረራ ጉዲና ላይ፣ ፖሊስ ለሦስተኛ ጊዜ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት፡፡
የመድረክ የውጭ ግንኙነት ኃላፊና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ (ኦፌኮ) ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በተጠረጠሩበት የሽብር ተግባር ላይ፣ ብዙ ምርመራዎችን ማድረጉን ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ፖሊስ አስረድቷል፡፡ ነገር ግን ቀሪ ማስረጃዎችን እያሰባሰበ መሆኑን ገልጾ፣ ተጨማሪ 28 ቀናት እንዲቀፈድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡
የዶ/ር መረራ ጠበቆች ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ በመቃወም፣ ደንበኛቸው ሕገ መንግሥታዊ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የሁለቱንም ወገኖች ክርክር ካዳመጠ በኋላ፣ የተጠየቀውን የዋስትና መብት በማለፍ ፖሊስ የጠየቀውን የ28 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ፈቅዷል፡፡ ለየካቲት 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 መሠረት ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ለመጠየቅ አንድ ዕድል ይቀረዋል፡፡

Tuesday, January 24, 2017

ግንቦት ሰባት ፥ ኢሳት እና ትግሉ – (ኄኖክ የሺጥላ)



ግንቦት ሰባት ፥ ኢሳት እና ትግሉ (ኄኖክ የሺጥላ)
ከግንቦት ሰባት ጋር የሚያስታርቅ ነገር እስከ አሁን አልገጠመኝም! ከግንቦት ሰባት ጋር ያጋጨኝ ነገር ፥ ከወያኔ ጋር ያጋጨኝ አይነት አይደለም! ግንቦት ሰባት የከሸፈ ፥ አቅም የሌለው ፥ አቅመ ቢስነቱን እያወቀ በደረቁ የኢትዮጵያ ህዝብን ለማጭበርበር ደፋ ቀና የሚል ድርጅት ስለመሆኑ ከማንም በላይ ደጋፊዎቹ እና መሪዎቹ በደንብ ያውቃሉ። ግንቦት ሰባት በአባላቱ ላይ ሳይቀር ፕሮፖጋንዳ የሚሰራ ድርጅት ነው። አሁንም በመላው አለም ላይ ሊያደርጉት ያሰቡት ጉዞ ፥ ከጭንቀት የመነጨ ፥ አባላትን ለማረጋጋት ታስቦ የተዶለተ ተራ የፖለቲካ ቁማር ስለመሆኑ ፥ ከስብሰባው ቀድሜ ፥ በስብሰባው ላይ ፥ ይህ ነው የሚባል የረባ ነገር እንደማያስተላልፉ መናገር እችላለሁ!
ችግሩ የግንቦት ሰባት መክሸፍ አይደለም ። ችግሩ ግንቦት ሰባት በኤች አይቪ እንደተያዘ ክፉ አባወራ ማሰቡ ነው እንጂ ! በዚህም ድምዳሜው ፥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የኢሳትን ተአማኒነት ፥ እና የኢሳትን የህዝብነት ለድርጅቱ ተክለ ሰውነት ሲባል እንዲረግፍ እያደረገ ያለ ድርጅት ነው ! እኔን ከያዘኝ ኢሳትም ይማቅ አይነት ነገር! ይህ ግንቦት ሰባትን ከወያኔ ጋር የሚያመሳስለው አብይ ጉዳይ ይመስለኛል። ግንቦት ሰባት ደጋፊዎቹን ያለ ምክንያት የመደገፍ ጥቅምን አጥምቆዋቸዋል ። ሃሳብን መሞገት ሲያቅታቸው ፥ ባለቻቸው ሚጢጢ ትልቅነት ግዝብዝ ሲሆኑ ታስተውላለህ ።
ለምሳሌ
የዛሬ ሁለት ሳምንት እዚህ ሳን ሆዜ የሚኖር የግንቦት ሰባት በከተማው ሁለተኛ ሰው የሚያስተዳድረው ሆቴል አለው። ይህ ሰው ጥሩ ወዳጄ የነበረ ነው። የግንቦት ሰባት አባል በነበርኩበት ወቅት ከዚሁ ሰው ጋር ነው ሎስ አንጀለስ ድረስ ተጉዘን የኤፍሬም ማዴቦን « አማራ ምን አባቱ !» አይነት ንግግር የሰማነው። ያም ሆኖ ከግንቦት ሰባት ራሴን ካገለልሁ በኋላ ከዚህ ሰው ጋር ያለኝን ሰዋዊ ወዳጅነት ያለ ምክንያት ወይም የግንቦት ሰባት አባል ስለሆነ ማቋረጥ አለብኝ ብዬ አላስብም ነበር ። ስለዚህም የዛሬ ሁለት ሳምንት ከወዳጆቼ ጋር በሆቴሉ ሄደን ምሳ ለመብላት ( በቁጥር ስምንት ስለሆነን ) በቅድሚያ ወንበር ለመያዝ ደወልሁለት ። ምንም ችግር የለም አለኝ። ከሰዓታት በኋላ ደውሎ « ድርጅቴን ግንቦት ሰባትን ስለጎዳህብኝ አንተ ምግብ ቤቴ መጥተህ እንድትመገብ አልፈልግም !» የሚል መልስ ሰጠኝ ። በመጀመሪያ ሰውን በፖለቲካ አቋሙ አላስተናግድም ማለት የሚያስከስሰው ነገር እንደሆነ እንኳ በቅጡ የሚያውቅም ሰው አለመሆኑ ገረመኝ ፥ በሁለተኛ ደረጃ እዚህ ድረስ እስኪበሰብሱ ድርጅት ማፍቀራቸው አዘንኩላቸው ። ይህም ከወያኔ ማንነት ጋር ፍፁም አንድ ነው !
ዛሬ ድርጅቴን ስለተናገርክብኝ እቤቴ አትበላም ያለኝ ሰው ነገ ስልጣን ቢይዝ ፥ ሃገር መግባት አትችልም ስላለማለቱ ዋስትናው ምንድን ነው ! እንግዲህ ይህ ሰው ራሱ በሳን ሆዜ የኢሳት የገቢ አሰባሳቢ አካል ነው ። አሁን በዚህ ሰው መነፅር ኢሳትን እንድናይ የሚያደርጉን ግንቦት ሰባቶች ናቸው ! የኢሳትን ህልውና የሚፈታተን ርካሽ ነገር የሚፈፅሙትም ፥ ኢሳት ያገኘው ህዝባዊ ተቀባይነት በመጠቀም ፥ ከነሱ ጋር በ አልቦነታቸው ምክንያት የሚጋጨውን ( ወይም የሚጠይቀውን ) ሰው ሁሉ ግጭቱን ወደ ኢሳት እያዞሩ ፥ በቀጥታ ፀቡን ከኢሳት ጋር እንድናደርግ የሚያደርጉን !
ይህ በዚህ የሚቀጥል ከሆነ ወደፊት ልክ ዛሬ የግንቦት ሰባት ህልውና አደጋ ላይ እንደወደቀው ( ከስሩ እንደተሽመደመደ ) ሁሉ ፥ የኢሳትም ህልውና አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም ! ትንቢት አይደለም ግን I can see it!
በቀጣይ ግንቦት ሰባት እንደ ስትራቴጂ ነድፎ መንቀሳቀስ የጀመረው ነገር ፥ ሆድ አደር እና ምልምል የአማራ ልጆችን በማሳመን ፥ የአማራ ማህበር እየፈጠሩ ፥ አማራን እንዲሰበስቡ የማድረግ ስራ ነው ። ይህ ለግንቦት ሰባት ለጊዜው የሚፈልገውን የሰው እና የቁስ ሃይል ያመጣለት ይሆናል ፥ ኋላ ላይ ግን ማቆም እና መቋቋም የማይችለው ጉልበት ተፈጥሮ እነዚህ በስውር የተቋቋሙ የአማራ ሃይሎች ተገንጥለው እንደሚወጡ ለመገመት ብዙ ማወቅ አይጠይቅም ! ወያኔ ትግሬ በተለያየ ጥቅማ ጥቅም ብአዴን የሚባል ቡድን መስርቶ አማራውን ለመቆጣጠር የሄደበት መንገድ ፥ ዛሬ ለወያኔ ከፍተኛ ስጋት እና የውስጥ አርበኛ በመሆን የቁም ስቅሉን የሚያሳዩት እነማን እንደሆኑ ፥ እነማን መረጃ እንደሚሰዱልን የታወቀ ነገር ነው !
ባጭሩ ከግንቦት ሰባት ጋር የሚያስታርቁኝ ( እኔን እና የአማራ ወጣቶችን ማለቴ ነው ) የሚከተሉት ይሆናሉ ብዬ እገምታለሁ
1ኛ ግንቦት ሰባት አቅም የሌለው አየር ወለድ ድርጅት መሆኑን አምኖ የትግል ስልት ለውጥ ማድረግ
2ኛ አማራን ለስልጣን መወጣጫነት ለመጠቀም ከማሰብ እና አማራን አዚህ ደረጃ ከመናቅ መውጣት
3ኛ ስለ አንድነት እየሰበከ እራሱ በብሄር የተደረጃ ድርጅት ነውና ፥ ይህንን መዋቅሩን ቀይሮ ሁሉ አቀፍ ህብረ ብሄራዊ ማዕከላዊ መዋቅር ያለው ድርጅት ለመሆን መንገድ መክፈት
4ኛ ላምባልዋለበት ኩበት መልቀሙን ማቆም! የአማራ ትግልን የኔ ነው ብሎ መታበዩን መግታት
5ኛ ከምንም በላይ በህዝብ ገንዘብ የቆመውን ኢሳትን የህዝብ እንዲሆን መፍቀድ! ለድርጅት ተክለ ሰውነት ሲባል የኢሳትን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል ተራ ጉንጭ አልፋ ፕሮፖጋናዳ በኢሳት እንዲሰራ ከማድረግ መቆጠብ
እና ሌሎች !
ኄኖክ የሺጥላ

Sunday, January 22, 2017

ብርቱ ሚስጥር በጋምቤላ ፍጅት ሲጋለጥ! የጋምቤላ ታጋች ህፃናት ለፖለቲካ ፎጆታ እየሆኑ ነው! ሙሉነህ ዮሃንስ



ብርቱ ሚስጥር በጋምቤላ ፍጅት ሲጋለጥ!
የጋምቤላ ታጋች ህፃናት ለፖለቲካ ፎጆታ እየሆኑ ነው!
ህፃናቶቻቸውን እና እንስሶችን እንደፈለጉ የደቡብ ሱዳን የሙርሌ ጎሳ አባላት የሚነጥቁባቸው ዞን ውስጥ ከፍተኛ ሹመኛ የሆነ ሰው ነው ያደረሰን።
ሚስጥሩን በደረስኩበት መረጃ መሠረት ገና ከዚህ በላይ የወረዳው ሰው ሁሉ ሊወሰድ ይችላል ይላል፡፡ ምክንያቶቹን እንዲህ ዘርዝሮ ልኮታል፡-
1. ለም የእርሻ መሬት ከእኛ እስከ አጎራባች አለ ይህን በሚያርሱ የወያኔ ኢንቨስተሮች ለበርካታ አመታት ከህይወት እስከ ንብረት መስዋትነት አስከፍሏቸዋል።
2. #ወያኔን ሊያሰጋ የሚችል ሁሉ እስካሁን በሙሉ ሃይል በየቦታው ባይንቀሳቀስም በወታደራዊ ጥናታቸው መሰረት ያሰጋልና ስለሚሉ እስከዛው እኛም የስጋት ምንጭ ተደርገን ስለምንቆጠርና ለጥቃትም በቀላሉ ተጋላጭ ስለሆንን ዘራችን የሚጠፋበት አደጋ ውስጥ ገብተናል።
3. ከደቡብ ሱዳን ውሎገብ የፈለግነውን የጦር መሳርያና የእለት ፍጆታ ሸቀጥ ያለስጋት እናስገባ ነበር። ያንንም ለማስቀረትና እኛል ለመፍጀት ነው።
4. የወያኔ ሴረኛ ቡድን ከደቡብ ሱዳን ጋር በጥበብ በመመሳጠር በግጦሽ በማመሳሰል ምንም የማያውቀውን ህዝቡን እያስገደለ ነው።
5. ለወረዳው ቅርብ በሆነ ሁኔታ የሠፈረው በትግራይ ኃላፊዎች ብቻ እንደፈለጉ የሚያዙት ልዮ ኃይል፣ ፌደራል ፖሊስ፣ ሽምቆች እንዲሁም መከላከያም አለ። የመጀመርያዋ ጥይት ሳትጮህ ለመከላከያ አዛዡ ተደውሎ ነበር እንደርሳለን ብለው አውቀው የውሃ ሽታ ሆነው ቀሩ፡፡
6. ቢያንስ በቅርብ ርቀት አስተማማኝ የአየር ኃይል አለ። ታድያ በትንሽ ደቂቃ ብቻ እስከ ወረዳው መድረስ ይችል ነበር ግን አልሆነም። ለምን አትበሉ። ዘር ፍጅቱ በወያኔ የተቀነባበረ ነው።
7. መሬታችንን ያለግብር የሚያርሱት የትግራይ ዜጎች ቢሆኑ ኖሮ የተጠቁት 57ቱ ወገኖቻችን ሳይመለሱ ተጨማሪ 16 ህፃናት መወሰዳቸው ሌሎችም ሊሞቱ ቀርቶ ደቡብ ሱዳንን በጨፈለቀ ነበረ፡፡
8. #በመጨረሻም የሱማሊያን አልሻባብ ተሻግሮ ለመግጠም ሰራዊት የሚልክ እንዲሁም አልፎ ላይቤርያና ሱዳን ሄዶ ሰላም አስከብራለሁ እያለ ኃይል የሚገብር የወንጀለኞች ጥርቅም ለራሳችን ዜጎች መሆን ሳይችል ይብስ ብሎ በአስቸኳይ አዋጅ ስም ሰላማዊ ህዝብ ሲያሸብርና ሲጨፈጭፍ ማየት እጅግ ያማል።
9. አሁን እኛም በስለናል። በተለይ የእኛን ወጣቶች በገፍ ለውትድርና የማያውቁትን ገጠራማው አካባቢ የሚመለምለው እንዳይሳካ ተግተን እየሰራን ነው። ለነፃነታችን መከበር ደቡብ ሱዳንን ሣይሆን ህዋህትን/ወያኔን ከአጋሮች ጋር ተደራጅተን እንታገላለን፡፡
ድል ለጭቁኑ ህዝብ! በማለት ይህን ብርቱ ሚስጥር ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለአለም እንዲታወቅ በአስቸኳይ ይድረስልን ብሏል።
ማሳሰቢያ፡-
ይህን ወደእንግሊዝኛና ወደተለያዪ ቋንቋወች በመተርጎም በቶሎ ስራ ልትጋሩ የምትችሉ በፍጥነት በውስጥ መስመር አግኙኝና የህዝባችንን ብሶት እናስተጋባ ለጋምቤላ ወገኖቻችን እንድረስላቸው።
አሁንስ ያማል!
ሙሉነህ ዮሃንስ

Wednesday, January 18, 2017

በስናይፐር የታጄበ ጥምቀት በጎንደር ቆንጅት ስጦታው



በስናይፐር የታጄበ ጥምቀት በጎንደር
( የጎህ ጋዜጠኛ ዞብል)
ከጎንደር ታቦቱን ከመቅደሱ ገብተው መሼከም እስኪቀራቼው ድረስ የመንግስት ወታደሮች ካህናቱን ቶሎ በሉ፣ ቶሎ በሉ እያሉ ያጣድፏቼው ነበር።
ታቦት በራሳቼው ላይ የተሼከሙ አባቶች ሁለት እጆቻቼው ታቦቱን ቢደግፉም እንባዎቻቼው በጎንደር
አስፋልት ላይ ጠብ፣ ጠብ፣ እያሉ ሲፈሱ ከበርካታ ካህናት አይኖቼ ቀረብ ብዮ አስተውያለሁ፣ መስቀል ኃይልነ ብላ የምታምን ቤተክርስቲያን ዛሬ ስናይፐር ኃይልነ የሚል መንግስት በስናይፐር የጎንደር ታቦቶች እንዲታጄቡ አደረገ። ድሮ በኦሞ መንገዱ ታጥቦ ምንጣፍ እየተነጠፈ እላዩ ላይ የሰላም ምልክት ቄጠማ የሚጎዘጉዙት ወጣቶች ዛሬ በብአሉ ስፍራ የሉም። በምትካቼው ካህናተ እግዚአብሔርን በግልምጫ እና
በስድብ የሚያዋርድ ሰራዊት ከህዝቡ በላይ ተገኝቷል። ታቦት ተሼካሚውን ካህን ተጎንብሶ አንድ ባለ ስናይፐር
“ቶሎ ቶሎ ሒድ ምን ይገትርሐል ” በማለት ሲናገር የተመለከቱ አንዲት መነኩሲት ምነው የአባቶቻችን አምላክ እንዲህ ፈጽሞ ረሰን ፣ አርባ አራቱ ታቦቶቻችን ከመዋረዳቸዉ በፊት ምን አለበት እኛን በሞት ቢጠራን በማለት ጮክ ብለው በመናገር ምርር ብለው ሲያለቅሱ ብዙ እናቶች በዋይታ አጄበዋቼው ነበር። “የምን ለቅሶ ነው ዝም በይ” ተብለው እኒህ እናት በታጣቂ ሲንገላቱ ህዝቡ መሀል ገብቶ ከባለ መሳሪያው አስለቅቋቼዋል።
ጎንደር ከወትሮው በተለየ መልኩ የጥምቀት ባዕል ሳይሆን ዘመድ አልባ አስከሬን የሚሼኝ በሚመስል መልኩ ፀጥ እረጭ ብላ በዓለ ጥምቀቱን በግዳጁ ስታከብር ፣ ታቦታቱን ወደ ማደሪያው በፌደራል፣ በመከላከያና በወያኔ ካድሬ ተከቦ በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከተማዋ ነዎሪዋቾን በተፈጥሮ አደጋ የተነጠቀች እስኪመስል በዓለ ጥምቀቱ የሰው ድርቅ መትቶት በደበዘዘ መልኩ አልፉል። ባከታሪኩ ጄግናው የጎንደር ህዝብም የተማማለበትን ጥምቀተን እንደወትሮው በድምቀት አናከብርም ያለውን ቃሉን በሚገባ አክብሯል!!!!

