Friday, August 18, 2017

በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተሰማn source mereja

በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተሰማ
በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ በዛሬው ዕለት የወልድያ ህዝብ ‹‹አላግባብ የተጫነብኝን ግብር አልከፍልም፡፡›› ብሎ አሻፈረኝ ማለቱን ከስፍራው የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡ በዚህም የተነሳ ከተማው ውጥረት ማርገዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ባለፈው ሳምንት ለአምስት ቀናት የስራ ማቆም አድማ ላይ የሰነበተው የወልድያ ህዝብ፣ በዛሬው ዕለትም ተቃውሞ አስነስቷል፡፡ የህወሓት መንግስት በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ የግብር ጫና መጣሉ አይዘነጋም፡
በሀገሪቱ ነጋዴዎች ላይ የተጫነውን የግብር ጫና ተከትሎ በመላው ሀገሪቱ ተቃውሞ መቀስቀሱ የሚታወስ ሲሆን፣ ወልድያም ተቃውሞ ከተቀሰቀሰባቸው ከተሞች አንዷ ሆና ሰንብታለች፡፡ በዛሬው ዕለት ተቃውሞው በድጋሚ ማገርሸቱን የተናገሩት የከተማዋ የቢቢኤን ምንጮች፣ ህዝቡ ግብሩ ካልተቀነሰለት በቀር ለመክፈል ዝግጁ አይደለም ብለዋል፡፡ ምንጮቹ አክለውም ‹‹በግብር ስም ዘረፋ መፈጸም ተገቢ አይደለም፡፡›› ሲሉም የህወሓትን መንግስት የዘረፋ አዝማሚያ ተችተዋል፡፡
የከተማዋ ህዝብ ግብር አልከፍልም ማለቱን ተከትሎ፣ የፖሊስ ኃይሎች በከተማዋ መሰማራታቸውን የገለጹት ምንጮች፣ እስከ ምሽቱ አንድ ሰዓት ድረስም ከተማዋ ውጥረት ላይ እንደነበረች ይገልጻሉ፡፡ ከምሽቱ አንድ ሰዓት በኋላ ከተማዋ ጭር ብላ መታየቷን የገለጹት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ መሸት ካለ በኋላ የፖሊሶች ቁጥር ጨምሮ መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡
ጥያቄአቸው እስካልተመለሰ ድረስ፣ የዛሬው ተቃውሞ በነገው ዕለትም ሊቀጥል እንደሚችል ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ከግብር ጫና ጋር በተያያዘ ተቃውሞ ከተነሳ በኋላ፣ መንግስት የግብር ቅነሳ ይደረጋል የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ በመጨረሻም ግን ውሸት መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
BBN

Monday, August 14, 2017

ኢትዮጲያ የማን ናት? መብቱ የዜጎች፣ ስልጣኑ የብሔሮች ነው – ክፍል 2 – ስዩም ተሾመ source zehabesha

“ኢትዮጲያ የማን ናት፡ የብሔሮች ወይስ የዜጎች?” በሚል ርዕስ ባወጣነው የመጀመሪያ ክፍል የኢህአዴግ መንግስት ባለፉት አስር አመታት ፍፁም አምባገነን እየሆነ መምጣቱን ተመልክተናል። ለዚህ ደግሞ ዋና ምክንያቱ ከሕገ-መንግስቱ መሰረታዊ መርሆች ውስጥ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” በሚለው መርህ ላይ መንጠልጠሉና በዚህም ራሱ የዘረጋውን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት ቀልብሶታል።
በመሰረቱ፣ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” የሚለው ሕገ-መንግስታዊ መርህ ከሀገርና መንግስት አመሰራረት ፅንሰ-ሃሳብ ጋር ይጋጫል። ሌላው ቀርቶ ከሕገ-መንግስቱ ጋር ራሱ ይጋጫል። በአጠቃላይ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” የሚለው መርህ “ፀረ-ዴሞክራሲያዊ” ነው። “በእንቅርት ላይ ጆሮ-ደግፍ” እንዲሉ መንግስታዊ ስርዓቱ ደግሞ በዚህ መርህ ላይ እንደመሆኑ ሕገ-መንግስቱ፥ ብሎም ፖለቲካዊ ስርዓት ካልተቀየረ በስተቀር ዴሞክራሲ “ላም አለኝ በሰማይ…” እንደሚሉት ሆኖ ይቀራል። በዚህ ፅሁፍ፣ “ከሕዝብ ሉዓላዊነት” መርህ አንፃር የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት እርስ-በእርሱ እንደሚጋጭ እንመለከታለን። በቀጣይ ክፍል ደግሞ ከሀገርና መንግስት አመሰራረት አንፃር የተሳሳተ መሆኑን እንመለከታለን።
ስዩም ተሾመ
በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 8 መሰረት “የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤቶች ናቸው”።ነገር ግን፣ ይህ መርህ ከሉዓላዊነት ፅንሰ-ሃሳብ ጋር ይጋጫል። በዚህ ረገድ ያለውን የተሳሳተ እሳቤ በግልፅ ለመረዳት እንዲያስችለን የሕገ-መንግስቱን የቃላት አጠቃቀም እና የኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በ1993 ዓ.ም ያዘጋጀውን የኣማርኛ መዝገበ ቃላት መሰረት በማድረግ ፅንሰ-ሃሳቡን በዝርዝር እንመለከታለን።
በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 39(5) መሰረት “ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ” ማለት ሰፋ ያለ የጋራ ባህሪይ የሚያንፀባርቅ ባህል ወይም ተመሳሳይ ልማዶች ያሉት፣ ሊግባባበት የሚችልበት የጋራ ቋንቋ ያለው፣ የጋራ ወይም የተዛመደ ሕልውና አለን ብለው የሚያምን፣ የሥነ ልቦና አንድነት ያለውና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖር “ማህብረሰብ” ነው። (የቃላት ድግግሞሽን ለማስቀረት ሲባል እንደየሁኔታው “ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ” የሚለው “ብሔር” ተብሎ ሊፃፍ ይችላል።) በዚህ መሰረት፣ ብሔር በቋንቋ፥ ባህል፥ ልማድና ስነልቦናዊ አመካከት፣ እንዲሁም በታሪክ፣ ኢኮኖሚና በመልክዓ ምድር የተሳሰረ ማህብረሰብ ነው። በመሆኑም፣ የብሔር መብቶች ከእነዚህ ተፈጥሯዊ ባህሪያት ጋር በቀጥታ የተያያዙ ናቸው። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 39 ላይ “የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብት” በሚል የተጠቀሱት ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይህን ያመለክታሉ።
መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተደነገጉበት የሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍል ሁለት መሰረት፣ በንዑስ አንቀፅ 39(1) “ማንኛውም ብሔር የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከመገንጠል መብት”፣ በንዑስ አንቀፅ 39(2) “ማንኛውም ብሔር በቋንቋው የመናገር፥ የመፃፍ፥ ቋንቋውን የማሳደግ እና ባህሉን የመግለፅ፥ የማዳበርና የማስፋፋት፣ እንዲሁም ታሪኩን የመንከባከብ መብት”፣ በንዑስ አንቀፅ 39(3) ደግሞ “ማንኛውም ብሔር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ መብት” እንዳለው ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ፣ በሕገ-መንግስቱ ንዑስ አንቀፅ 40(3) መሰረት “የመሬት ባለቤትነት መብት”፣ እንዲሁም በንዑስ አንቀፅ 43(1) መሰረት ደግሞ “የልማት መብት” እንዳላቸው ይጠቅሳል።
በዋናነት በሕገ-መንግስቱ እውቅና የተሰጣቸው የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብቶች ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ናቸው። ከዚህ በተረፈ፣ በሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍል አንድ ስር የተዘረዘሩት በሙሉ የግለሰብ ሰብዓዊ መብቶች ናቸው። በክፍል ሁለት ከተዘረዘሩት ውስጥ ከአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) በስተቀር ያሉት በሙሉ የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ፣ እያንዳንዱ ግለሰብ ግን እንደ አንድ ብሔር ተወላጅ ከላይ የተጠቀሱት የብሔር መብቶች ይኖሩታል።
የአማርኛ መዝገበ ቃላት “ሉኣላዊ” (Sovereign) የሚለውን ቃል “ነፃ የሆነ መሬት፣ ነፃ የሆነ፥ ምሉዕ ስልጣን ያለው ሀገር፥ መንግስት” የሚል ፍቺ ይሰጠዋል። “ሉዓላዊነት” (Sovereignity) ማለት ደግሞ “ምሉዕ የሆነ መብት፥ የነፃነትና ሥልጣን የበላይነት” እንደሆነ ይገልፃል። በዚህ መሰረት፣ “የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት” የሆነ አካል በቅድሚያ ምሉዕ መብትና ነፃነት ሊኖረው ይገባል።
