Sunday, September 25, 2016

«ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው ጁኔይድ ሳዶ ሙሉ ታሪኩ እነሆ፤



«ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው ጁኔይድ ሳዶ ሙሉ ታሪኩ እነሆ፤ Achamyeleh Tamiru
«ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው የቀድሞው የኦሮምያ ክልል ፕሬዝደንት የነበረው ጁኔይድ ሳዶ ነው። ጁኔይድ ሳዶ «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይንም «የእባብ ልጅ እባብ» ያለው ያሁኑን የአማራ ትውልድ ነው። ሙሉ ታሪኩ እንደወረደ እነሆ፤
__________
<< «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ/የእባብ ልጅ እባብ» የሚለውን አቶ ጁነዲን ሳዶ ነበር ያሉት!!! ሰውየው ከኢህአዴግ ጋር በትልቅ የስልጣን ኮርቻ የነበሩና ዛሬ እራሳቸውን ከፓርቲው ያራቁ ወደተቃውሞም የገቡ ሊደነቁ የሚገባቸወ ናቸው። ቢሆንም ቅሉ ከመንግስት ጋር ተጣልቶ የሸሸ የድሮ ባለስልጣን ሁሉ እንደ ሀቀኛ መቁጠርና ማጀገን ግን ጅልነት ነው። የአቶ ጁነዲን ሳዶን ለአብነት እንይ ከዚህ ቀጥሎ የማወራላችሁ በጊዜው እዚያው ሰብሰባ ላይ በአካል ከነበረና የአቶ ጁነዲን ሳዶ ስም ሲነሳ እጅጉን የሚያመው አንድ ጓደኛየ ነው።
ጊዜው በ1997 ዓ.ም. የምርጫ ወቅት ነበር። አቶ ጁነዲን ሳዶ የኦሮሚያ ክልል ተወላጅ የሆኑትን የአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ሰብስቦ ፖለቲካዊ ስብከት እያደረገ ነው። በሰብሰባው የነፍጠኛው ስርዓት በኦሮሞ ህዝብ ላይ ያደረሰው በደል፣ የነፍጠኛ ስርዓቱ የኦሮሞ ህዝብ ጠላትነት ብዙ ተሰበከ ከዚያም ለጥቆ አሁን ያሉት የነፍጠኛ ልጆችም ከአባቶቻቸው እንደማይለዩ እንደውም ተደራጅተው የነፍጠኛውን ሰርዓት ለመመለስ እየጣሩ እንዳሉና ይሀንን መፍቀድ አንደሌለባችው ብዙ ተባለ። በዚሁ ብዙ ሰው በስሜት ተናጠ። በመሀል አንድ ተማሪ ተነስቶ «ታድያ የዛሬ መቶ ዓመት የነበረን ነገር ካሁኑ ጋር እንዴት በቀጥታ ማገናኘት ይቻላል? እንዴት ያሁኑ የአማራ ተወላጆች ከዚያኛው ጋር በቀጥታ መገናኘት ተጠያቂም ማድረግ ይቻላል?” ብሎ ጠየቀ።
አቶ ጁነዲን ሳዶ የሰጡት መልስ እጅግ አሸማቃቂ ነበር። ቃል በቃል «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ/ የእባብ ልጅ እባብ» ነበር ያሉት። እጅግ አደገኛና መሰሪ አገላለፅ ነበር ያስፈራል! እንደነጁነዲን ሳዶ ዐይነቶች ጥላቻን የሚዘሩና ሌላ በርካታ በደል በህዝብ ላይ ያደረሱ ሰዎች ከመንግስት ጋር ተጣልተው መፅሐፍ ፅፈው ወይም በሌላ መልክ ተከስተው ይቅርታ ቢጠይቁ እንደኔ ተቀባይነት ያለው አይመስለኝም።>>
––––––––––
አቶ አሰፋን እጅግ እናመሰግናለን። ምንም እንኳ ሰውየውን የምናውቀው ብናውቀውም እሳቸው ደፍረው ይህንን የጁኔይድ ጉድ ባይነግሩን ኖሮ «የእባብ ልጅ እባብ» ብሎ እባብ ያደረገን ጁኔይድ ትናንት ወያኔ አላምጦ ስለተፋው ዛሬ እንደ እስስት መልኩን በመቀየር ህዝባዊ መስሎ የአዞ እንባ እያነባ የዋህ መስሎ ሊታይ «ቢሞክር ጅብ በማያውቀው አገር ሂዶ ቆርበት አንጥፉልኝ አለ» እንለዋለን።
የጋሽ አሰፋን ጽፉፍ ካነበብሁ በኋላ ጁኔይድ ትናንትና በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው ክፍል ያደረገውን ቃለ ምልልስ ካደመጥሁ በኋላ ዛሬ በሶስት ነገሮች ብቻ «ይቅርታ!» የጠየቀው ሰውዬ ትናንትና ያን ሁሉ አጥፍቶ ይቅርታው አልከበደውም ወይ ብዬ ትናንትና የተናገራቸውን ንግግሮች ፍለጋ ገባሁ። አንዱን ከታች ለጥፌዋለሁ። በዚህ ንግግሩ ውስጥ «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ/ የእባብ ልጅ እባብ» የሚለው ንግግሩ በኮድ ስም አለ። ወደ ድሮው ስርዓት ሊመልሱን ምናም የሚለው የኮድ ንግግር ነው። በዚህ የኮድ ንግግር ጁኔይድ እነ ልደቱን እያለ ያለው «ኢልሜን ቦፋ ቦፋደቴ» ወይም «የእባብ ልጅ እባብ» ነው።
ጁኔይድ ሳዶ ትናንትና በአሜሪካ ድምጽና በኦ.ኤም.ኤን የሰጠውን ላዳመጠ አሁን ይህንን ከታች ያተምሁትን ንግግር ከስድስት አመታት በፊት የተናገረው ነው ቢሉት ማን ያምናል? ይህንን ንግግር ይቅርታስ ያነጻዋል?



No comments:

Post a Comment