Sunday, January 15, 2017

በጎንደር ከተማ አመፅና ሁከት አስነስታለች የተባለች ግለሰብ የሽብር ወንጀል ክስ ተመሠረተባት source EthiopianReporter.com



በአማራ ክልል በተለይ በሰሜን ጎንደር ከተማ በተለያዩ የዞን ከተሞችና በአዲስ አበባ ጭምር አመፅና ሁከት በማስነሳት፣ የአመፅ ጥቃቶች እንዲፈጸሙ በማስተባበር ከፍተኛ የሆነ የግልና የመንግሥት ንብረት ላይ ውድመት አድርሳለች የተባለች አንድ ግለሰብ ከሌሎች አምስት ግለሰቦች ጋር የሽብር ወንጀል ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
በቅጽል ስሟ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም አላና ፖታሽን በታክስ ማጭበርበር source ethiopian reporter




ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም አላና ፖታሽን በታክስ ማጭበርበር ወነጀሉ

-  አላና ፖታሽ ግን በሰላማዊ መንገድ ችግሩን እንፍታ ብሏል
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አላና ፖታሽ የተሰኘውን በአፋር ክልል በፖታሽ ማዕድን ፍለጋ ተሰማርቶ የነበረውን የካናዳ ኩባንያ በታክስ ማጭበርበር ወነጀሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጥር 1 ቀን 2009 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤታቸው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ አላና ፖታሽ የኢትዮጵያ መንግሥትንና አይሲኤል የተባለውን የእስራኤል ኩባንያ ማጭበርበሩን ተናግረዋል፡፡ የአገሪቱ የማዕድን ዘርፍ ስላለበት ሁኔታና እንደ አላናና አይሲኤል ያሉ የማዕድን ኩባንያዎች ሥራቸውን አቋርጠው መውጣት በዘርፉ ላይ ስለሚኖረው ተፅዕኖ የተጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የአላና ጉዳይ ከታክስ ስወራ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡
‹‹የአላና ፖታሽ ጉዳይ ግብር ከማጭበርበር ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ኩባንያው ወደ ሁለት ቢሊዮን ብር መክፈል ያለበት የግብር ዕዳ አለበት፡፡ ያንን ግብር መክፈል አለበት፡፡ መንግሥት ይኼን በሆነው መንገድ በሕግም ፈልጎ ያስከፍላል፤›› ብለዋል፡፡
በቶሮንቶ ስቶክ ገበያ ተመዝግቦ ሲንቀሳቀስ የቆየው አላና ፖታሽ፣ ‹‹አላና ፖታሽ አፋር›› የሚባል እህት ኩባንያ በማቋቋምም በአፋር ክልል ዳሎል አካባቢ የፖታሽ ማዕድን ፍለጋ ሥራ ለስድስት ዓመታት ያህል ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ አላና ፖታሽ አፋር ለማዕድን ፍለጋ ሥራው 90 ሚሊዮን ዶላር ማውጣቱን፣ 3.2 ቢሊዮን ቶን የፖታሽ ክምችት ማግኘቱን በወቅቱ አስታውቋል፡፡
የፖታሽ ክምችቱን ለማልማት 750 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው፣ የፖታሽ ማምረቻ ፋብሪካውን ገንብቶ በዓመት አንድ ሚሊዮን ቶን በማምረት ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከ430 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ለማስገኘት የሚያስችል ዕቅድ ለመንግሥት አቅርቦ ይሁንታን አግኝቶ ነበር፡፡ እ.ኤ.አ. በ2013 የማዕድን ሚኒስቴር ለአላና ፖታሽ አፋር የከፍተኛ ማዕድን ማምረቻ ፈቃድ ሰጥቶታል፡፡
ይሁን እንጂ በዓለም ገበያ የማዕድናት ዋጋ በመውደቁና አላና ፖታሽ የሚፈለገውን ካፒታል ማሟላት ባለመቻሉ፣ እስራኤል ኬሚካልስ ሊሚትድ (አይሲኤል) ለተባለው ታዋቂ የማዳበሪያ አምራች የአክሲዮን ድርሻውን ሸጧል፡፡ አይሲኤል ቀደም ሲል የአላና ፖታሽ በቶሮንቶ ስቶክ ገበያ 16 በመቶ የአክሲዮን ድርሻ ገዝቶ ነበር፡፡ እ.ኤ.አ. በ2015 የተቀረውን 84 በመቶ በ140 ሚሊዮን ዶላር ገዝቶታል፡፡
በወቅቱ የማዕድን፣ ፔትሮሊየምና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር ኃላፊዎች ስለሽያጩ ቀደም ብሎ አልተገለጸልንም ሲሉ ቅሬታቸውን ያሰሙ ቢሆንም፣ የአላና ፖታሽ ኃላፊዎች በበኩላቸው ለሚኒስቴሩ አሳውቀናል ሲሉ አስተባብለዋል፡፡
አላና ፖታሽን ከገዛ በኋላ አይሲኤል የአላና የማዕድን ማምረቻ ፈቃድ እንዲዛወርለት ለማዕድን ሚኒስቴር አመልክቷል፡፡ ሚኒስቴሩ ማመልከቻውን በመገምገም ላይ ሳለ የፖታሽ ፕሮጀክቱ ሥራ እንዳይቋረጥ አይሲኤል ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎች አስገብቶ ሥራውን እንዲቀጥል መፍቀዱን የቀድሞው ሚኒስትር አቶ ቶለሳ ሻጊ ለሪፖርተር መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ የማዕድን ሚኒስቴር ኃላፊዎች አይሲኤል አስፈላጊዎቹን ሰነዶች አሟልቶ እንዲያቀርብ ጠይቀው ጉዳዩን በማየት ላይ ሳሉ፣ አይሲኤል (አላና ፖታሽ አፋር) ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ጋር በታክስ ጉዳይ ውዝግብ ውስጥ ገብቷል፡፡ ባለሥልጣኑ በአላና ፖታሽ ሊከፈል የሚገባ የዊዝሆልዲንግና የቫት ክፍያ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ በአላናና በአይሲኤል መካከል በተፈጸመው ሽያጭ ውል መንግሥት ሊያገኝ የሚገባውን የካፒታል ዕድገት ግብር በአጠቃላይ 55 ሚሊዮን ዶላር ግብር እንዲከፈል ጠይቋል፡፡
የአይሲኤል ኃላፊዎች በበኩላቸው በአላና ሊከፈል የሚገባ 15 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን የዊዝሆልዲንግና የቫት ግብር ለመክፈል ተስማምተው የነበረ ቢሆንም፣ ባለሥልጣኑ ይህን ሊቀበል አልቻለም፡፡
በግብር ጥያቄው የተደናገጡት የአይሲኤል ኃላፊዎች ሥራቸውን አቁመው ከአገር ወጥተዋል፡፡ በጥቅምት 2009 ዓ.ም. የአይሲኤል ዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት ሊያሠራን ስላልቻለ በኢትዮጵያ የጀመርነውን ኢንቨስትመንት ለማቋረጥ ተገደናል፤›› ሲል መግለጫ አውጥቷል፡፡
‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊውን መሠረተ ልማትና የሕግ ማዕቀፍ ሊያቀርብልን ባለመቻሉ፣ የታክስ ባለሥልጣኑ አላና ፖታሽ አፋር ላይ ሕገወጥ የታክስ ጥያቄ በማቅረቡ የኩባንያው ሥራ እንዲቋረጥ ወስነናል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ድርጊት ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ከለላ ውሎችን የጣሰ ነው፤›› ብሏል ቦርዱ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የሰጡት ምላሽ ከአይሲኤል መግለጫ ጋር የማይጣጣም ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ መንግሥት አላና ፖታሽን እንጂ አይሲኤልን እንደማያውቀው ነው የተናገሩት፡፡
‹‹አይሲኤልን በተመለከተ አይሲኤል ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር የተደራደረው ነገር የለም፡፡ አላና ፖታሽ ከሚባል አንድ የፖታሽ ኩባንያ ጋር የኢትዮጵያ መንግሥትን ሳያሳውቁ ከበስተጀርባ ተደራድረው ነው የመጡት፡፡ እኛ አሁንም የምናውቀው አላና ፖታሽን ነው፡፡ በኢትዮጵያ ተመዝግቦ ሲንቀሳቀስ የነበረው እሱ ነው፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አይሲኤል ከበስተጀርባ ተደራድሮ ከበስተጀርባ እንደሄደ ተናግረዋል፡፡
‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ላይ ተጠያቂ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም እኛ የምናውቀው አላና ፖታሽን ነው፡፡ እኛ አገር ውስጥ ተመዝግቦ የሚሠራው አላና ፖታሽ ነው፡፡ ከቀጠለ ይቀጥላል፣ ካልቀጠለ ለሌላ ኩባንያ እንሰጣለን፡፡ ብዙ ፈላጊዎች ስላሉ ብዙ የሚያሳስበን ጉዳይ አይደለም፤›› ብለዋል፡፡ አላና ፖታሽ አይሲኤልን እንዳጭበረበረ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት፡፡ ‹‹አይሲኤል በራሱ በአላና ፖታሽ የተጭበረበረ መሆኑን አውቆ ነው የሸሸው፡፡ ምክንያቱም እኛ ግብር ይከፈል ስንል እነሱ ከጀርባ የተፈራረሙት ይህን ሁሉ ስለማያካትት፣ ከዚህ ተቋም ጋር መቀጠል አንችልም ብለው ነው የሄዱት፡፡ አሁንም ቢሆን መጥተው ግብሩ ከተከፈለ በኋላ ስማቸውን ለማዛወር ከፈለጉ የኢትዮጵያ መንግሥት ዝግጁ ነው፤›› ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይኼን ቢሉም የቀድሞ አላና ፖታሽ ማኔጅመንትና ቦርድ አባላትና የአይሲኤል ኃላፊዎች በድብቅ የተደረገ ስምምነት እንደሌለ ይናገራሉ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተያየት የቀድሞ የአላና ፖታሽና የአይሲኤል ኃላፊዎችን አስደንግጧል፡፡
ከአላና ፖታሽ አፋር መሥራቾች አንዱ የሆኑት አቶ ነጂብ አባቢያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሰዎች ሳያሳስቷቸው እንዳልቀሩ ነው የተናገሩት፡፡ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝን እናከብራቸዋለን፡፡ ኢትዮጵያን የምታህል ትልቅና፣ ከአፍሪካ በፍጥነት በማደግ ላይ የምትገኝ አገር መሪ ናቸው፡፡ አላና ፖታሽን በተመለከተ ግን የቀረበላቸው መረጃ የተሳሳተ ነው፡፡ ዞሮ ዞሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚናገሩት በበታቾቻቸው በቀረበላቸው መረጃ ነው፡፡ እኔ የቀረበላቸው መረጃ የተሳሳተ ነው ባይ ነኝ፡፡ ይህን ለማረጋገጥ ደግሞ በጣም ቀላል ነው፡፡ አላና ፖታሽንና አይሲኤልን በተመለከተ የተፈጸመው ውል የተመዘገበና በእኛና በመንግሥት እጅ የሚገኝ ለመሆኑ ሰነዶቹን በእርጋታ በመመርመር ማረጋገጥ ይቻላል፤›› ብለዋል አቶ ነጂብ፡፡
አላና ፖታሽ ለአይሲኤል መሸጡ በገሃድ የተካሄደ እንደሆነ፣ በወቅቱ የአላናና የአይሲኤል ከፍተኛ ኃላፊዎች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ከፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፣ ከቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ ከቀድሞ የማዕድን ሚኒስትር አቶ ቶሎሳ ሻጊ ጋር በመገናኘት አይሲኤል በኢትዮጵያ ለመሥራት ስላሰበው ሰፊ ኢንቨስትመንት ማብራሪያ መስጠታቸውን፣ በወቅቱም መሪዎቹ ዕቅዱን በበጎ ሁኔታ መቀበላቸውንና ማበረታታታቸውን ተናግረዋል፡፡
‹‹በድብቅ የተደረገ ድርድር የተባለው እኔ አልገባኝም፡፡ ሁለቱም ኩባንያዎች በስቶክ ኤክስቼንጅ ለሕዝብ ለሽያጭ የቀረቡ በመሆናቸው ማንኛውንም መረጃ መደበቅ አይችሉም፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ባለአክሲዮኖች ስላላቸው ለእነሱ እያንዳንዱን ነገር ማሳወቅ በሕግ ይገደዳሉ፡፡ ግዢውም ቢሆን በዓለም አቀፍና በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ሪፖርተርን ጨምሮ ዘግበውታል፡፡ ምኑ ነው ድብቅ?›› ብለዋል፡፡
አይሲኤል አላና ፖታሽን ከመግዛቱ ቀደም ብሎ ጀምሮ ከግብርና ሚኒስቴርና ከግብርና ትራንስፎርሜሽን ኤጀንሲ ጋር በቅርበት ይሠራ እንደነበር የአይሲኤል ኃላፊዎች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ የአይሲኤል ዋና ባለድርሻና የእስራኤል ቁጥር አንድ ቱጃር የሆኑት ኢዳን ኦፋርና በወቅቱ የአይሲኤል ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት ሚስተር ስቴፋን ቦርጋስ፣ ኩባንያቸው በኢትዮጵያ በማዳበሪያ አጠቃቀም ዙሪያ ለሚካሄዱ ፕሮግራሞች የገንዘብና የባለሙያ ድጋፍ በማድረግ ላይ መሆኑን ቃለ መጠይቁ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ 600,000 ዶላር መለገሳቸውን ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
የታክስ ማጭበርበር ተፈጽሟል ስለተባለው አቶ ነጂብ አይሲኤል አላና ፖታሽን ከመግዛቱ በፊት ለአንድ ዓመት ያህል አላና ፖታሽ ስላለው ንብረትና ዕዳ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው የኢትዮጵያና የውጭ ባለሙያዎች ቀጥሮ ሰፊ የምርመራ ሥራ መሥራቱን፣ ባካሄደውም ጥናት አላና ያለበትን ዕዳ አብጠርጥሮ ማወቁንና ዕዳውንም ለመክፈል መስማማቱን ተናግረዋል፡፡
‹‹እንኳን በዓለም ገበያ ላይ የተመዘገበ ኩባንያ ስትገዛ አይደለም አዲስ አበባ ውስጥ አንድ አነስተኛ ቤት ስትገዛ የባንክ ዕዳ አለበት ወይ? የአገር ውስጥ ገቢ አለበት ወይ? ክርክር አለበት ወይ? መንገድ ይወጣበታል ወይ? ብለህ ትጠይቃለህ፡፡ እንዴት ነው አይሲኤልን የሚያህል ግዙፍ ኩባንያ የሚገዛውን ኩባንያ ዕዳ ሳያጣራ ገንዘብ የሚከፍለው?›› ሲሉ በሁኔታው ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡
ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደብዳቤ እንደሚጽፉ፣ ከተፈቀደላቸውም በአካል ቀርበው ለማስረዳት ፈቃደኛ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ‹‹ያለውን አለመግባባት በሰላማዊ መንገድ እንደምንፈታው አምናለሁ፡፡ ሁሉም ነገር በመዝገብ የተያዘ ነው፤›› ያሉት አቶ ነጂብ፣ አላና ፖታሽ ለማዕድን ፍለጋ ሥራው 90 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጉን፣ በወቅቱ ለ450 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል መፈጠሩን፣ አብዛኛው ባለአክሲዮን ድርሻውን ከስሮ መሸጡን ተናግረዋል፡፡
ሪፖርተር በስልክ ያነጋገራቸው የቀድሞ የአላና ፖታሽ ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፈርሃድ አባጎቭ፣ ከሕግ አማካሪዎቻቸው ጋር ተመካክረው ምላሽ እንደሚሰጡ ተናግረዋል፡፡
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች አይሲኤል ለገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የአላና ዕዳ የሆነ ወደ 10 ሚሊዮን ዶላር (200 ሚሊዮን ብር) የታክስ ግብር ለመክፈል ሐሳብ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም፣ ባለሥልጣኑ 55 ሚሊዮን ዶላር የካፒታል ዕድገት ታክስ ጨምሮ እንዲከፍል በመጠየቁ ሳይስማሙ ቀርተዋል፡፡
እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 4 ቀን 2016 አይሲኤል (አላና ፖታሽ አፋር) ለገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንና ለማዕድን ፔትሮሊየምና የተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ የዳሎል ፖታሽ ፕሮጀክቱን ዘግቶ ለመንግሥት ማስረከብ እንደሚፈልግ፣ አላና ፖታሽ አፋር የሚጠበቅበትን (ያለበትን) በሰነድ የተደገፈ ግብር እንዲሁም ሌላ ማንኛውም ዕዳ ካለ ለመዝጋት ፍላጎት እንዳለው አሳውቋል፡፡ ፕሮጀክቱን ለመዝጋት የሚልካቸውን ባለሙያዎች ምንም ዓይነት ችግር እንደማይፈጠርባቸው ዋስትና እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡
ሪፖርተር ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን አስተያየት ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም፡፡ አይሲኤል ለጻፈው ደብዳቤ እስካሁን ከመንግሥት በጽሑፍ የተሰጠ ምላሽ አለመኖሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሪፖርተር ለአይሲኤል ኃላፊዎች በኢሜይል አድራሻቸው ለላካቸው ጥያቄዎች ማተሚያ ቤት እስከገባበት ሰዓት ድረስ ምላሽ አላገኘም፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የማዕድኑ ዘርፍ ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት አስተዋጽኦ ሊያደርግ እንደሚችል የገለጹ ቢሆንም፣ ኢኮኖሚው በማዕድን ዘርፉ ላይ ጥገኛ እንዲሆን መንግሥታቸው እንደማይፈልግ አስረድተዋል፡፡ 