በአጠቃላይ፣ በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉት ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሙሉ መሰረታዊ የግለሰብ መብትና ነፃነት ሊሆኑ ይችላሉ። የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብቶች ግን በአንቀፅ 39፣ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት መብቶች ብቻ ናቸው። በዚህ መሰረት፣ አንድ ግለሰብ ምሉዕ መብትና ነፃነት አለው። በተቃራኒው አንድ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ ግን ምሉዕ መብትና ነፃነት የለውም።
ቀደም ሲል ለመግለፅ እንተሞከረው፣ “ሉኣላዊነት” (Sovereignity) ማለት “ምሉዕ የሆነ መብት፥ የነፃነትና ሥልጣን የበላይነት” ነው። በዚህ መሰረት፣ አንድ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ ሉዓላዊ ስልጣን እንዲኖረው በቅድሚያ ምሉዕ መብትና ነፃነት ሊኖረው ይገባል። ነገር ግን፣ በሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍለ አንድና ሁለት ስር ከተዘረዘሩት 31 መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች ውስጥ የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብት የሆኑት በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት ብቻ ናቸው። ከእነዚህ ውጪ ያሉት በሙሉ የግለሰብ መብቶች ናቸው።
እያንዳንዱ ግለሰብ በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት የብሔር መብቶች እንደ አንድ ብሔር ተወላጅ ይኖሩታል። እያንዳንዱ ብሔር ግን በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) ከተጠቀሱት ውጪ ሌላ ዴሞክራሲያዊ መብት ሊኖረው አይችልም። ምክንያቱም፣ ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ እንደ ግለሰብ በራሱ ሃሳብና አመለካከት የሚንቀሳቀስ ምክንያታዊ ፍጡር ስላልሆነ ሌሎች ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሉትም። በተመሳሳይ፣ እንደ ሰው ሰብዓዊ ፍጡር ስላልሆነ “ሰብዓዊ” መብት ሊኖረው አይችልም። ስለዚህ፣ በሕገ-መንግስቱ ራሱ ምሉዕ መብት ያለው ግለሰብ እንጂ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ አይደለም።
በአጠቃላይ፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን የሚችለው እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ ዜጋ እንጂ የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች አይደሉም። ምክንያቱም፣ የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት በምዕራፍ ሦስት ስር ከዘረዘራቸው 31 መሰረታዊ መብቶች ውስጥ ሦስት መብቶች ብቻ ያሏቸው ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች “የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት” እንደሆኑ ይገልፃል። ነገር ግን፣ “ሉኣላዊነት” የምሉዕ መብትና ነፃነት ባለቤትነት እንደመሆኑ መጠን ውስን መብት ያላቸው ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤትነት ሊኖራቸው አይችልም። በዚህ መሰረት፣ የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት እርስ-በእርሱ እንደሚጋጭ በግልፅ መረዳት ይቻላል።
በመጨረሻም፣ በሕገ-መንግስቱ መሰረት እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ ዜጋ ምሉዕ የሆነ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት አለው። በዚህ መሰረት፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን የሚችሉት ሁሉም ኢትዮጲያዊያን ወይም ሁሉም የሀገሪቱ ዜጎች ናቸው። ይሁን እንጂ፣ በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 8 መሰረት “የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤቶች እንደሆኑ ተደንግጓል። ስለዚህ፣ ሕገ-መንግስቱ እርስ-በእርስ እንዲጋጭ የተደረገበት ምክንያት ምንድነው?
በመሰረቱ፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት የሆነ አካል ባለመብት ብቻ ሳይሆን ባለስልጣን ጭምር ነው። ምክንያቱም፣ ሉዓላዊ ስልጣን ያለው አካል በሀገሪቱ መንግስት ላይ የስልጣን የበላይነት ይኖረዋል። ስለዚህ፣ የሀገሪቱ መንግስት ተጠሪነቱ ለዚህ አካል ይሆናል። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት መሰረት፤ የሀገሪቱ ዜጎች መብትና ነፃነት አላቸው፣ ብሔሮች ደግሞ የሉዓላዊ ስልጣን አላቸው። ዜጎች ምሉዕ መብት አላቸው፣ ነገር ግን መብታቸውን የመጠየቅ ምሉዕ (ሉዓላዊ) ስልጣን የላቸውም። ብሔሮች ደግሞ ምሉዕ (ሉዓላዊ) ስልጣን አላቸው፣ የሚጠይቁት ምሉዕ መብት ግን የላቸውም። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት መሰረት መብቱ የዜጎች ሲሆን ስልጣኑ ግን የብሔሮች ነው!
በአጠቃላይ፣ የሀገሪቱ ዜጎች የማይጠይቁት መብት ሲኖራቸው፣ የሀገሪቱ ብሔሮች ደግሞ የማይጠቀሙት ስልጣን አላቸው። የኢህአዴግ መንግስት ዘወትር ስለ ብሔር መብትና እኩልነት ይደሰኩራል። ዜጎች የመብትና እኩልነት ጥያቄ ሲያነሱ ግን እንደ ጠላት እያደነ ያስራል፥ ይገድላል፥…ወዘተ።

Friday, August 11, 2017

የሜቴክ ውንብድና….በአዲስ አበባ ትራንሰፖር አውቶቢስ ግዢ ላይ (ጥብቅ መረጃ) source zehabesha

በበዛብህ ሲሳይ (2009) ሀይድራባድ ህንድ
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ ሰሞኑ በቀድሞ የስርዓቱ ልሳን በነበረው በአቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሜቴክ ከንግድ መርከብ ስለገዛቸው ሁለት መርከቦችና ሊያቋቁመው ስላሰበው የውሃ ትራንስፖርት ንግድ ስራ እንዲሁም በአገሪቷ ላይ ያደረሰውን ኪሳራ ካይሁ በኃላ ነው፡፡ እውነት ነው ተቋሙ ሲቋቋም ጀምሮ ለገዢው ጉጅሌ ኢኮኖሚያዊ ትርፍ እንዲያመጣ ተብሎ ብቻ አይደለም የትግራይ ተወላጆችን ከሰሜን ኤርትራዋኖች ላይ እንዲሁም ከደቡብ ደግሞ ሰፊው የኢትዮጰያ ህዝብ ላይ የፖለቲካዊ ልእልና እንዲያመጣ ጭምር እንጂ፡፡ ስለዚህ አቶ ኤርምያስ እንደ አስቀመጠው የሜቴክ መሪዎቹ ሲጋራን በቄንጥ ሚያጨሱ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ እኩይ አላማቸው ላይ የሚሳተፉትን ሆድ አደር “ሙሁራን” ወይም ባለሰርተፊኬቶችን ወይም እንዴት ማስተዳደርና መጠቀም እንዳለባቸው ስለሚያውቁ ይሄው ይሄ ሁሉ ጉዳት በአገሪቱ ላይ ሊያደርሱ ቻሉ፡፡ አንዳንዴ የፈረንጅንም ጫማ ላሾችንም (Bootlikers) ይጠቀማሉ፡፡ በዚህ ጽሁፍ ዋና አላማ ሜቴክ ተልዕኮውን እንዴት እንደሚያሳካ ለማሳይት የታሰበ ሲሆን ፅህፉ ያለውን ነባራዊ ሁኔታን ብቻ የሚያሳይ ነው..ፍርዱን ደግሞ እናነተ ስጡ… መልካም ንባብ !!