Thursday, January 12, 2017

ጨለንቆ አኖሌና “ኦሮሞው” የአጼ ሚኒሊክ ጦር ..#ግርማ_ካሳ



አኖሌን ምእራብ አርሲ ዞን፣ ጨለንቆ ደግሞ ምስራቅ ሃረርጌ ዞን ያሉ ከተሞች(መንደሮች) ናቸው። በሁለቱ ከተሞች በሚሊኖች የሚቆጠር ገንዘብ ወጭ ሆኖ ሁለት ሃዉልቶች ተሰርተዋል። ክሊኒክና ትምህርት ቤት ሊገነባበት ሲችል።
በነዚህ ቦታዎች ከመቶ አመታት በፊት ጦርነቶች ተደርገው ነበር። ጦርነቶቹ በአጼ ሚኒሊክ ጦር አሸናፊነት የተጠናቀቁ ናቸው። የሃዉልቶቹም አላማ ታሪክን ለማስታወስ፣ ወይንም ከታሪክ ለመማር ሳይሆን፣ በኢትዮጵያዉያን መካከል ጥላቻን ለመርጨትና ኢትዮጵያን ያቀኑ ታላቅ መሪን ስም ለማጉደፍ ነው።
እነዚህ ሃዉልቶች ምን ያህል የታሪክ መሰረት እንዳላቸው በራሱ አጠያያቂ ነው።
በጨለንቆ ጦርነቱ በጥቂት ሰዓታት የተጠናቀቀ ጦርነት ነበር። በጥቂት ሰዓታት ዉስጥ ያዉም ዘመናዊ ባልሆኑ መሳሪያዎች የተደረገ ጦርነት ብዙ እልቂትም እንዳስከተለ አድርጎ ማቅረቡ በታሪክ አንጻር አያስኬድም። አንድ በሉ።
ጦርነቱ የተደረገው ከኦሮሞ ገዢዎች ጋር አልነበረም፤ ከአዳሉ ገዢ ከሃረሩ ኤሚር አብዱላሂ ጋር ነበር። በሃረር የነበረውን ኤሚር፣ የኦሮሞ ብሄረተኞች እንደ ረቢ(መምህር) የሚቆጥሯቸው ዶር አሰፋ ጀለታ፣ የቱርክ ግብጽና አደሬዎች ጥምረት ( Turko-Egyptian and Adare alliance ) ብለው ነው የሚገልጹት። ይህ ጥምረት ለዶክተር አሰፋ ጀለታ ኦሮሞውን የጨቆነና አደሬዎችን ያፈረጠመ ጸረ-ኦሮሞ ጥምረት ነው። “ The gada system was attacked in eastern Oromia by the Turko-Egyptian and Adare alliance. The interethnic alliance and interdependence between the Adare and the eastern Oromo were shattered when the faction of the former invited the Turko-Egyptian power to colonize the Hararghe region in 1875.132 Under the Turko-Egyptian rule, between 1875 and 1885, the Adare consolidated their power and accumulated wealth and capital at the cost of the majority Oromo.” ሲሉ ነው ዶር አሰፋ የጻፉት። ዶር አሰፋ የ”ኦሮሞ ጠላት” አድርገው ያቀረቡትን አገዛዝ፣ አጼ ሚኒሊክ ማስገበራቸው በምን መልኩ በኦሮሞ ላይ ብቻ ያነጣጠረ ጥቃት ተደርጎ መወሰዱ በራሱ አስቂኝ ነው። ሁለት በሉ።
የጨለንቆ ጦርነት ከመደረጉ በፊት፣ አጼ ሚኒሊክ ልክ በወለጋና በጂማ እንዳደረጉት የሃረሩ ኤሚር፣ እንዲገብሩና ስልጣኑን እንደያዙ እንዲቀጥሉ ተማጽኖ አቅርበዉላቸው ነበር። ሆኖም የሃረሩ ኤሚር “ክርስቲያኖች ገናን ስለሚያከብሩ ይዘናጋሉ” በማለት፣ በገና ቀን በአጼ ሚኒሊክ ጦር ላይ ጦርነት ከፈቱ። ሆኖም ተሸንፈው አፈገፈጉ። በጨለንቆ የመጨረሻው ድል ሆነ። እንግዲህ የጨለንቆ ጦርነት በዚህ መልኩ፣ በወቅቱ በነበረው አስተሳሰብ ሰላማዊ የሆኑ አማራጮች ሁሉ በመሟጠጣቸው የተደረገ ጦርነት ነበር። ሶስት በሉ።
በአኖሌ፣ የአጼ ሚኒሊክ ወታደሮች የሴቶችን ጡት ቆርጠዋል በሚል እንደ አቶ ተስፋዬ ገብረአብ ያሉና አንዳንድ የኦሮሞ ብሄረተኞች ሲጽፉና ሲናገሩ ሰምተናል። ሆኖም ይሄን ታሪክ አፈታሪክ ነው ከማለት ዉጭ የጽሑፍ ማረጋገጫ ያቀረበ አንድም አካል የለም። በወቅቱ፣ ከዚያም በፊት የነበሩ ታሪኮችን የዘገቡ ብዙ የሙስሊም ጸሃፊዎች፣ ከአዉሮፓ የመጡ፣ እዚያው አገር ቤት የተወለዱ ነበሩ። ሆኖም አንድም ይሄ በአኖሌ ተደረገ የተባለውን በጨረፍታ እንኳን ( remotely)ያሰፈረ የለም። አፈ ታሪክ ብቻ ነው። አፈ ታሪክም በወቅቱ የነበሩ የአርሲ ተዋጊ መሪዎች ወታደሮች ለመመልመል የነዙትና እና ከመደጋገሙ የተነሳ እንደ እውነት ተደረጎ በአንዳንዶች የተወሰደ ሊሆን ይችላል።አራት በሉ።
እርግጥ ነው በአርሲ ለንጂሶ ዲጋ የተባሉ የአርሲ ኦሮሞ መሪ፣ ለአጼ ሚኒሊክ አልገብርም በማለት ከአራት አመት በላይ ከፍተኛ ትንቅንቅ እንዳደረጉና በኋላ እጅ እንደሰጡ ይነገራል። በጦርነት ብዙ ሰው መሞቱ የማይቀር ነው። በአርሲ ብቻ ሳይሆን በወላይታም ተመሳሳይ የሆነ ጠንክራ ጦርነት አጼ ሚኒሊክ ገጥሟቸውም ነበር።
ሌላ የአርሲ ኦሮሞ መሪ ሮባ ቡቤ ይባሉ የነበሩና በኋላ ሮባ ቡታ የሚል መጠሪያ የተሰጣቸው ፣ ሲጄመር ለአጼ ሚኒሊክ የመገበር ፍላጎት ያልነበራቸው፣ በኋላ ግን በሰላም የገበሩ መሪ ነበሩ። ይሄንን የሚገልጽ ብዙ የጽሁፍ መረጃዎች አሉ። እንግዲህ በአኖሌ ተፈጸመ የተባለው በተፈጸመበት ወቅት የነበሩ የነ ለንጂሶ ዳጋ እና ሮባ ቡታ ገድል በስፋት ተጽፎ፣ የአኖሌ ታሪክ በጽሁፍ አለመቅረቡ በራሱ አጠያያቂ ነው።
ለንጂሶ ዲጋ እና ሮባ ቡታ በአርሲ ኦሮምዎች ዘንድ በጣም ተወዳጅ የነበሩና የተከበሩ መሪዎች ነበሩ። ምንም ጥላቻን እና መከፋፈልን ከመንዛት ዉጭ ለኦሮሞው ማህበረሰብ የማይጠቅመውን የአኖሌና የጨለንቆ ሃዉልቶችን ከማቆም፣ እነዚህን የኦሮሞ መሪዎችን ታሪክ የሚዘክር፣ ያደረጉት አስተዋጾ የሚያስተምር ሃዉልቶች በአርሲ ቢሰሩ ባልከፋ ነበር። አስተማሪም ነበር የሚሆነው።
ከመቶ አመታት በፊት ጠንካራ የኦሮሞ ግዛት በሚባለው በጂማ ይገዙ የነበሩት ኦሮሞው አባ ጂፋር፣ ከአጼ ሚኒሊክ ጋር ስምምነት ስላደረጉ ምንም አይነት ጦርነት በዚያ አልተደረገም። አባ ጅፋር አጼ ሚኒሊክ ከሞቱ በኋላ እስከ 1932 ዓ.ም በጂማ አገረ ገዢ ነበሩ። በወለጋ የለቂ ነቀምቴ ሞቲ ወይም ገዢ የነበሩት ሞሮዳ በቀሬ፣ በሰላም ለራስ ጎበና የአጼ ሚኒሊክ ጦር የጦር አዛዥ ገብረው፣ የወለጋ ገዢ ሆነው መቀጠላቸው ተጽፏል።
አጼ ሚኒሊክ ተነጥለው ይከሰሳሉ እንጅ፣ ከአጼ ሚሊኒክ ጀርባ ሆነው አገሪቷን ያሽከርክሩ የነበሩት በአብዛኛው ኦሮሞዎች ነበሩ። ያለ ኦሮሞዎች የአጼ ሚኒሊክ መንግስት የትም አትደርስም ነበር። የአጼሚኒሊክ ጦር የ”ኦሮሞ” ጦር ነበር ማለት ይቻላል። አጼ ሚኒሊክን ራሱ ከአጼ ቴዎድሮስ ካመለጡበት ጊዜ ጀምሮ ተንከባክበው ጠንክራ ሆነው እንዲወጡ ያደረጉት በዋናነት ኦሮሞዎች ነበሩ።
እንግዲህ በኢትዮጵያ ዉስጥ ብዙ ጦርነቶች ተደርገዋል። ለምሳሌ የተወሰኑትን ብንጠቅስ፡
– በአስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን ግራኝ መሀመድ ድፍን ኢትዮጵያን ተቆጣጥሮ በነበረበት ወቅት በተለያዩ ቦታዎች የተለያዩ ጦርነቶች ተደርገዋል። የግራኝ ጭፍጨፋ ለማስታወስ ስንት ሃዉልቶች መሰራት አለባቸው ?
– እነ አጼ አምደጺዮንም ሃዲያ የመሳሰሉትን ሳይቀር በጦርነት አስገብረዋል። ስንት ሃዉልቶች መሰራት አለባቸው ?
– ከዚህ በፊት የተያዘብንን መሬት ለማስለቀቅ እንደሆነ አድርገው ነው የሚናገሩት። ግን ራሳቸው የኦሮሞ ልሂቃን ( እንደ ዶር አሰፋ ጀለታ ያሉ) ከ1522 እስከ 1612 የቡታ ጦርነቶች የሚባሉ አወጀው ኦሮሞዎች እንደተስፋፉ ይገልጻሉ። ዶር አሰፋ ሲጽፉ “ The Oromo fought twelve butta wars between 1522 and 1618, recovering, expanding, and establishing Oromia to its present boundaries.19 In the course of their continued expansion into various regions, different groups established autonomous gada governments” ነበር ያሉት። “recovering” የሚለው ጦርነቱ ለመደረጉ ምክንያት ለመስጠት ተብሎ የቀረበ አጠያያቂ ቢሆንም “ expanding, and establishing “ የሚለው ግን ትክክለኛና ሊሰመርበት የሚገባው። በድፍን ኢትዮጵያ ነው የቡታ ጦርነት የተደረገው። እንግዲህ ስንት ሃዉልት ማሰራት ሊኖርብን ነው ?
– ከሃረሩ ኤሚር ጋር አጼ ሚኒሊክ ብቻ አይደለም የተዋጉት። በ16ኛው ክፍለ ዘመን የሃረሩ ኤሚር ኑር ኢብን ሙላሂድ በኦሮሞ ተዋጊዎች በጦርነት ተሸንፎ ነበር። በሃረር ሌላ ሃዉልት ሊያስፈለግ ነው ማለት ነው ?
– በዘመነ መሳፍንት ንጉሶች ስም ብቻ እንጂ ስልጣን የነበራቸው መሳፍንቱ ነበሩ። ከመሳፍንት ጠንካራ የሆነ የንጉሱ እንደራሴ ተብሎ ይጠራ ነበር። ከ1828 እስከ 1831 በደብረ ታቦር የንጉሱ እንደራሲ ሆነው የነበሩ የየጁ ኦሮሞው ማሪዬ ተከዜን ተሻግረው በትግራይ ከነበሩ ደጃዝማች ሳባጋዲስ ጋር ባደረጉት ከፍተኛ ጦርነት ብዙ ሰው ሞቷል። በትግራይ መቀሌ ካለው የሰማእታት ሃዉልት በተጨማሪ ሌላ ሃዉልት መሰራት ሊያስፈልግ ነው ማለት ነው ?
– በ1844 የጂማ ኦሮሞ ሞቲ በሲዳማ ጃንጃሮ ግዛት ላይ ጦርነት ከፍቶ ብዙ ሲዳማዎች አልቀዋል። በ3 አመታት በኋላ የጃንጃሮ ንጉሱ መልሶ ከጂማ መንግስት ነጻ ሊወጣ ችሏል። በ1880 አባ ጂፋ የጂማው እንደገና ጦርነት ከፍተዉ የጃንጃሮችን ግዛት ወረው ከግዛታቸው ጋር ጠቅልለዋል። በጃንጃሮ ሃዉልቶች ያስፈለጋሉ ማለት ነው ?
– በ1882 የእምባቦ ጦርነት በሚባለው በሸዋ ንጉስ ሚኒሊክ ጦርና በጎጃም ንጉስ ተክለሃይማኖት ጦር መካከል ከፍተኛ ደም መፋሰስ የነበረበት ጦርነት ተደርጓል። በጦርነቱ ንጉስ ተክለሃይማኖት ይሸነፋሉ። አጼ ዩሐነስ እና ዋግ ሹመ ጎበዜ ወይም አጼ ተክለጊዮርጊስ ከፍተኛ ዉጊያ አድርገው ። ዋግ ሹም ጎበዜ ተሽንፈዋል። በሸዋ አጼ ቴዎድሮስ ከአጼ ሚኒሊክ አባት ንጉስ ሃይለመለኮት ጋር ተዋግተው ሸዋን አስገብረዋል።
የሰገሌ ጦርነት በሚባለው በኦሮሞው የወሎ ንጉስ ሚካኤል እና በጨቦ ኦሮሞ ፊታወራሪ ሃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ(አባ መላ) መካከል የተደረገው ጦርነት በአባ መላ አሸናፊነት ተጠናቋል።
እንግዲህ እንዲህ እያልን እጅግ በጣም ብዙ የጦርነት ታሪኮችን መዘርዘር እንችላለን። ለዚያ ሁሉ ጦርነቶች ሃዉልት ልናቆም ነው ማለት ነው ?
የአገራችን ብቻ ሳይሆን የሌሎች አገሮች ታሪኮችም የጦርነት ታሪኮች ነው። አገሮች የተገነቡት በጦርነትና በመስፋፋት ነው። የድሮ ዘመን ሰዎችን አሁን ባለን ሊበራል ዴሞክራሲ አስተሳሰብ መመዘኑ ደካማነት መሆኑን ተረድተን፣ ተበደልኩ፣ ጦርነት ተከፍቶብኝ ነበር ያለ ሕዝብ እርሱም በሌላ የታሪክ አጋጣሚ ጦርነት የከፈተና የበደለ መሆኑ አስበን፣ ስንት የከፉ ጦርነቶች እያሉ ሁለቱን ብቻ ነጥሎ በማውጣትና ሃዉልት በማቆም፣ አንድ ማህበረሰብ ብቻ ለማጥቃት የሚደረገው ደባ ቆሞ፣ በዚህም ሆነ በዚያ ሁላችንም አሁን ኢትዮጵያ በምትባል አንዲት አገር ዉስጥ ያለን መሆናችንን ተረድተን፣ ከዘረኝነት በጸዳ መልኩ ተያይዘን፣ ተከባብረን በፍቅር አገራችንን ብንገነባ ነው ይሻላል። ከታሪክ እንደምንማረው አሁን ባለችው ኢትዮጵያ ከአማራው፣ ከትግሬው ባልተናነሰ የኦሮሞው አሻራ አለበት። ኦሮሞነት ኢትዮጵያዊነት ነው። ኢትዮዮጵያዊነትን የሚጠላ ኦሮሞ ኦሮሞ አይደለም። ታሪክን የማያውቅ፣ በጥላቻ የታወራ የዉሸት ኦሮሞ ነው።
http://trace.tennessee.edu/cgi/viewcontent.cgi?article=1005&context=utk_socopubs
http://gadaa.com/oduu/22246/2013/10/06/arsi-oromo-political-and-military-resistance-against-the-shoan-colonial-conquest-1881-6/

ወልቃይት ጠገዴ ግንባር ከትግራይ የተነሳ ሃይል ተደመሰሰ | ገዱ አንዳርጋቸው በወታደሮች ታጅቦ ደባርቅ ይገኛል የሙሉነህ ዮሐንስ ዘገባ