በመጀመሪያ ግን አንባቢያን ሊገነዘቡት የምፈልገው ሜቴክ መቆጣጠር ሚፈልገው የኢኮኖሚ አውታር በዋነኝነት ከአገር ውስጥ ወይም ከዉጭ ሃገር ልዪ የፋይናንስ ድጋፍ ያላቸውን ፕሮጀክቶች ሲሆን ትራንስፖርት ደግሞ ዋነኛ ነው ምክንያቱም ከአለም ባንክ ወይም ከቻይና ኤግዚም ባንክ አብዛኛው ብድር የሚሰጠው ለመሰረተ ልማት ግንባታ በመሆኑ ነው፡፡ ሜቴክ ገና ጥርሱን ሳይነቅል ዘሎ ዝርፊያውን የጀመረው የቀድሞ ኢትዮ- ጂቡቲ ባቡር ሃዲድ ላይ ጉብ በማለት ነው፡፡ ለተበተነው የባቡር ሰራተኞች ደሞዝ እከፍላለሁ በሚል ተልካሻ ሰበብ በ1907 የተመረተውን ንፁህ የባቡር ሃዲድ ብረት ወረሰው፡፡ ካለምንም ማስረጃ፡፡ ለዚያውም በ ፈረንጆች 2006 ከአውሮጳ ህብረት በተገኘ የ50 ሚሊዮን ዩሮ ብድር የመልሶ ማቋቋም እድሳት ስራ ጀምሮ የነበረውን እንዲቋረጥ በማድረግ ነው (ግርጌ ፎቶውን ይመልከቱ)፡፡ በመስኩ የተሰማሩት ባለሞያዎች እንሚሉት የቀድሞ የባቡር መስመር በትክክል ቢሰራ ኢትዮጵያ የምታስገባውንም ሆነ የምታስወጣውን ጭነት በአስተማማኝ ከማስተናገዱ አልፎ ሃገሪቱ በሚቀጥሉት ሃያ አመታት ልታመጣው የምትችለውን የኢኮኖሚ እድገትም መሸከም የሚችል ነበር፡፡ ይሄ ለነክንፈ እና አርከበ አይገባቸውም፡፡ የአዲስ አበባ ባቡርም በሰዓት ሃያ ሺህ ህዝብ ያመላልሳል በለው ጉፋያአቸወን ነፍተው አመት እንኳን ሳያገለግሉ ግማሽ ያህሉ ወላለቀው መሃል ሜዳ ላይ ቆሙ!! ሌላው ቢቀር ኢትዮ- ጂቡቲ ባቡር ታሪካዊነቱ ታይቶ ልክ በሰለጠኑት አገራት እንደሚገኙት የድሮ የባቡር መስመሮች ለቱሪዚም አገልግሎት መዋል ይችል ነበር፡፡ በተለይ ከአዲሱ መስመር በበለጠ በብዙ ከተሞች ላይ ማረፊያ ተሪሚናሉች ስላሉት ከተሞችን በንግድ በማስተሳሰር ከፍተኛ አስተዎጽኦ ማምጣት ይችል ነበር፡፡ይሄም ባቡር ወደ 32 ሚሆን ቦታ ላይ ሲያርፍ የቀድሞ ግን ከ100 በላይ ቦታዎች ላይ በማረፍ የከተሞች የኢኮኖሚ እና የማህበረሰብ ትስስርን ያጠናክር ነበር፡፡ ሆኖም ለታሪክ ደንታ የማየሰጣቸው የትግራይ ጉድሌዎችን ያቀፈው ሜቴክ ታሪካዊዉን የበቡር ሃዲድ ብረት ሃላፊነት በጎደለው መንገድ ስልቅጥ አድርጎ በላው፡፡

ከዚህ የረቀቀ አገርን የማውደም ሴራ በሰተጀርባ ያለውን ለመረዳት ግን ከጀነራሎቹ ጋር በመሆን ለሜቴክ ጭንቅላት የሆኑትን ሆድ አደር ምሁራን ተብየዎችንም አብረን ማየት ያለብን፡፡ ምክንያቱም ጠቋሚዎቹና አስተባባሪዎቹ እነሱ ስለሆኑ!!!