ሰሜን ጎንደር ወልቃይት ጠገዴ ግንባር ከትግራይ የተነሳ ሃይል ተደመሰሰ | 16 ሙቶ ብዙ ቆሰለ | ገዱ አንዳርጋቸው በወታደሮች ታጅቦ ደባርቅ ይገኛል
የሙሉነህ ዮሐንስ ዘገባ
Image may contain: outdoor
ከትግራይ በሽራሮ በኩል ተከዜን ተሻግሮ ወደ ወልቃይት ጠገዴ ይጓዝ የነበረውን የወያኔ ወታደራዊ ኮንቮይ አድፍጠው የቆዩ የአካባቢው ጀግኖች ከፋኞች ድባቅ መተውታል። እጅግ የሚያስደስተው ደግሞ ወያኔ ይጠቅሙኛል ብሎ ያሰባቸው ያካባቢ ሚሊሺያ ታጣቂወች ከህዝቡ ጋር አብረው ተሰልፈው የወያኔ ሃይል መውጫ እንዳያገኝ አድርገው ቀጥተውታል።
በደረሰን መረጃ መሰረት 16 ወያኔ ተገሎ ወደ 30 ሲቆስል ብዛት ያለው ቀላልና የቡድን መሳሪያወች ተማርከዋል። ሰፊውን የሁመራ ወልቃይት ጥገዴና ጠለምት መሬቶች በገፈፋ ከጎንደር የነጠቀው ወያኔ አሁንም እንደ ግጨው የመሰሉ ሰፋፊ የጠገዴ ተጨማሪ ቦታወችን ወደትግራይ ለመውሰድ ከመሞከር አልቦዘኑም። ተከዜን ተሻግረው ካልሄዱ ጤናም የለ እረፍትም የለ! ጎንደር ወስኗል! አማራ ወስኗል! ኢትዮጵያም ወደ ቀደም ክብሯ ትመለሳለች::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ የአማራ ክልል ር ዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ሰሜን ደባርቅ ከተማ እንደሚገኝ ታወቀ:: ዛሬውኑ ዳባት ደርሶ ወደጎንደር እንደሚመለስ መረጃ አለ::
ፎቶው ያጀቡትን ዘመናዊ መኪኖችና የወታደር ጋጋታ ያሳያል። የፈሪ ዱላ! የምንትስ ባል ከሞት አያስጥል! ለልምምጥ የሄደው ገዱ የህዝብን ጥያቄ መመለስ አይችልም።
Image may contain: one or more people and outdoor
የጎንደር ሕዝብ ላይ አለቆቹ ወያኔዎች ሙሉ ጦርነት ሲከፍቱበት ከአሽከርነት የላቀ ድርሻ የሌለው የበድኑ የብአዴን መሪ ገዱ ሰልፉን እንዲያስተካክል ያገኘውን አጋጣሚ ሁሉ አሟጦ እየጨረሰ ነው። ወያኔም ጉርቦውን ልትፈጠርቀው አድብታ እየጠበቀች ነው።
ወያኔን በቅጡ የተረዷትና የቀደሟት የተከፉ የጎንደር ጎበዝ አለቆች ናቸው! ሰሞኑን ቆላማውን የወገራ ህዝብ ከጎበዝ አለቆች ጋር አሸማግሉኝ ምህረት ይጠይቁ እያለች ከንቱ ልፋት ላይ ነች።
የነፃነት ጥያቄ በአፈና አይመለስም!
ህዝብ ያሸንፋል©!

“አይነኬዎች በተፈጠሩበት ሙስናን መታገልም ዝም ማለትም አገር ያፈርሣል” – ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ቆንጅት ስጦታው



“አይነኬዎች በተፈጠሩበት ሙስናን መታገልም ዝም ማለትም አገር ያፈርሣል” – ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ
አዲስ አድማስ
“…ለግሪካውያኑ ፈላስፎች ለእነ አርስቶትልና ፕሌቶ ሙስና አገር የሚያፈርስ ነገር ነው፡፡ ለምሳሌ አርስቶትል፤ “ሙስና የፍትህ ስርአት ነፀብራቅ ነው፤ ፍትህ የሁሉም ነገር አያያዥ ሰንሰለት ነው” ይላል፡፡ ለአርስቶትል ፍትህ ማለት ማህበረሰቦች እንደየተፈጥሮአቸውና ይዘታቸው የራሳቸውን ድርሻ ብቻ ሲወጡ ነው፡፡ ሙስና የሚመነጨውም የማህበረሰቡን ውህደትና ሰላም ከማደፍረስ ነው ይላል አርስቶትል፡፡ ይህ ማለት ሙስና በሰፈነበት ሀገር ባለስልጣናት ከግላዊ ጥቅም ብቻ በመነሳት የማህበረሰብን ጥቅም በመንካት ሀገርን የሚያፈርሱ ናቸው ማለት ነው፡፡
የጣሊያኑ ፈላስፋ ጁሊያስ ሲሴሮም ስለ ሙስና የሚያስቀምጠው ትርጉም ተመሳሳይ ነው፡፡ “የሙስና ተቀዳሚ መሰረት የሚሆነው ማህበረሰቡን ለማስተዳደር በኃላፊነት የተቀመጡ ሰዎች በፍቅረ ንዋይ እየተነዱ ከዋና ተግባራቸው ሲወጡ ነው” ይላል፡፡ ይህ ባለስልጣናት ከነጠላ ጫማ ወደ ሀመር መኪና በአንዴ ሲሸጋገሩ እንደማለት ነው … ፈላስፋው ከዚህ አይነት ችግር መውጣት የሚቻልበትን አቅጣጫ ሲያስቀምጥ፤ የፖለቲካ አመራሩን ገርቶና ኮትኩቶ ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ መመለስ መቻል ብቻ ነው ይላል፡፡
የሮማው የታሪክ ፀሐፊ ሌቪ በበኩሉ፤ የተወሰኑ ሰዎች (ማህበረሰቦች) ብረት ያነግቡና ሰራዊት ያቋቁሙና በጦርነት አንድን ሀገር ይወራሉ፣ ከወረሩ በኋላ ምቾት፣ ቅንጦት፣ ድሎት ሲበዛ ወደ ሙስና ቁልቁለት ውስጥ ይገባሉ ሲል ይገልፃል፡፡ እውነት ነው፡፡ የመሳሪያ ድልና ሙስና የተያያዙ ናቸው፡፡ ሙስና የተንሰራፋበት ስርአት ዝም ብለው ቢተዉት ወደ ማይቀረው ውድመት መውረዱ አይቀርም፤ በአንፃሩ ደግሞ የተስፋፋውን ሙስና ለመግታት ቢሞክር፣ ለማስተካከል በሚደረገው ግብ ግብ ስርአቱ አይቀሬ ይሆናል፤ ይላል ይህ የሮማ ታሪክ ፀሐፊ፡፡ አሁን እኔ ይሄን በጥያቄ ነው የማልፈው፡፡ በኛ ሀገር ተጨባጭ ሁኔታ የፖለቲካ አዙሪት ውስጥ ገብተናል ወይ? ሙስና መኖሩን መንግስትም ተቀብሎታል፡፡ መንግስት ሙስና መኖሩን ከተቀበለ ዘንዳ ዝም ብሎ ቢተወው ስርአቱን ይንደዋል፤ እናስተካክል ቢልም ስርአቱን ይንደዋል፡፡ ዋናው ጥያቄ አሁን የቱ ጋ ነን የሚለው ነው፡፡
እኛ ሀገር ያለው ሙስና የሚነሳው ከፖለቲካ ነው። በዚህ ላይ መተማመን ላይ ከተደረሰ ሙስናው ስርአታዊ ነው ወይንስ ከግለሰቦች የመነጨ? እነ እገሌ በሞራል ስለላሸቁ ነው ወይንስ ስርአቱ ራሱ ሞሳኝ ስለሆነ ነው? ሙስና ወይም ምዝበራ የፖለቲካ ትንታኔ ሆኖ ሲቀርብ መጀመሪያ መነሳት ያለበት ጥያቄ፣ በስርአትና በግለሰብ መካከል ያለው ግንኙነት ነው፡፡ በቅዱሳት መፅሃፍት በመጀመሪያ ቃል ነበር ተብሏል፡፡ በፖለቲካ ትንተናም በመጀመሪያ ስርአት ነበር፡፡ ስለዚህ ሙስና የግለሰብ የሞራል መበስበስን የሚያሳይ ቢሆንም መነሻው ከስርአት ጋር የተቆራኘ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በሌላ አባባል በኛ ሀገር ያለው ሙስና መነሻው ስርአት ነው፡፡
ምን አይነት ስርአት ላይ ነው ያለነው?
የኢህአዴግን ጉዳይ ከፖለቲካ አኳያ ውስብስብ የሚያደርገው፣ ስርአቱ የፖለቲካ ህይወቱን የጀመረው ህገ መንግስት አዘጋጅቶ ከማቅረብ ነው፡፡ በመሆኑም ኢህአዴግ ከህገ መንግስቱ ጋር ያለው ግንኙነት ምን ይመስላል ብሎ መፈተሽ ያስፈልጋል፡፡ ከህገ መንግስቱ አኳያ ስንመለከት፣ ሙሉ ለሙሉ ህገመንግስቱን ጥሎ፣ አውሮፓውያን “ቄሳራዊ” እንደሚሉት ፈላጭ ቆራጭ ስርአት አልተመሰረተም፡፡ ከዚህ ይልቅ የኢህአዴግ አካሄድ ህገ መንግስቱን በከፊል እየሻረ ሲያሻው ደግሞ እያከበረ የሚንቀሳቀስ፤ ስልጣን በጥቂት ሰዎች እጅ የተከማቸና መሪዎች የህግ ማዕቀብ ሳይጣልባቸው የፈለጉትን የሚያደርጉበት ስርአት መሆኑ ነው፡፡ በህገ መንግስቱ ላይ ፍፁማዊ የበላይነትን የተጎናፀፈ ስርአት ነው፡፡
እዚህ መደምደሚያ ላይ የደረስኩት ስርአቱ ሁለት መሰረታዊ ጥሪዎችን ማስተናገድ አለመቻሉን ተመልክቼ ነው፡፡ በአንድ በኩል የዲሞክራሲ ጥሪን ማስተናገድ አልቻለም፤ በሌላ በኩል የሊበራሊዝም ጥሪንም ማስተናገድ አልቻለም፡፡ የዲሞክራሲ ጥሪው የስልጣን ክፍፍል ላይ ነው፡፡ ሊበራሊዝም የሰውን መብቶችና ነፃነቶች የሚያካትት ነው፡፡ አሁን ላለፉት 14 እና 15 ዓመታት የምየናው በዲሞክራሲና ሊብራል እሴቶችና በስልጣን ላይ ለመቆየት የሚደረግ ፍልሚያን ነው፡፡
በዚህ በኩል የዲሞክራሲ ጥሪ አለ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የኢህአዴግ በስልጣን ላይ የመቆየት ፍላጎት አለ፡፡ አሁን ሁለቱ እየተጋጩ እየተመለከትን ነው። ሁለቱ በተጋጩ ጊዜ አሸናፊው ማን እንደሚሆንም ግልፅ ነው፤ ዲሞክራሲ የታጠቀ ኃይል የላትም፣ በአንፃሩ በስልጣን የመቆየት ፍላጎት በሚገባ የታጠቀ ሀይል አለው፡፡ ሁለቱ ሲጋጩ አሸናፊው ወይም ጨፍላቂው ግልፅ ነው፡፡ በዚህ መሃል ዜጎች ሰለባ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡
የኢህአዴግ ጥንተ አብሶ (The original sin) የሚነሳው ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልን መነሻ አድርጎ የሚሄድ ስርአት ካለመሆኑ ነው፡፡ አንድ ኢትዮጵያዊ ፕሮፌሰር፤ “ኢህአዴግ ማን ሀብታም ማን ድሃ መሆን እንዳለበት የሚወስን ድርጅት ነው” ይላል። ቁጭ ብሎ ይህቺን ሰውዬ ሀብታም እናድርጋት እንዴ? ይህቺ እንኳ ድሃ ትሁን እያለ የሚወስን ነው። ለዚህ ነው ትናንት በእግሩ ሲኳትን የነበረ ዛሬ ሰው፣ የ2 ሚሊዮን ብር መኪና እየነዳ ገርምሟችሁ የሚያልፈው፡፡ የኔ አባት ነጋዴ ነው፡፡ 20 ሺህ ብር ትርፍ ለማግኘት 40 ዓመት ነው የሰራው፡፡ አሁን አንድ ወጣት ሀብታም መሆን ከፈለገ መጀመሪያ ማድረግ ያለበት ወደ መንግስት መጠጋት ነው፡፡ የመንግስት ሰራተኛ መሆን አንድ ሀብታም የመሆኛ መንገድ እየሆነ ነው፡፡
መጀመሪያ በፓርቲ ይቧደናሉ። ማዘጋጃ ቤት ውስጥ የሆነ አስተዳደር ይሆናል፡፡ እንደምንም ብሎ 5000 ካሬ ሜትር ቦታ ካገኘ እሷን በሚሊዮን ብር ይሸጣል፡፡ በቃ ሀብታም ሆነ ማለት ነው፡፡ አንዱ የዘመናችን ሙስና መገለጫ ይሄ ነው፡፡ አሁን ያለው ጭንቀት ስርአቱን እናስተካክለው ቢሉት ሊፈርስ ነው፣ ዝም ብለው ቢተዉትም ሊፈርስ ነው። ስለዚህ አዙሪት ውስጥ ገብተናል ማለት ነው፡፡ ሁለተኛው አዙሪት ደግሞ አንድ ስርአት ዲሞክራሲና ሊበራሊዝም ሲጎድለውና በጥቂት ቡድኖች ሲመራ የህግና የፖለቲካ አይነኬዎችን ይፈጥራል፡፡ ከህግ በላይ የሆኑ በፖለቲካ የማይጠየቁ፣ ደፋር የሆኑ ሀብታሞችን ይፈጥራል፡፡
የአፄውንና የአሁኑን ስርአት በነዚህ አመክንዮዎች ካወዳደርን የሰማይና የምድር ያህል ይራራቃሉ። በአፄው ዘመን፣ እነ ራስ፣ እነ ቢትወደድ፣ እነ ደጃዝማች… ስልክ እንኳ ዝም ብለው አይጠቀሙም። አንድ ጊዜ መኳንንቶቹ የስልክ ሂሳብ ሳይከፍሉ እዳቸው 5 ሺህ ብር ደረሰ። በወቅቱ የዘርፉ ኃላፊ የነበሩት አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ፤ “ቄሳርና አብዮቱ” በሚለው መፅሃፋቸው እንደገለፁት፤ የእነዚህን ከፍተኛ የሀገር አመራሮች ስልክ አስቆርጠዋል፡፡ የልኡላኖቹን ጨምሮ ማለት ነው፡፡ እነዚህ ባለስልጣናት እንዴት እንነካለን ሲሉ ለንጉሱ አቤቱታ ያቀርባሉ፡፡ ንጉሱም ታዲያ “ምናችሁ ተነካ? ትክክል ነው የተደረገው፤ ለምን አትከፍሉም?” ብለው እንዲከፍሉ ተገደዋል፡፡ በወቅቱ እንግዲህ አይነኬዎች አልነበረም ማለት ነው፡፡
አሁንስ? የማንን ስልክ ማን ያስቆርጣል? አደገኛ ነው፡፡ በፊት በፊት እኛን መመርመር አይቻልም” ያሉ የዘመናችን የመንግስት ተቋማትን አይተናል፡፡ ይሄ እንግዲህ የፖለቲካ አይነኬዎች መፈጠራቸውን ያረጋግጥልናል፡፡ መሬት የዘረፉ እጃቸውን ቸብ ቸብ ተደርገው፣ ተቀጡ ተብለው ወዲያው ይለቀቃሉ፡፡ አንድ ሞባይል የመነተፈ ግን አደገኛ ቦዘኔ ተብሎ ከ2 ዓመት በላይ ይታሰራል፡፡ የፖለቲካ ኃይልና የዘረፋ ኃይል ውህደቱ ከፍተኛ ነው፡፡ “ይሄ የኔ ሰው ነው፤ አትንካው” የሚባልበት የአይነኬዎች ስርአት ነው የምለው ከዚህ አንፃር ነው፡፡
በንጉሱ ጊዜ የሆነ አንድ እውነተኛ ታሪክ አለ፡፡ አንድ የመንግስት ገንዘብ ያዥ 2ሺህ ብር ይሞስንና ዳኛ ፊት ይቀርባል፡፡ ዳኛው ጥፋተኛነቱን ካረጋገጡ በኋላ … “ሰማህ አንተ” ይሉታል (መዳፋቸውን ጨብጠው) “የመንግስት ገንዘብ እንደዚህ ነው የሚያዘው፤ ጨመቅ …. ጨመቅ ስታደርጋት ፍጭጭ እያለች በጣቶችህ መሃል ስትወጣ እሷን ላስ ታደርጋለህ እንጂ መዳፍህን ከፍተህ እንዴት በሙሉ ትገምጠዋለህ” አሉት፡፡ አሁን ግን ሁሉም ነገር ተገምጦ አልቋል፡፡
በደርግም ሆነ በንጉሱ ጊዜ ሀብታምና ድሃው ልዩነቱ ግልፅ ነበር፡፡ ሀብታም የሚባለው ጫማ ያደርጋል፡፡ ቤቱ ቋንጣ፣ ጠጅ ምናምን ይኖራል፣ ወይም አንድ ሁለት ውሽማ አላቸው፤ ሌላ የላቸውም፡፡ አሁን ግን እንዴት እየኖርን እንደሆነም አይታወቅም፡፡
ዛሬ በዚህ ሀገር፤ “የ380 ሺህ ብር አልጋ አግኝቼ ልገዛ ነው” ፣… “እንዴት ርካሽ አልጋ አገኘህ!” እያሉ የሚያወሩ ሰዎችን እያየን እኮ ነው፡፡ በዚያው ልክ ቀን ከሌት ላቡን ጠብ እያደረገ አንዲት የማዳበሪያ ፍራሽ ለመግዛት በተስፋ የሚኳትን ደግሞ ቤቱ ይቁጠረው፡፡ በዜጎች መካከል በእውነት ምን ያህል ልዩነት እንዳለ እኔም አይገባኝም ወይም ለመግለፅ ከብዶኛል…፡፡”

Wednesday, January 11, 2017

ከፍተኛ አመራሩ ተጠያቂ ያልሆነው ማስረጃ ስለሌለ ነው›› ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ EthiopianReporter.com  



–  ማስረጃ ከተገኘ የትኛውንም አመራር አንተውም ብለዋል
–  የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ለማንሳት የሚያጣድፍ ነገር አለመኖሩን ጠቁመዋል
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መደበኛውን ጋዜጣዊ መግለጫ ከሰጡ ሁለት ዓመት ገደማ ሆኖታል፡፡ ባለፈው ሰኞ ጥር 1 ቀን 2009 ዓ.ም. የግሉን ፕሬስ ጨምሮ ለውጭ

Tuesday, January 10, 2017

የጨለማ ተሃድሶ (ደምህት) source abay media

ህዝባችን ሰላም አግኝቶ የፍትህ ተጠቃሚና የስልጣን ባለቤት የሚሆንበት ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት ሲል ህዝባዊነት የሌላቸውን ጨቋኝ ስርዓቶች በክንዱ ድባቅ እየመታቸው እንደመጣ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው።
ሆኖም ግን “ባጎረስኩ እጀን ተነከስኩ” እንደሚባለው የአበው አባባል ሆኖ በመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ትግል መስዋዕት፣ ስልጣን ጨብጦ ያለው የወያኔ ኢህአዴግ ስርዓት፣ ከአለፉት ስርዓቶች አምባገነንነትን ወርሶ የህዝብ ስልጣንን ለብቻው በማድረግ፣ በገዛ ደሙ ወደስልጣን ባወጣው ህዝብ ላይ በየቀኑ ለመገመት የሚያስቸግር ግፍና በደል እያወረደ ይገኛል። ይህ አምባገነን ስርዓት በህዝብ ላይ ለሚፈፅመው በደል ለማረም የሚሰጠውን ምክር ባለመቀበሉ ወደባሰ ሁከትና ግርግር እንዳመራ የሚታወቅ ነው።
ስለሆነም የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉንም አይነት አማራጮች ሞክሮ ምላሽና ፍትህ በማጣቱ እንደቀድሞው በትግሉ የስርዓት ለውጥ ለማድረግ በሁሉም የአገራችን አካባቢዎች ህዝባዊ ዓመፅ ተቀጣጥሎ ይገኛል።
ይህንን ተከትሎም የኢህአዴግ ባለስልጣናት የስርዓት ለውጥ ለማምጣት በማቀጣጠል ላይ ያለውን ህዝባዊ አመፅ አቅጣጫውን ለማሳት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ ወደለየለት ወታደራዊ ትዕዛዝ ገብቷል። በንፁሃን ዜጎች ላይ እያካሄደው ያለው አፈናና ግፍ፣ በተለይ ደግሞ የአማራና የኦሮሞ ወጣቶችን ከአደባባይ እያፈሰ ወደ እስርቤቶችና ወታደራዊ ማሰልጠኛዎች እንዲወርዱ ፈርዶባቸዋል።
በተለይ ወደ ብርሸለቆ፤ ጦላይ፤ ይርጋለም፤ አዋሽ ዘጠኝና ሌሎችም ማሰልጠኛዎች የአገራችን ወጣቶች ስለመብታቸውና ተጠቃሚነታቸው ስለጠየቁና ስለተቃወሙ ብቻ በስርዓቱ የፀጥታ ሃይሎች ተደብድበዋል።  በጥይት ተረሽነዋል። በእነዚህ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እስርቤቶች ምንም አይነት ወንጀል የሌለው ንፁህ ወገን በጥርጣሬና በስጋት ብቻ በፀጥታ ሃይሎች ከቤቱ ውስጥና ከጎዳናዎች እየታፈሰ ለእስር በመዳረግ በረሃብና በጥማት ብሎም አሰቃቂ የወንጀል ምርመራ ቶርቸር አስገብቶ በማሰቃየት ያልዋሉበትን ድርጊት ወንጀለኛ ነኝ፣ አይደገምም በል እየተባሉ የሚሰቃዩት ዜጎች መቁጠሪያ የላቸውም።
በዚህ መሰረት ይህ ፀረ ህዝብ ቡድን መብቴን ያለውን ህዝብ በቁጥጥር ውስጥ እያስገባ፣ እናንተ መብት የሚባል ነገር አያስፈልጋችሁም። የሆነ አይነት ጥያቄ ካነሳችሁ እጣችሁ ይህ ነው እያለ አረመኔያዊ ተግባር እየፈፀመ አስገድዶ በማናዘዝ ከዚህ ከወጣችሁ በኋላ ደግሞ ወደሁከትና ግርግር አልመለስም፣ አልገባም ብላችሁ መሃላ ፈፅሙ እያለ የተወሰኑትን ትርጉም የሌለው የአፈና ታርጋ ለጥፎ ሲለቃቸው አብዛኞች ደግሞ በስቃይና በመከራ ስር ሆነው እጣቸውን በመጠባበቅ ላይ ናቸው።
በዚህ ሁኔት በስጋት ተውጦ ያለው የስርዓቱ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ለመብታቸውና ለተጠቃሚነታቸው ሲሉ ያቀረቡት ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ ተገደው ወደ አደባባይ በመውጣት የተቃወሙትን ዜጎች ዓመፅ አንስታችኋል እየተባሉ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛዎች ወርደው ለብዙ ወራት ሲሰቃዩ ከቆዩ በኋላ፣ ሰሞኑን “አይደገምም” የሚል ምልክት ያለው ጨርቅ በማልበስ የተለመደውን ተግባረቢስ ፕሮፖጋንዳ ሲናገርና ሲሰብክ ታይቷል።
ከእነዚህ አስመሳይ ቃላቱ ውስጥ የተወሰኑትን ለመግለፅ ያክል መንግስት የራሱ ችግሮች ያሉት መሆኑን በማመን እነዚህን ስህተቶች ለማረም ደግሞ በተሃድሶአችን ታርመናል፣ እናንተም የተሃድሶ ስልጠና ወስዳችኋል የሚል መማፀኛ ቢያሰማም እንኳ ይህንን ተግባር ግን ብዙ የፖለቲካ ተንታኞችና ምሁራን “ብርሌ ከነቃ አይሆንም እቃ” የተደረገው ተሃድሶም የጨለማ መንገድ ነው ብለውታል።
ምክንያቱም የወያኔ ኢህአዴግ አመራሮች ከመሃላና ከቃልኪዳን ባለፈ ከአረመኔያዊ ተግባራቸውና ከስልጣን ስስታቸው ተቆጥበው ለህዝብና ለሃገር የሚቆረቆር ህሊናና ህዝባዊ ወገንተኝነት ተሰምቷቸው በተግባር ሊሰሩና ሃገርን ከመበታተንና ከድህነት እንደማያድኑ ህዝብ በደንብ ያውቃቸዋል። ስለዚህ አሁንም ቢሆን ባወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት በህዝብ ላይ እያደረሰው ያለው ግፍና በደል እንዲያበቃና በሌላ በኩል ደግሞ ስርአቱ እያደረገው ያለው ወደ ጨለማ የሚያስገባ ተሃድሶ እንዲያከትም ሁሉም የበኩሉን ሊያደርግ ይገባል። ምክንያቱም መብታችን ይከበር ብሎ የጠየቀ ጭቁን ወገን ወደ አረንቋና ወታደራዊ ማሰልጠኛ እስርቤቶች ታጉሮ የጨለማ የተሃድሶ መንገድ ስለሚፈረድበት።

በጎንደር የቦንብ ፍንዳታ ደረሰ

                                 ሰበር ዜና
 ማምሻውን በደረሰን ዜና መሰረት በጎንደር ቀበሌ 18 በሚገኘው  ኢንታሶል   ሆቴል ቦንብ ፈንድቶ ሰዎች መጎዳታቸው ታውቋል።
በሆቴሉ ውስጥ ፋሲል የእግር ኳስ ቡድን የባንክን ቡድን ማሸነፉን ተከትሎ የሚዝናኑ ወጣቶች ነበሩ። ከ5 በላይ በጽኑ የቆሰሉ ሰዎች  ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ለማውቅ የተቻለ ሲሆን፣ ወታደሮችና ፖሊሶች አካባቢውን በመክበባቸው በትክክል የሞቱና የቆሰሉ ሰዎችን ቁጥር ለማወቅ አልተቻለም።
ዛሬ ማክሰኞ ጥር 2 ቀን 2009 ዓም ጠዋት ላይ ደግሞ አቶ ባረኮ በሚባል ቦታ ላይ ማንነታቸው ያልተወቁ ኃይሎች አንድ የፌደራል ገድለው የጦር መሳሪያውን ይዘው ተሰውረዋል።  ትናንት ዋርካ በሚባለው አካባቢም እንዲሁ መጠነኛ የቦንብ ፍንዳታ ተከስቶ ነበር።
ፍንዳታውን ማን እንዳደረሰው የታወቀ ነገር የለም። በቅርቡ በባህርዳር ከተማ በአንድ ሆቴል ላይ ተመሳሳይ ፍንዳታ መድረሱ ይታወቃል።

መንግስት በአመራሮቹ ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃ ግልፅ አይደለም ተባለ ቆንጅት ስጦታው



መንግስት በአመራሮቹ ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃ ግልፅ አይደለም ተባለ
‹‹በሙስና ተጠርጥረው የሚመረመሩት አብዛኞቹ የመንግስት ባለስልጣናት ናቸው” የፌደራል ጠ/አቃቤ ህግ
መንግስት “በጥልቅ ተሃድሶው” ግምገማ የተለያዩ ጉድለቶች ተገኝቶባቸዋል በተባሉ መካከለኛና  ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ መውሰዱን የገለፀ ሲሆን ተቃዋሚ ፓርቲዎች “እርምጃው ግልፅነት ይጎድዋል፤ በሚፈለገው መጠንም አይደለም” ብለዋል፡፡
የትግራይና የአማራ ክልል መንግስታት በቅርቡ በአጠቃላይ ከ1380 በላይ መካከለኛና ከፍተኛ አመራሮችን ከስልጣን ማባረርና ዝቅ ባሉ መደቦች ላይ የመመደብ እርምጃዎች መውሰዳቸውን ያስታወቁ ሲሆን የኦሮሚያ ክልልና የደቡብ ክልል ግምገማዎች ሲጠናቀቁ ተመሳሳይ እርምጃዎች ይወሠዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የአማራ ክልል መንግስት 240 አመራሮችን በሙስና ጠርጥሮ የማጣራት ምርመራ እያካሄደ መሆኑን ገልጿል፡፡
የ‹‹ጥልቅ ተሃድሶው›› አካል ነው በተባለው እርምጃ ከሰሞኑ በአዲስ አበባ  በሙስና የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ያዋለ ሲሆን ተጠርጣሪዎችን የመመርመር ስልጣንን ከፀረ ሙስና ኮሚሽን የተረከበው የፌደራል ፖሊስ፤ በስም ያልተገለፁ የመንግስት ከፍተኛ ሹማምንትን ጨምሮ 130 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ እየመረመረ መሆኑን ገልጿል፡፡ ቀደም ሲል የአዲስ አበባ አስተዳደርም አመራሮችን ጨምሮ 125 ግለሰቦችን በተመሳሳይ የሙስና ወንጀል ጠርጥሮ እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ከነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የመንግስት ባለስልጣናት ናቸው ተብሏል፡፡
‹‹መንግስት አመራሩን መፈተሽ አለበት፤ ሙሰኞችን መቅጣት አለበት›› በማለት በተደጋጋሚ ያሳስቡ ከከረሙ ተቃዋሚዎች መካከል አንዳንዶቹ ሰሞኑን መንግስት በአመራሮቹ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ግልፅነት እንደሚጎድለው ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ስራ አስፈጻሚ አባልና የፓርቲው የጥናትና ምርምር ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ፤ ‹‹መንግስት በመገናኛ ብዙሃን እርምጃ መወሰዱን ሲገልፅ በእነማን ላይ እርምጃው እንደተወሰደ? እና በምን ጉዳይ የሚሉትን ጥያቄዎች እንድናነሳ የሚያስገድድ ግልፅነት የጎደለው እርምጃ ነው ብለዋል፡፡
“በሙስና የተጠረጠሩ አመራሮች ጉዳይ በግልፅ ለህዝብ መነገር አለበት” የሚሉት አቶ ዋሲሁን ይህ አይነቱ አካሄድ ህዝብ በሚፈልገው ልክ ከግምገማዎቹ ውጤት እንዳያገኝ ያደርገዋል›› ብለዋል አመራሮችን የማባረርና ከደረጃ ዝቅ የማድረግ እርምጃዎች ተወስደዋል የተባለውም ቢሆን ግልፅነት ይጎድለዋል ብለዋል አቶ ዋሲሁን። የመኢአድ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉጌታ አበበ በበኩላቸው፤ “እርምጃዎች የሚወሠዱት ዝም ብሎ እርምጃ እየወሰድን ነው ለማለት ከሆነ የሚፈለገውን ስር ነቀል ለውጥ ሊያመጡ አይችሉም፤ እርምጃው ሲወሰድም ህዝቡ በግልፅ ያጠፉትን ጥፋት እንዲገነዘብ ተዘርዝሮ ተገልፆ መሆን አለበት ይላሉ፡፡
እርምጃ መወሠዱ መልካም መሆኑን የገለፁት አቶ ሙሉጌታ ግን ግልፅነት የጎደለውና የመንግስትን ቁርጠኛ እርምጃም የማያሳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
‹‹መንግስት ግለሠቦችን ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ስርአቱንና አሰራሩን ገምግሞ እርምጃ መውሰድ ነበረበት፤ አሁን እየታየ ያለው ስርአቱን የመጠገን ሂደት ነው፤ ብለዋል፤ አቶ ሙሉጌታ፡፡
የመድረክ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የተከበሩ አቶ ገብሩ ገ/ማርያም  በበኩላቸው የእርምጃ አወሣሠዱ ለህዝብ ግልፅ ያልሆነ፣ በማን ላይ ምን እርምጃ ተወሰደ የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ ያልመለሰ በመሆኑ ተቀባይነቱ እምብዛም ነው ሲሉ ተችተዋል።
የእርምጃ አወሳሰዱ የታችኞቹን ብቻ ሳይሆን እስከ ላይኞቹ መድረስ እንዳለበት ገልፀው አጠቃላይ ግለሰቦች ላይ ከማነጣጠር ባለፈ የስርአትና የፖሊሲ ለውጦች ላይ ማተኮርም እንደሚገባ አቶ ገብሩ አስገንዝበዋል፡፡
የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እፈታለሁ በሚል አመራሮችን የማባረር፣ ከስልጣን ዝቅ የማድረግና የመሣሠሉ እርምጃዎች በተከታታይ ሲወሰዱ እንደ ነበር ያስታወሱት የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ) ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ ባለስልጣናትን ግልፅነት በሌለው መንገድ አንዴ መሾም ሌላ ጊዜ ማውረድ ተገቢ አይሆንም ብለዋል። ቁርጠኛ እርምጃ የሚባለው ይሄ ከሆነ ለመቀበል ያስቸግራል የሚሉት አቶ ተሻለ፤ አመራሮችን ዋስትና በማሳጣት በአግባቡ እንዳይሰሩ የሚያደርግና የተባረሩ አመራሮችን የሚያስኮርፍ ተግባር ነው ብለዋል፡፡ የህዝቡም ጥያቄ ባለስልጣናት ይባረሩ የሚል ሳይሆን ስርአቱ እንዲሻሻል የሚሉ እንደሆነ አቶ ተሻለ ጨምረው ገልፀዋል፡፡  በሙስና ተርጥረው በተያዙት ግለሰቦች ጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ፈንታው አምባው ከተጠርጣሪዎቹ አብዛኞቹ በመንግስት አመራር ላይ የነበሩ ግለሰቦች መሆናቸውን ጠቁመው በአሁኑ ወቅት ጉዳዩን ፖሊስ እየመረመረው መሆኑንና እስካሁን የምርመራ መዝገቡ ለአቃቤ ህግ አለመቅረቡን አስታውቀዋል፡፡
ማስረጃ የማሠባሠብና ማስረጃን የመመዘን ስራ ፖሊስና አቃቢ ህግ በጋራ እየሰሩ መሆኑንና መረጃዎች በሚገባ ከተጠናቀሩ በኋላ ለህዝብ ስለጉዳዩ በዝርዝር እንደሚገለፅ ተናግረዋል፡፡

Saturday, January 7, 2017

” የማይሰርቅ ባለስልጣን የተደበቀ አጀንዳ አለው። ” የሕወሓት ክቡር ሚኒስትሮች እና የገና በዓል ስጦታዎቻቸው ቆንጅት ስጦታው



” የማይሰርቅ ባለስልጣን የተደበቀ አጀንዳ አለው። ” የሕወሓት ክቡር ሚኒስትሮች እና የገና በዓል ስጦታዎቻቸው
#Ethiopia " የማይሰርቅ ባለስልጣን የተደበቀ አጀንዳ አለው። " የሕወሓት ክቡር ሚኒስትሮች እና የገና በዓል ስጦታዎቻቸው በበዓል ስጦታዎች ተንበሸበሽኩ፡፡ ......... ይኼንን የምታየውን ሙክት ,,,,,,,,,, ይኼንን ካርቶን ሙሉ ኮኛክና ውስኪ ........ ይኼንን 59 ኢንች ዘመናዊ ቲቪ ....... የአዲሱን ኒሳን ፓትሮል መኪና ቁልፍ  ....... ሰው ግን ለምንድነው ሌባ የሚሆነው፡፡. ..... አንዳንዱ ኑሮ አልሞላለት ሲለው ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ የመበልፀግ ትልቅ ራዕይ ስላለው ...........
#Ethiopia ” የማይሰርቅ ባለስልጣን የተደበቀ አጀንዳ አለው። ” የሕወሓት ክቡር ሚኒስትሮች እና የገና በዓል ስጦታዎቻቸው
በበዓል ስጦታዎች ተንበሸበሽኩ፡፡ ……… ይኼንን የምታየውን ሙክት ,,,,,,,,,, ይኼንን ካርቶን ሙሉ ኮኛክና ውስኪ …….. ይኼንን 59 ኢንች ዘመናዊ ቲቪ ……. የአዲሱን ኒሳን ፓትሮል መኪና ቁልፍ ……. ሰው ግን ለምንድነው ሌባ የሚሆነው፡፡. ….. አንዳንዱ ኑሮ አልሞላለት ሲለው ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ የመበልፀግ ትልቅ ራዕይ ስላለው ………..
[ክቡር ሚኒስትር ከአማካሪያቸው ጋር እያወሩ ነው]
  • ምንድነው እየሰማሁት ያለው?
  • ምን ሰሙ ክቡር ሚኒስትር?
  • በዓለም ዙሪያ ማለቴ ነው፡፡
  • ዶናልድ ትራምፕ ከሁለት ሳምንት በኋላ ሥልጣን ይጨብጣሉ፡፡
  • እሺ?
  • ባራክ አባማ ይሸኛሉ፡፡
  • እሺ?
  • ሌላ ደግሞ …
  • ሌላ ምን?
  • የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር በሙስና ተጠርጥረው በፖሊስ ተመረመሩ፡፡
  • ሙስና ስትል ምን ትዝ አለኝ መሰለህ?
  • ምን ትዝ አለዎት ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰው ግን ለምንድነው ሌባ የሚሆነው፡፡
  • ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡
  • ለምሳሌ?
  • አንዳንዱ ኑሮ አልሞላለት ሲለው ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ የመበልፀግ ትልቅ ራዕይ ስላለው ነው፡፡
  • ህም…
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • እኔ ግን ከአንተ ከንቱ ሐሳብ እለያለሁ፡፡
  • እስኪ ይንገሩኝ ክቡር ሚኒስትር?
  • ሙስና ውስጥ የሚገባው በሞራል መዝቀጥ ምክንያት ነው፡፡
  • አልገባኝም ክቡር ሚኒስትር?
  • የደሃ ኩሩ ሌብነትን ይፀየፋል፡፡
  • የሀብታም ኩሩስ ክቡር ሚኒስትር?
  • እሱ በሁለት ይከፈላል፡፡
  • በምንና በምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ሞራል ካለው ምልጃ አይፈልግም፣ አይልከሰከስም፡፡ ሞራል ከሌለው ግን ከደሃ ላይም ይቀማል፡፡
  • እኔ ግን ክቡር ሚኒስትር …
  • አንተ ምን?
  • ማለቴ አለ አይደል?
  • ምንድነው እሱ?
  • ይኼ ዘመን እኮ ያሳሳል፡፡
  • በምኑ?
  • ደልቃቃ ቪላ፣ ቅንጡ መኪና፣ ፀዳ ፀዳ ያሉ …
  • ማቴሪያሊስት ከሆንክ የሚያጓጓ ብዙ ነገር አለ፡፡
  • እርስዎ ምንድነዎት?
  • እኔ ነፍስና ሥጋዬን አመጣጥኜ ነው የምኖረው፡፡
  • እንዳይሰሙዎት?
  • እነ ማን?
  • በሀብት ላይ ሀብት የሚደረድሩት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ ህሊናዬን ነው የምፈራው፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ብዙዎች ወደኋላ የቀሩት ህሊና ህሊና ነው ሲሉ ይባላል እኮ፡፡
  • ይኼ የአንተና የቢጤዎችህ ወሬ ነው፡፡
  • ሀብት ያካበቱት ግን እንዲህ አይሉም፡፡
  • ሰማህ?
  • አቤት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይኼ ሁሉ ዳርዳርታህ ይገባኛል፡፡
  • ምንድነው እሱ ክቡር ሚኒስትር?
  • ህሊናዬን ትቼ ሌላ ነገር ውስጥ እንድገባ፡፡
  • እንዴት አወቁ ክቡር ሚኒስትር?
  • ዓይንህ ያሳብቃል፡፡
  • ምን እያለ?
  • ለምን አንሰርቅም እያለ ነዋ፡፡
  • እርስዎ መስረቅ ወይም ሌብነት ይላሉ እንጂ የተከበረ ስም አለው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ይባላል?
  • ቢዝነስ!
  • የትኛው ዲክሽነሪ ውስጥ ነው ያገኘኸው?
  • አራዶቹ ዲክሽነሪ ውስጥ፡፡
  • ሌብነት አራድነት ከሆነ ጨዋነት ምን ሊባል ነው?
  • በዚህ ዘመን ጨዋነት ራሱ አይታመንም፡፡
  • ለምን?
  • ምናልባት የተደበቀ አጀንዳ ይኖረዋል ተብሎ ይፈራል፡፡
  • ማነው የሚፈራው?
  • ጠንቃቆቹ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እነዚህን ጠንቃቆች ከማለት ሌላ ማለት ይቀላል፡፡
  • ጠንቃቆች ምን ይባሉ ክቡር ሚኒስትር?
  • ሴረኞች!
[ክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊያቸውን ጠርተዋት እየተነጋገሩ ነው]
  • ይኼ አማካሪዬ ከእነ ማን ጋር ነው የሚውለው?
  • በብዛት ጓደኞቹ ሀብታሞች ናቸው ይባላል፡፡
  • ከድሮ ጀምሮ ነው?
  • ኧረ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያፈራቸው ናቸው አሉ፡፡
  • አንቺ በምን አወቅሽ?
  • ወሬ ይደበቃል እንዴ ክቡር ሚኒስትር?
  • ማን ነገረሽ?
  • ክቡር ሚኒስትር ምንጩን አይጠይቁኝ፡፡
  • የሀብታሞች ጓደኛ ለመሆኑ ምን ማረጋገጫ አለሽ?
  • ምሳው ክትፎ እራቱ ጎልድ ሌብል እንደሆነ በስፋት ይወራለታል፡፡
  • ሀብታሞቹ ለምን ጓደኛ አደረጉት?
  • የወርቅ ማዕድን የሚባል ቅፅል ስም ስላለው፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • ሁሉ በእጁ ሁሉ በደጁ እንደሆነ ስለሚነገርለት ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የእኔ አማካሪ?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ስለሆነ?
  • የክቡር ሚኒስትሩ የተከበረ አማካሪ ስለሆነ ነዋ፡፡
  • ቢሆንስ?
  • ቁልፉ በእጁ ነው ይባልለታል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ የት ሄጄ?
  • እርስዎ አዲስ ስለሆኑ እሱ ነው የሚታወቀው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • በምንድነው የሚታወቀው?
  • ነገሮችን በማሳለጥ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ማሳለጥ?
  • አዎን ማሳለጥ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ማለት ነው?
  • ውሳኔዎችን ያስቀለብሳል፣ ለቢጤዎቹ በሚጠቅም መንገድ ያስወስናል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይኼንን እያደረገ ነው?
  • ከማድረግም በላይ ዕውቅና አግኝቶበታል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን የሚባል ዕውቅና?
  • የተከበሩ አማካሪ፡፡
  • አንቺም ታውቂያለሽ?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምን አልነገርሽኝም?
  • እርስዎ መቼ ጠየቁኝ?
  • ካልተጠየቅሽ አትናገሪም?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ልሳንሽ ይዘጋ፡፡
[ክቡር ሚኒስትሩ እየተበሰጫጩ ሾፌራቸው ወደ ቤት እየወሰዳቸው ነው]
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን ሆንኩ?
  • የተናደዱ ይመስላሉ፡፡
  • አንዳንዴ የሚያናድድ አይጠፋም እባክህ፡፡
  • እነዚህን ሁለት ሰዎች አጠገብዎ አስቀምጠው እንዴት አይናደዱ ክቡር ሚኒስትር?
  • ማንን?
  • አማካሪና ጸሐፊ ተብዬዎቹን ነዋ፡፡
  • ለምን እንዲህ አልክ?
  • ሁለቱ አንድ ላይ ሲገጥሙ አይቻሉም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ያደርጋሉ?
  • የጥቅም ተጋሪ ናቸው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አሁን ግን የተጣሉ ይመስላሉ እኮ?
  • የጥቅም ግጭት ሲፈጠር እርስ በርስ ይያያዛሉ፡፡
  • ከዚያስ?
  • አንዳቸው ሌላቸውን ማማት ነው ሥራቸው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አሁን ተጣልተዋል ማለት ነው?
  • ዞረው መግጠማቸው አይቀርም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እኔ ከጸሐፊዋ እንደሰማሁት አይመስለኝም፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር ጥቅም ያፋቅራል፣ ጥቅም ያጋጫል ሲባል አልሰሙም?
  • ይኼንን ሁሉ ጉድ ሰምቼ ሊታረቁ?
  • እነሱ ቆዳቸው ወፍራም ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ሁለቱንማ እለያየለሁ፡፡
  • አንዳቸው ለአንዳቸው ይቅርታ ይጠይቁዎታል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ይኼን ያህል ምን ስለሆኑ?
  • ስለሸጡት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምንድነው የሸጡት?
  • ህሊናቸውን፡፡
[ክቡር ሚኒስትር ቤት ሲገቡ ባለቤታቸው ከደጅ በፈገግታ ተቀበሉዋቸው]
  • ምን ተገኘ እባክሽ እንዲህ በፈገግታ የተሞላሽው?
  • ደስ ሲለኝስ?
  • ይኼን ያህል?
  • አዎን ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ንገሪኝ እባክሽ?
  • በዓል ደርሷል አይደል?
  • አዎን፡፡
  • ከወጪ ተገላገልኩ በዚያ ላይ …
  • ምን አግኝተሽ?
  • ስጦታ፡፡
  • የምን ስጦታ?
  • በበዓል ስጦታዎች ተንበሸበሽኩ፡፡
  • ማን ሰጠሽ?
  • ማን ምን እንደላከልኝ ላሳይህ፡፡
  • እንዴ ይኼ ሁሉ ምንድነው?
  • ይኼንን የምታየውን ሙክት የላከልኝ አማካሪህ ራሱ ነው፡፡
  • ምን?
  • ይኼንን ካርቶን ሙሉ ኮኛክና ውስኪ የላከልኝ የአማካሪህ ጓደኛ ነው፡፡
  • እንዴ?
  • ይኼንን 59 ኢንች ዘመናዊ ቲቪ የላከልኝ ሌላው የአማካሪህ ጓደኛ ነው፡፡
  • ኧረረረ …
  • ይኼንን ደግሞ …
  • ይኼንን ምን?
  • ተመልከተዋ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የቁልፍ መያዣ ይመስላል፡፡
  • ተሳስተሃል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምንድነው እሱ?
  • የአዲሱን ኒሳን ፓትሮል መኪና ቁልፍ የላከው ደግሞ የተከበረው አማካሪ ምርጥ ጓደኛ ነው፡፡
  • ምን አልሽ አንቺ?
  • መልካም የገና በዓል

Friday, January 6, 2017

የስብሓት ነጋ ኣዲስ ነጠላ ዜማ – በነስየና ገብሩ የሰራሁት ደባና ተንኮል ከውስጤ ፀፅቶኛልና ይቅርታ ይደረግልኝ ቆንጅት ስጦታው



“ቆጨኝ” + “ይቅርታ” !
÷÷÷÷÷÷÷÷÷
* “ይቅርታ 1993 ዓ/ም በነስየና ገብሩ የሰራሁት ደባና ተንኮል ከውስጤ ፀፅቶኛልና ይቅርታ ይደረግልኝ”
!
!
!
!

* “ከስየ፣ ገብሩ፣ ኣውዓሎምና ኣረጋሽ ጀግንነት የመለስ ምላስ መተማመኔ ቆጨኝ” !
!
!
የስብሓት ነጋ ኣዲስ ነጠላ ዜማ)
* “…ስብሓት ነጋ የ1993 ዓ/ም በህወሓት ያጋጠመው ክፍፍል ማስቆም ነበረብኝ። ኣንዳዶቹ ኣጋጣሚው ለስልጣን ተጠቅመውበታል(መለስ)። ሁለቱም ወደ ኣንድ መምጣት ኣለባቸው።
መለስን ባልሰማ ኖሮ በ1997ና ዘንድሮ 2008/2009 ዓጋጥሞ ያለው ፖለቲካዊ ችግር ባላጋጠመ ነበር።…”
ኣቶ ስብሓት ለኣዲስ ዘመን ጋዜጣ የሰጡት ቃል መጠይቅ።
“…ይቅርታና … ቆጨኝ…” እያሉ ነው።
የጀግኖቻችን ተግባር፣ ብስለት፣ ስብእና የሃገር ፍቅር ከመለስ ምላስ በእጅጉ እንደሚበልጥ እናውቃለን

እስኪ ሰከን እንበል – #የመደማመጥ_ቀናነት ቡድን። ቆንጅት ስጦታው



እስኪ ሰከን እንበል ———–#የመደማመጥ_ቀናነት ቡድን። ————- ግን እንደኛ አገርና ህዝብ አስፈሪ የህልውና አደጋ ላይ ያለ ይኖራል? እንደኛስ መላቅጡ የጠፋበት ህዝብ ይኖራል። 100 ሚሊዮን ህዝብ፣ 100 ቁዋንቁዋ፣100 የፖለቲካ ድርጅት ፣ 100 ብሄረሰብ ፤ በኢትዮጵያ የአየር ፀባይ፣ በኢትዮጵያ መልክአ ምድር፣ በኛ ጎረቤቶች፣ በኛ መንግስት፣ በኛ ድርቅና እና ራስ ወዳድነት! እስኪ አስቡት ጎበዝ ሳት ብሎን ጦርነት ውስጥ ብንገባ ምን ሊፈጠር እንደሚችል።
ተመድ፣ አአድ ገሌ መሌ ጭው ባለ ሜዳ አንድ ቁዋንዋ አንድ ሀይማኖት ላለው አገር እንኳ ምንም እንዳልፈየደ እያየን! አንድስ የሚያክል ጠላት አስቀምጠን የጠላት ያለህ፣ ጠላት አውርድ የምንል ምን ክነቶን ይሆን። ባለፉት አስርታት የወረደብን መአት እንኳን ለኛ ለአለም ትምህርት አይሆንምን? የ25 እና 40 አመት ሰቆቃና ስቃይ ያላስተማረን ምን ሊያስተምረን ነው? ምን ስንሆን ይሆን ባንክሮ ናማሰብ ማስተዋል የምንጀምረው? ወያኔን እንላለን እንጂ እኛው እራሳችን ነን ሀገራችንን በልተን እየጨረስናት ያለው። ወያኔስ ኢትዮጲያን ማጥፋት ስራው ነው። የኛስ ምን ይሉታል።
ወያኔን በርግጥ እንጠላለን። ግን ወያኔን የምንጠላበትን ድርጊት ላለማድረጋችን ምን ማረጋገጫ አለን? በየርከኑ ስንነሰነስና ስንበጣጠስ ስንት ትንንሽ ልንሆን እንደሆነ አስተውለነዋል? ተበጣጥሰን ተሰነጣጥቀንስ አማን ውለን አማን እንደማናድርስ ነጋሪ ያስፈልገናል? እኛ እኮ እስከየሩሳሌም ግዛታችን ነው ብለው የሚያልሙ አባቶች ልጆች ነን። እኛ እኮ ለአለም ጥቁሮች ሁሉ የነፃነትን ቀንዲል የለኮሱ አርበኞች ልጆች ነን። ሌሎች ከኛ ሊማሩ እንጂ ይሳለቁ ዘንድ እንዴት እንፍቀድ! አረ ተዉ ጎበዝ! አረ በባንዲራው! እኛ ስንጎማመድ እኮ የምትጎመደው ይች ምስኪን አገር ነች። ይረከቡት የሚያጡት እኮ ልጆቻችን ናቸው።
አረ በልጆቻችን! የኛ መጠላለፍ የጠላታችንን ክንድ እያፈረጠመው ነውና ወደ ልቦናችን እንመለስ። ሰከን፣ በሰል እንበል። ቅንነት ካለ ሁሉም ይቻላል። ወደ ጎን የሰበቅነውን ሰይፍ ወደ ጠላት እንቀስረው። ለህዝባችን ስንል ትንሽ ዝቅ እንበል። ዝቅ ያለን ሁሉ አንድየ ከፍ ያደርገዋል። ይሄንን የማህበራዊ መገናኛ አሳፋሪ ጦርነት ዛሬውኑ አቁመን ትግላችን ላይ እናተኩር። አገራችን አታልቅስብን። ወገናችን አይዘንብን፣ ልጆቻችን አይፈሩብን። ጠላታችንም አይሳለቅብን። የኢትዮጵያ መፃኢ እጣ ፈንታ በእጃችን ነው። ቅን ከሆንን እግዚአብሄርም ያግዘናል።
#የመደማመጥ_ቀናነት ቡድን።
#የመደማመጥ_ቀናነት ቡድን።

Thursday, January 5, 2017

በአየር ኃይል አብራሪዎችና ቴክኒሺያኖች ላይ እርምጃ መወሰድ ተጀመረ By posted by ብርሃኑ አየለ




በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች እና በቴክኒክሺያኖች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው።ገዢው ፓርቲ በኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ምድቦች ውስጥ በአካሄደው ግምገማ ከተቃውሞው ጋር በተያያዘ ግንኙነት አላቸው ተብሎ በሚጠረጠሩ አባላት ላይ ከእስር እስከ ሥራ ማገድ እርምጃ እየወሰደ ነው።
በምስራቅ አየር ምድብ በተዋጊ ሄሊኮፕተር በረዳት አብራሪነት ተመድቦ የሚገኘው የመቶ አለቃ ገመቹ ሀሰን ከግምገማ በኋላ ከአየር አብራሪነት የታገደ ሲሆን የግምገማው መሪ የነበረው የአየር ኃይል ም/አዛዥ እና የዘመቻ ሀላፊ ብርጋዴር ጄኔራል ማአሾ ሀጎስ ስሙን በመጥቀስ በረራ እንድታቆም የተደረገበትን ምክንያት ታውቃለህ ብሎ ሲጠይቀው መቶ አለቃም ገመቹም በንዴት አዎ አውቀዋለሁ የታገድኩበት ገመቹ ስለሆንኩ ነው ብሎ ምላሽ ሰጥቷል። ይህን ተከትሎ አብራሪው በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ ከስራው ታግዶ ይገኛል።
በሌላ በኩል በምእራብ አየር ምድብ በተደረገው ግምገማ የሚግ 23 ጄትአብራሪ የሆነው የመቶ አለቃ መስራች እንዳለ በአማራ ክልል እየተካሄደ ከአለው ሕዝባዊ ተቃውሞ ጋር ግንኙነት አለህ በማለት እርምጃ ሊወሰድበት እንደሆነ ከአየር ኃይል ምንጮቻችን ገልፀዋል። መቶ አለቃ መስራች እንዳለ ላይ ስለሚወሰድበት እርምጃ ከፍተኛ የኃይል አዛዦች እየመከሩበት የሚገኙ ሲሆን እስከ አሁን ባገኘነው መረጃ መሰረት ውሳኔ እንዳልተሰጠበት ታውቋል።
ከዚህ በፊት ከማእከላዊ አየር ምድብ ተይዘዉ የታሰሩት 3 አብራሪዎች ከ2 አመት በላይ ተፈርዶባቸዉ ናዘሬት እስርቤት ይገኛሉ። በማዕከላዊ አየር ምድብ በተደረገ ግምገማ ላይ የአየር ሃይል አባላት ስለታሰሩት አብራሪዎች በማንሳት “እነሱ ያለጥፋታቸዉ ነዉ የታሰሩት፤ አየር ሃይሉ ያለምንም ምክንያት ሰዎችን እያሰረና እያባረረ ተቋሙን እየጎዳ ነዉ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ አመራሮቹ ማስተካከል አለባቸዉ” በማለት አባላቱ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በአየር ሀይል አብራሪዎችና በስርአቱ ከፍተኛ የጦር አዛዦች መካከል ከፍተኛ የሆነ አለመግባባት እንዳለ ከአየር ሃይል ያሉ ምንጮቻችን ገልጸዋል። የአየር ሃይል አብራሪዎች ባለው የስራ ብልሹነት ምክንያት ስራዎች እየተስተጓጎሉ ነው በማለት ቅሬታቸውን ይገልጻሉ። ለስርአቱ ታማኝ ደጋፊዎች የሚባሉት አብራሪዎች ጥፋት ቢሰሩም እንኳን ተጠያቂዎች አይደረጉም።
በምስራቅ አየር ምድብ ማዘዣ በሆነው ድሬዳዋ አየር ሃይል ሶሰት ሄሊኮፕተሮችን በመግጨት ከባድ ኪሳራ በተቋሙ ላይ ያደረሰዉ ሌ/ኮ ፀጋ ዝአብ ካሳ የተባለ የሄሊኮፍተር አብራሪ በአሁኑ ሰአት ምንም እርምጃ ሳይወሰድበት በስራው ላይ ይገኛል። ተቋሙ እንደዚህ እይነት ከባድ ኪሳራ ባደረሱት አካላት ላይ እርምጃ ሳይወስድ በሌሎች አብራሪዎች ላይ አላግባብ የሚወሰዱ እርምጃዎች በአየር ሃይል አባላት ላይ ከፍተኛ የሆነ ቅሬታን እያስነሳ ነው።
ለአገዛዙ ታማኝ አይደሉም ተብለው በሚጠረጠሩ የአየር ሃይል አብራሪዎች ላይም ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑን ምንጮቻችን ገልጸዋል።

የወያኔ ተልዕኮ አማራን የማጥፋት ዘመቻ = መምህር አሸናፊ ሸዋርካብን በባህር ዳር ማረሚያ ቤት ውስጥ እረሽነውታል፡፡ቆንጅት ስጦታው



የባህር ዳር ማረሚያ ቤት እና የወያኔ ተልዕኮ አማራን የማጥፋት ዘመቻ
በአማራዋ ፈርጥ ከተማ ባህር ዳር ሀዘን ፣ጩኸት ፣ለቅሶ ፣ሽብር ፣ሁከት በፀረ አማራው ቡድን ወያኔ የዕለት ከዕለት ጉዳይ ከሆነ አመታትን አስቆጥራልች፡፡የአማራን ህዝብ ለማጥፋት እና ለማዳከም ጠላቴ ነው ብሎ በፕሮግራም ነድፎ በ1968 ዓ.ም የተነሳው ወያኔ አማራ የሆኑና በአማራነታቸው ፅኑ አቋም ያላቸውን የአማራ ልጆች ቤት ለቤትና በአደባባይ ካለምንም ምክንያት መረሸኑ ሳያንሰው ካለው ፍርሃትና ጭንቀት የተነሳ በቁጥጥር ስር አድርጎ በማረሚያ ቤት የፍርድ እስረኛ ያደረጋቸውን የአማራ ልጆችንም ኢ-ሰብዓዊ በሆነ መልኩ እየረሸነ ጭራቃዊ ተልዕኮኑን እየፈፀመ ይገኛል፡፡
በታህሳስ 24፦2009 ዓ.ም መምህር አሸናፊ ሸዋርካብን በባህር ዳር ማረሚያ ቤት ውስጥ እረሽነውታል፡፡
መምህር አሸናፊ ሸዋርካብ በታሪክ ትምህርት የሁለተኛ ድግሪ የነበረው ሲሆን ሟች ወንድማችን በጎጃም ክፍለ ሃገር በአገው ምድር አውራጃ በአዲስ ቅዳም ከተማ መሰናዶ ት/ቤት የታሪክ መምህር ሲሆን ትግሁ እና ሀገር ወዳጅ የሆነ በተማሪዎቹና የስራ ባልደረባዎቹ ዘንድ ተወዳጅ አስተማሪ ነበር፡፡አሸናፊ ሀገሩን ወዳድና በተለይ ወያኔ በአማራው ላይ የሚያደርሰውን ግድያ ፣ማፈናቀል፣ዘረፋ እና ሰብዓዊ ጥሰትን አጠንክሮ ይቃወምና በአማራነቱን በፅኑ የነበረ ጀግና ነው፡፡አሸናፊ ሀገር ውስጥ የነበረው ትግል ያስቸግረው ስለነበር ሀገር ውስጥ የነበረው አደረጃጀት ከጨረሰ በኋላ ወደ ትጥቅ ትግሉ ለመቀላቀል ወሰነ፤ከእዚያም በሀምሌ ወር 2007 ዓ.ም ወደ አማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ(አዴሃን) ለመቀላቀል መንገዱን ወደ በረሃ አደረገ፡፡ነገር ግን ሁሉም ነገር እንደጠበቀው ሳይሆን ቀረና አብሮኝ ይሞታል የትግል አጋሬ ነው ብሎ ያስከተለው አቶ ፍቃዱ አጥናፍ ብርሃኑ የተባለ የወያኔ ሰላይ አብሮት በመከተል ሁመራ ላይ ለወያኔ ደህንነቶች ሊያሲዘው ችሏል፡፡ፍቃዱ አጥናፍም ተልዕኮውን በወገኑ አሸናፊ ላይ ከፈፀመ በኋላ በወያኔ ትልቅ ምስጋና ተችሮት በአገው ምድር አውራጃ በአንከሻ ወረዳ ግምጃ ቤት ከተማ ገንዘብና ፕላን ፅህፈት ቤት ውስጥ ሹመት ተቀብሏል፡፡
አሸናፊ ሸዋርካብ አማራነቱ ሚያንገበግበው እና ሚሳሳለት ማንነቱ እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ ያረጋግጥ ነበር፤ይህም በጠላት ምርመራ ወቅት የሰሜን ምዕራብ ቀጠና የፀረ ሽብር ግብረ ሃይል ወንጀል መርማሪ በሆነው ባንዳ በትውልዱ አማራ በኢንስፔክተር አብረሃም ታምራት ከፍተኛ ኢ-ሰብዓዊና አካላዊ ጉዳት ቢደርስበትም ጀግናው እና ኩሩው መምህር አሸናፊ ሸዋርካብ በአማራነቱ ምንም ሳያፈገፍግ እስከ ዕለተ ሞቱ ተጋፍጧል፡፡ወያኔ በአሸናፊ ላይ የአምስት(5) አመት የእስራት ቅጣት በይኖበት የነበረ ቢሆንም አማራን በማሰር ብቻ የማይረካው ወያኔ በቀን 24 ፡04፦2009 ዓ.ም አሸናፊን ከማረሚያ ቤት ውስጥ ገድሎታል፡፡
የቀብር ስነ ስርዓቱም በደቡብ ጎንደር አዲስ ዘመን በቀን 25፡04፥2009 ዓ.ም ተፈፅሟል፡፡
ለሟች በቤተሰቦችና ወዳጆች መፅናናትን እየተመኘን አዴሃንም ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶታል፡፡ድርጅታችን አሸናፊ የሰዋለትን አላማ አማራን ከጥፋት በማዳን ዳር እናደርሳለን፡፡

የአማራ ህዝብ በቆራጥ ልጆቹ ማንነቱን ያስከብራል!!

Wednesday, January 4, 2017

የመንግስት የውጭ እዳ፣ ከ 2 ቢ.ዶላር ወደ 22 ቢ.ዶላር (በአስር ዓመት Written by  ዮሃንስ ሰ.



#Ethiopia የመንግስት የውጭ እዳ፣ ከ 2 ቢ.ዶላር ወደ 22 ቢ.ዶላር (በአስር ዓመት)
ብድሩ፣ ለትምህርት…የሚውል ነው።ግን፣ ጨርሶ አንድ ቃል ማንበብ የማይችሉ ተማሪዎች በዝተዋል። ………. የወለድ ክፍያው፣ በአመት 350 ሚሊዮን ዶላር ሆኗል።
Written by  ዮሃንስ ሰ.
• አምና የውጭ እዳ ለመመለስ፣ 1 ቢሊዮን ዶላር ተከፍሏል።
• የወለድ ክፍያው፣ በአመት 350 ሚሊዮን ዶላር ሆኗል።
• አዎ፣ ብድሩ፣ ለትምህርት፣ ‘ለመሰረተ ልማት’ የሚውል ነው።
• ግን፣ ጨርሶ አንድ ቃል ማንበብ የማይችሉ ተማሪዎች በዝተዋል።
ይሄ ነገር፣ እንዴት ቢገለፅ ይሻላል? የእዳውና የወለዱ ሸክምኮ፣ “በደብል ዲጂት” ሽቅብ እየመጠቀ ነው። ሸክሙ፣ ምንኛ ከባድ እንደሆነ፣ በውል ለመገንዘብና በደንብ ለመግባባት፣ ሁነኛ ዘዴ ያስፈልገናል። በምስል እያየን ለማገናዘብ እንሞክር? ወይስ በፅሁፍ… በቃላት ቢገለፅ ይሻላል?
“በምስል ወይስ በቃላት” እያልን የምናማርጠው፣ ለመቀናጣት እንዳልሆነ ይገባችኋል። እንዲያውም፣ ከጭንቀት የመነጨ ይመስላል። በእርግጥም፣ ጉዳዩ፣ የሚያሳስብ ወይም የሚያስጨንቅ ስለሆነ፣ አስተማማኝ የመግባቢያ ዘዴ ለመምረጥ ብንሞክር አይገርምም።
ይሄንን፣ እንደ ቀላል ነገር አትቁጠሩት። ስለ እዳውና ስለ ወለዱ አይደለም የማወራው። በምስል እና በቃላት አማካኝነት… መረጃዎችን የማገናዘብና የመግባባት ችሎታ፣ ቀላል ብቃት አይደለም። በየእለቱ ፅሁፍ እናነባለን – መልእክቱም ይገባናል። ‘ግራፍ’ አይተን፣ የትኛው እንደቀነሰና እንደጨመረ ወይም የትኛው እንደበለጠና ስንት እንደደረሰ እንገነዘባለን።
በአግባቡ እስከተገለፀ ድረስ፣ በፅሁፍና በመስል መግባባት፣ ብዙም አያስቸግረንም። ለሰላምታ የመነጋገር ያህል ነው። ወይም ደግሞ፣ በሁለት እግር የመራመድ ያህል፣… ገና ስንወለድ፣ አብሮን የተፈጠረ “ነባር ችሎታ” ይመስለናል። ግን አይደለም። ለነገሩማ፣ መራመድም፣ “ነባር ችሎታ” አይደለም። በፅሁፍና ‘በግራፍ’ መግባባትማ… በብዙ ቢሊዮን ዶላርም፣ ተፈልጎ የማይገኝ እየሆነብን ነው። እንዴት? ማንበብና ማባዛት የማይችሉ ተማሪዎች ተበራክተዋል። እና፣ እንዴት ነው፣ “ተማሪዎች” ብለን ልንጠራቸው የምንደፍረው? በየእለቱ፣ ክፍል ውስጥ የምንሰጣቸው ነገርስ፣ እንዴት “ትምህርት” ተብሎ ይጠራል? ማናናቄ አይደለም። ብዙ ገንዘብ የፈሰሰበት፣ ብዙዎች የደከሙበት ጉዳይ እንደሆነ እየካድኩ አይደለም።
ከመንግስት በጀት ውስጥኮ፣ ሩቡ ያህል፣ ለትምህርት ነው የሚመደበው። ‘የትምህርት ጥራትን እናሻሽላለን’ ብለው፣ በብድርና በእርዳታ፣ ላይ-ታች የተሯሯጡ የውጭ መንግስታትና አለማቀፍ ተቋማትም ብዙ ናቸው (አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ጃፓን… የአለም ባንክ፣ ዩኔስኮ፣ ዩኒሴፍ፣ ሴቭ ዘ ቺልድረን… በጣም ብዙ ናቸው)። ለዚያውም፣ ለብዙ ዓመታት ነው የተሯሯጡት – ለአስርና ከዚያ በላይ ዓመታት።
ግን፣… ዛሬም ድረስ፣ የትምህርት ጥራት፣… ገና ‘ጠብ’ አላለም። ይሄ፣ “በይመስለኛል” የተነገረ መርዶ አይደለም። የቆዩና ያረጁ መረጃዎችን ብቻ በመያዝ የተነገረ ድምዳሜም አይደለም።
ከአዳዲስና ሰፋፊ ጥናቶች የተገኘ መረጃ ነው።
በትምህርት ሚኒስቴር ፈቃድና በዩኒሴፍ መሪነት፣ በአለማቀፍ የምርምር ተቋማት አማካኝት፣ በ297 ትምህርት ቤቶች የተካሄደውን ጥናት መጥቀስ ይቻላል። ቀለል ተደርጎ የተሰራ ‘ግራፍ’፣ ለአብዛኞቹ ተማሪዎች፣ ትልቅ ‘እንቆቅልሽ’ እንደሚሆንባቸው ሪፖርቱ ይገልፃል።
ለምሳሌ፣ “የወለድ ክፍያን ለማሳየት የተዘጋጀውን ግራፍ ተመልከቱ። በ2007 ዓም፣ የኢትዮጵያ መንግስት፣ ስንት ሚሊዮን ዶላር የብድር ወለድ እንደከፈለ ግለፁ” የሚል ጥያቄ፣ በእጅጉ ይከብዳቸዋል – ለአራተኛ ክፍል ተማሪዎች።
“255 ነዋ። ማለትም 255 ሚሊዮን ዶላር” ብለው በቀላሉ መመለስ አይችሉም። ከዚህ የቀለለ ጥያቄ ቀርቦላቸው፣ በትክክል መመለስ የቻሉ የአራተኛ ክፍል ተማሪዎች፣ 23% ብቻ ናቸው። ከመቶ ተማሪዎች መካከል፣ 23ቱ ብቻ።
“ይሄማ መራቀቅ ነው” ልትሉ ትችላላችሁ። ፈፅሞ አይደለም። ግን ይሁን። የማንበብ ችሎታም እንደሰማይ ሩቅ እየሆነ ነው።
በእንግሊዝ መንግስት እርዳታ ተጀምሮ፣ የኔዘርላንድና የአየርላንድ መንግስታትም ድጋፍ ተጨምሮበት፣ ለአስር ዓመታት በስፋት የተካሄው ‘ያንግ ላይቭዝ’ ጥናት፣ አዳዲስ መረጃዎችን ይዞ መጥቷል። አዲሱ መረጃ፣ የ12 ዓመት ልጆች ላይ ያተኮረ ነው። ልጆቹ… ግማሽ ያህሉ፣ 6ኛ ክፍል ደርሰዋል። ሌሎቹ ደግሞ፣ በአብዛኛው ከ3ኛ እስከ 5ኛ ክፍል ላይ ናቸው።
ጥሩ። ግን፣ የማንበብ ችሎታቸው እንዴት ነው?
ከመቶ ልጆች መካከል 35ቱ፣ አንዲት ዓረፍተነገር እንኳ ማንበብ አይችሉም (በየትኛውም ቋንቋ)።
የሂሳብ ችሎታቸውስ? ለምሳሌ የማባዛት ችሎታቸው እንዴት ነው? ለልጆቹ የቀረበላቸው የማባዛት ጥያቄ ቀላል ነው። 2 x 4 ስንት ይሆናል?
ከመቶ ተማሪዎች መካከል፣ 30ዎቹ ጥያቄውን በትክክል መመለስ አልቻሉም። አትርሱ። የ12 ዓመት ልጆች ናቸው። አብዛኞቹም፣ ከሦስተኛ እስከ ስድስተኛ ክፍል የደረሱ። ግን፣ ሲሶዎቹ፣ ገና… ማባዛት አይችሉም።
ሌላ አዲስ ጥናትም አለ – በአሜሪካ መንግስት እርዳታ አምና የተካሄደ ጥናት። የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎችን ተመልከቱ።
ከመቶ ተማሪዎች መካከል 20ዎቹ፣ ፈፅሞ አንዲትንም ቃል ማንበብ አይችሉም።
ከመቶ ተማሪዎች መካከል፣ ዓረፍተነገር አንብበው መረዳት የሚችሉት ከሃያ ያንሳሉ። 80 ከመቶ ተማሪዎች፣ አንብበው መረዳት አይችሉም።
ይሄ ትልቅ ችግር ነው – ከእዳና ከወለድ ሸክም በእጅጉ የሚበልጥ፣ የሚያሳስብና የሚያስጨንቅ ችግር!
ግን፣ ከዚህም የባሰ ችግር አለ።
የፖለቲካ ቁማር ይበልጥብናል
አብዛኞቹ የሦስተኛ ክፍል ተማሪዎች፣ አንዲት ዓረፍተነገር አንብበው መረዳት እንደማይችሉ አየን። 2 ሲባዛ በ4 ስንት እንደሚሆን ማስላት የማይችሉ ተማሪዎችን ተመለከትንም። እንዲህ አይነት አሳሳቢ ችግር የተጋረጠበት ሰው፣ ምን ማድረግ አለበት?
ለጤናማ አስተሳሰብ፣ ክብር ያለው ሰው፣… ከምር ጉዳዩ አሳስቦት፣ “የዚህ ችግር መንስኤ ምንድነው? ከምን ጋር የተያያዘ ነው? ጊዜያዊና ዘላቂ መፍትሄዎቹስ ምንድናቸው?” ብሎ ይመረምራል።
አብዛኞቻችን ግን፣ ያን ያህልም፣ ከምር አያሳስበንም። “የችግሩ መንስኤና መፍትሄ”… ምናምን… ብሎ ማሰብ፣ ሞኝነት የመስለናል። ያው፣ እንደተለመደው፣ ከሁሉም በፊት፣ “የፖለቲካ ጨዋታ” ይቀድምብናል – ጎራ ለይተን ‘ቲፎዞ’ ለመሆን። በቃ፣ ‘ጌም’ ነው።
አንዳንዶቹ፣ የገዢው ፓርቲ ጭፍን ደጋፊ በመሆን፣ ትምህርት ምንኛ እጥፍ ድርብ እንደተስፋፋ፣ ትምህርት ቤቶች እንደተበራከቱ፣ ‘የሚሊዬኔም ግቦች’ እንደተሳኩ… እለት በእለት በመዘርዘር፣ ነገሩን ዋና የፖለቲካ መቆራቆሻ ያደርጉታል።
ገሚሶቹም፣ በጭፍን ተቃዋሚነት፣ መንግስትን ለማብጠልጠል፣ ትልቅ አዳፍኔ መሳሪያ አገኘን ብለው፣ የውግዘት ውርጅብኝ ለማዝነብ ይሽቀዳደማሉ። እንዲያውም፣ ሁሉም ተማሪ፣ ማንበብና መደመር የማይችልበት ጨለማ እንዲፈጠር እስከመመኘትም ይደርሳሉ – መንግስትን ይበልጥ ለማውገዝ።
ታዲያ ከሁሉም የከፋው ችግር፣ እንዲህ አይነት የጭፍንነት ችግር አይደለም ትላላችሁ?
እና ምን ተሻለ?
ከጭፍን የድጋፍና የተቃውሞ ስካር ተገላግለን፣ የችግሮቻችንን መንስኤዎች ለማጥናትና መፍትሄ ለመፈለግ፣ በጊዜ ብንጣጣር ይሻላል።
አለበለዚያኮ፣ ጉዟችን ወደ ጨለማ ነው የሚሆነው። አንብቦ መረዳትና የሂሳብ ስሌት የማይችሉ የሦስተኛና የአራተኛ ክፍል ተማሪዎች እየተበራከቱ እያየን፣ ለፖለቲካ ጨዋታ መሽቀዳደም ሞኝነት ነው።
በበኩሌ፣ ስለመንስኤውና ስለመፍትሄው፣ ለመወያያ የሚሆኑ መረጃዎችንና የቁምነገር ሃሳቦችን ይዤ እመጣለሁ።
ለዛሬ ግን፣
በአንድ በኩል፣ በፅሁፍና በምስል፣ በቃላትና በ’ግራፍ’፣ መረጃዎችን የመግለፅና የማገናዘብ ችሎታን ቀለል አድርገን እንዳናይ ለማስታወስ በመመኘት፣…
በሌላ በኩል ደግሞ፣ የውጭ እዳና ወለድ፣ ራሱን የቻለ ትልቅ ችግር እንደሆነ እንድንገነዘብና መፍትሄ እንድናበጅለት አስቤ፣ በምስል ያዘጋጀኋቸውን መረጃዎች ተመልከቱልኝ።
መረጃዎቹ፣ ባለፈው ሳምንት በገንዘብ ሚኒስቴር ከተሰራጨው የብድር መረጃዎች ሪፖርት በመነሳት ያሰባሰብኳቸው ናቸው – የበርካታ አመታት ሪፖርቶችን በማሰስ።
መቼም፣ በምስል አጠናቅሬ ያቀረብኳቸውን መረጃዎች፣ በፅሁፍ አልደግምባችሁም። ግን… አንድ ሁለቱን ብቻ ልድገማቸው።
እዳ ለመክፈል የሚውለው የውጭ ምንዛሬ፣ በሦስት ዓመት ልዩነት በእጥፍ ጨምሮ፣ 1 ቢሊዮን ዶላር መድረሱና ከዚያም ማለፉ፣ ለአገሪቱ ትልቅ ፈተና ነው። በተለይ ደግሞ፣ የኤክስፖርት ንግድ እያደገ አለመሆኑ፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ያባብሳል።
በእርግጥ፣ እስካሁን፣ ከፍተኛ ቀውስ አልተፈጠረም – በሁለት ምክንያቶች።
አንደኛ፣ በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ባለፉት ሁለት ዓመታት ቀንሷል። በዚህም ምክንያት፣ ለነዳጅ ግዢ የሚውለው የውጭ ምንዛሬ በግማሽ ቀንሷል። 1.2 ቢሊዮን ዶላር ዳነ ማለት ነው። ለዚያምኮ፣ ተገዝቶ የሚመጣው ነዳጅ አልቀነሰም። እንዲያውም ጨምሯል። ከ2005 ዓ.ም ጋር ሲነፃፀር፣ አምና ተገዝቶ የመጣው የነዳጅ መጠን በእጥፍ ይበልጣል። በዋጋ ግን ያንሳል። ይህም፣ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ፣ ክፉኛ ከመቃወስ እንድንተርፍ አግዞናል – እስካሁን።
ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ቀውስ እንዳይፈጠር የረዳን ሁለተኛ ነገር፣ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ለቤተሰብ የሚልኩት ዶላር መጨመሩ ነው። ከ2003 ወዲህ በእጥፍ ስለጨመረ፣ አምና ወደ አራት ቢሊዮን ዶላር ተጠግቷል።

አዲስ አበባ “በአዲሱ ማስተር ፕላን ወደ ጎን መለጠጧን አቁማ ወደ ላይ ከፍ ማለት ትጀምራለች” ኮሚሽኑ ቆንጅት ስጦታው



አዲስ አበባ "በአዲሱ ማስተር ፕላን ወደ ጎን መለጠጧን አቁማ ወደ ላይ ከፍ ማለት ትጀምራለች" ኮሚሽኑ
በ1994 ዓ.ም ተግባራዊ መደረግ የጀመረው ዘጠነኛው ማስተር ፕላን በ2006 ዓ.ም የመጠቀሚያ ጊዜው አብቅቷል፡፡ አሥረኛው ማስተር ፕላን ከኦሮሚያ ልዩ ዞን ጋር አቀናጅቶ ለማካሄድ በርካታ ሥራዎች የተሠሩ ቢሆንም፣ ከኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ በመቅረቡ እንዲቀር ተደርጓል፡፡ በዚህ ምክንያት ባለፉት አራት ዓመታት አዲስ አበባ ይፋ ማስተር ፕላን ሳይኖራት ቆይቷል፡፡
ይሁንና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ማስተር ፕላኑ ከመፅደቁ በፊት የወረዳ፣ የክፍላተ ከተማና ማዕከል የሚገኘው ዋናው ምክር ቤት ጋር በጋራ እንዲወያዩበት ማድረጉን ገልጿል፡፡
ታኅሳስ 22 ቀን 2009 ዓ.ም በተካሄደው ውይይት በሚቀጥሉት አሥር ዓመታት ወይም 25 ዓመታት ተግባራዊ የሚደረገው ማስተር ፕላን ይዘትና ይዟቸው የሚመጣቸው ተስፋዎች ላይ፣ የቀድሞው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ፕሮጀክት ኃላፊ አቶ ማቴዎስ አስፋው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
አዲስ አበባ ከተማ በ130 ዓመት ታሪኳ ዘጠኝ ማስተር ፕላን አስተናግዳለች፡፡
ከዚህ ቀደም ወደ ጎን ስትለጠጥ ቆይታ ያላትንም 54 ሺሕ ሔክታር መሬት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ግንባታ ያካሄደችበት አዲስ አበባ፣ ከኦሮሚያ ክልል በደረሰው ከፍተኛ ደም አፋሳሽ ተቃውሞ ሳቢያ “በአዲሱ ማስተር ፕላን ወደ ጎን መለጠጧን አቁማ ወደ ላይ ከፍ ማለት ትጀምራለች” ሲሉ አቶ ማቴዎስ ገልጸዋል፡፡
በሚቀጥሉት አሥር ዓመታት የአዲስ አበባ ሕዝብ ቁጥር አሁን ካለበት አራት ሚሊዮን በተጨማሪ፣ 1.3 ሚሊዮን ሕዝብ አዲስ ነዋሪ ሆኖ እንደሚመዘገብና ይህ ሁሉ ሕዝብ በመሀል ከተማ እንደሚሰፍር ይታወቃል።

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እናት ወይዘሮ ፋናዬ ይርዳቸው ስለ ልጃቸው ያቀረቡት አቤቱታ ቆንጅት ስጦታው



የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እናት ወይዘሮ ፋናዬ ይርዳቸው ስለ ልጃቸው ያቀረቡት አቤቱታ
============
24/4/2009ዓ.ም
ለኢትዮጵያሰብዓዊመብትኮሚሽን
አዲስአበባ
ጉዳዩ፡-የልጄ የተመስገን ደሳለኝን ጤንነትና የጉብኝት ሁኔታን ስለማወቅ
የልጄ ተመስገን ደሳለኝን ጉዳይ ይዤ እናንተው ጋር መመላለስ የግድ ሆኖብኝ ዛሬም ከደጃችሁ መጥቻለሁ፡፡ ባሕሌና አስተዳደጌ ያስተማረኝ አንድቦታ ለአንድ ጉዳይ መመላለስለ ችግሩ ባለቤትም ሆነ ለመፍትሄ ሰጭው አሰልቺ መሆኑን ነው፡፤ እውነት ለመናገር ዛሬም ወደ በራፋችሁ ስመጣ እንደው እነዚህን ሰዎች ስራ እያስፈታኋቸው ይሆን ከሚል ሃፍረት ጋር ነው፡፡ ግን ምን ላድርግ? ጉዳዩ ልጅን የሚያኽል የስጋ ክፋይ ነገር ሆነብኝ፡፡ እንድትረዱልኝ የምፈልገው እኔም ተቸግሬ እያስቸገርኳችሁ መሆኑን ነው፡፡ በተጨማሪም ጭንቀት እረፍት ስላሳጣኝና ጤናዬንም እየፈተነኝ በመሆኑ የመፍትሔ ያለህእ ያልኩ አለሁ፡፡
ከዚህ ቀደም እናንተ መ/ቤት ብቅ ያልኩት ልጄን ለመጎብኘት ፈቃድ እንዳገኝ ትተባበሩኝ ዘንድ ነበር፡፡ በወቅቱ የተሰጠኝ ምላሽ እጅግ እንዳስደሰተኝ በአደባባይ መናገሬን ማንምያውቀዋል፡፡ አንጀቴ እንደራሰም ሁሉም ተረድቶታል፡፡ ዛሬም በድጋሜ ስመጣ በባለፈው መፍትሔ ተበረታትቼ ነው፡፡ ይህን ሳልናገር ማለፍ በእኔ እድሜ ለሚገኝ ሰው መልካም አይሆንም፡፡ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ የዛሬውም አቤቱታየ ተመሳሳይ ምላሽ እንደሚኖረው በሙሉ ልቤ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
በዝዋይ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የሚገኘው ልጄ ተመስገን ደሳለኝ ከታሰረ ሁለት ዓመታት አለፉ፡፡ በዚህ ግዜ ውስጥ የወገብ ህመምና የጨጓራ በሽታ እየባሰበት መምጣቱን በተደጋጋሚ ሰምቻለሁ፡፡ አንደኛው ጆሮውም ስቃይ እየፈጠረበት መከራውን እንዳባሰበት እሱን ባየሁበት ወቅት ለማወቅ ችያለሁ፡፡ ይባስ ብሎም የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር አለፍ አለፍ እያለ ያለመጎብኘት እገዳ ይጥልበታል፡፡ ይኽን ታዲያ ምን ትሉታላችሁ? በእስር ላይ ሌላ እስር አይደለምን? እነዚህና መሠል ተደራራቢ ችግሮች እየከፉ መምጣታቸው በእኔና በተቀሩት ጎብኝዎቹ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትና ጭንቀትን ፈጥሮብናልን፡፡
ከሳምንንታት በፊት ህዳር 28/2009ዓ.ም የዝዋይ ማረሚያ ቤት ሰዎች ልጄ የት አንዳለ አናውቅም በማለታቸው ለአስር ቀናት እምጥ ይግባ ስምጥ ሳላውቅ በእየሰር ቤቱ ከሚንከራተቱት ልጆቼ ጋር ልጄን ፈለኩት፡፡ አለገኘሁትም፡፡ የወለደ አንጀት አልስች ልቢለኝ “እርሜን ላውጣ” እያልኩኝ ልጄን ስል ሰነበትኩኝ፡፡ መቼምአምላክ ሰሚነውና በአስረኛው ቀን ታህሳስ 7/2009ዓ.ም በዝዋይ እስር ቤት ተመሰገን ተገኘ አሉኝ፡፡
ደስም አለኝ፡፡ ግን ምን ዋጋ አለሁ ይኼን ደስታ ማቅ የሚያለብስ ሌላ ወሬ ደረሰኝ፡፡ ‹‹የልጄን ዓይን አያለሁ›› ብዬ በተነሳሁ ውዬ ሳላድር በድጋሜ የክልከላው ዕጣ እኔኑ ገጠመኝ፡፡
ከዚህም አልፎ ህመሙ እንደ ባሰበትና ከእስር ቤቱ ቅጥር ውጭ ወደሚገኘው ባቱ ሆስፒታል እንዳደረሰው ልጆቼ ቢደብቁኝም ስለጉዳዩ የሚያውቁ ሰዎች ነግረውኛል፡፡ ይህን ከሰማሁ ጀምሮ ተመስገን ስል ዛሬም አለሁ፡፡
ብቻ ተባበሩኝ፤ እርዱኝ፡፡ ይኼን መከራ ብቻዬን ለመወጣት አቅም የለኝም፡፡ የምታግዙኝ ነገር እንዳለ ስለተረዳሁ ነው የእናንተንም ደጅ የምጠናው፡፡ እገዛችሁ ልጄን የማየት ምኞቴንና እርሱም የሚያስፈልገውን የህክምና እርዳታ በአፋጣኝ እንደሚያስገኝለት ሙሉ ዕምነት አለኝ፡፡ እስኪ ለሁሉም ፈጣሪ ይርዳን፡፡
ከሰላምታጋር፡፡
ወ/ሮ ፋናዬይርዳቸው
ግልባጭ
 ለጠቅላይሚኒስቴር ጽ/ቤት
 ለተወካዮችምክርቤትአፈ-ጉባዔ ጽ/ቤት
 ለተወካዮችምክርቤትየህግ፣ ፍትህናአስ/ር ጉዳዮች ቋ ኮሚቴ
 ለጠቅላይዐቃቤህግ ጽ/ቤት
 ለሰብዓዊ መብቶችጉባኤ (ሰመጉ)
 ለሕዝብ ዕምባ ጠባቂ ተቋም
 ለኢትዮጵያቀይመስቀልማሕበር
 ለሚዲያዎች

በእነ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ አስተባባሪነት ቂሊንጦን በማቃጠልና ታራሚዎችን በመግደል የተጠረጠሩ 121 እስረኞች ተከሰሱ EthiopianReporter.com



ከጥር ወር 2008 ዓ.ም. ጀምሮ ከእስር ለማምለጥ ከዶ/ር ፍቅሩ ማሩና ከተለያዩ እስረኞች ጋር ሲወያዩ የከረሙ ታራሚዎ፣ ነሐሴ 28 ቀን 2009 ዓ.ም. ቂሊንጦ ጊዜያዊ የተከሳሾች ማረፊያ ቤትን በማቃጠልና የ23 እስረኞችን ሕይወት አጥፍተዋል የተባሉ 121 እስረኞች ተከሰሱ፡፡
የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ለፍርድ