ሙሁር ተብየዎችን በማፍራት ግንባር ቀደም የሆነው ገና ከተቋቋመ 20 አመት በሞላው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የሜቴክን አላማ የሚተገብሩለትን በላተኞችን የሚኮተኩትበት ዋነኛ ወታደራው ተቋም ነው፡፡ አካዳሚያዊነቱን ግን ብላሽ ብቻ አይገልፀውም፡፡ አንዴ እዚያ የሚያስተምር ጓደኛየን C ሰጠኅን ብለው ደብድበውታል፡፡ ከዚህ ተቋም የሚመረቁ “ባለሞያዎች” የወታደር ስነ-አምሮ የተላበሱ በመሆናቸው በሲቨል ተቋም ዉስጥ ሲገቡ ይሄንን የመታዘዝና-የማዘዝ ህግጋትን ስለሚተገብሩ ወይም በውይይትና የአመክንዮ ልእልና ስለማያምኑ በሜቴክ አለቆች ዘንድ እጅጉን ጀርባ የሚጣልባቸውና የሚወደዱ ናቸው፡፡ በዩንቨርሲቲው ትምህርት ላይ እያሉም እርስ-በራስ የመገማገምን ትምህርትና የሰዎችን ጉልበት ማሟጠጥ የሚችሉበትን ክህሎት ይቀስማሉ፡፡ ስለዚህ ወደ ስራ ሲገቡ የራሳቸውን ኔትዎርክ በቶሎ ይዘረጉና ምዝበራውን ያሯሩጡታል፡፡ በለራዕዩ መለስ አገሪቱ የተማረ ወታደር አያሰፈልግጋትም ካለ ከዚህ ተቋም የሚወጡት ለሌላ አላማ ነው ማለት ነው፡፡
ከዚህ ቀጥሎማ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ተቋማቶችን በአይን በመማተር ለአለቆቻቸው ሹክ ይላሉ፡፡ ገሚሱን ቻይና በመላክ የውንብድና ሊቅ ሲያረጉዋቸው የተቀሩትን ደግሞ አይናቸውን ጨፍነው አገራዊ (local) ሮል ሞዴል እንዲያበጁ ያረጓቸዋል፡፡ እኔም ከአምስት ከማያንሱ የቀድሞ የስራ ባለደረቦቼ የተረዳሁት አብዛኛዎቹ መለስን እንዲሁም ጥቂቶቹ ስየን እንደ ትልቅ ሮልሞዴል እንደሚዩዋቸው ነው፡፡ ሁለት ዘራፊዎችን!!! ከዚህ ዝግጅት በኃላ ወደ ሲቭል ተቋማት በማስገባት ነባር ተቋማትን በማፍረስ በምትካቸው አዳዲስ ለሚቋቋሙጽ ስም በመስጠት በሮዎችን መክፈት !…ለምሳሌ ኤጀንሲ ፣ባለስልጣን፣ ፅ/ቤት ፣ ተቆጣጣሪ፣ …የረሳሁት ካለ አግዙኝ! ከዚህም አዳዲስ የሚቋቋሙበት ዋና አላማ ተቋሙን ለማደራጀት ተብሎ ከሚመደበው የማቋቋሚያ ገንዘብ ለቤት ክራይ፣ ለጠረቤዛ፣ ለመኪና፣ ..ወዘተ ብለው እንዲጨርሱትና አዳዲስ ተቋማት ውስጥ የራሳቸውን ሰዎች በመሰግሰግ ወደፊት ለሚዘርፉት መንገድ በማበጀት ተጠያቂነት ፈፅሞ እንዳይኖር ለማድረግ ነው፡፡
የሜቴክ መሰሪ አላማ ለመመልከት እስቲ የአዲስ አበባ የመንገዶችና ትራንስፖርት ቢሮን እንይ፡፡ በ2005 ከንቲባ ደሪባ ኩማ ሲሾሙ የከተማይቱን የትራንሰፖርት ችግር ይቀርፋሉ ተብሎ በሰፊው ተዘግቦ ነበር፡፡ በተለይ ፎርቹንና ሪፖርተር ከተቋሙ ጋር ልዩ ጥቅም ስላላቸው የማይመስል ወሬ በማራገብ አንደኛ ናቸው-ለምሳሌ አዲስ አበባ የብስኪሌት ታክሲ ልታገኝ ነው (1 ቀን ሳየሰራ 16 ሚሊዮን ብር አፈር ድሜ ያበላና የከተማዋ ነዋሪዎችም ሽንታቸው እስኪለቁ የሳቁበት)…..15 ፎቅ ያለው ዘመናዊ በኤሌክትሪክ የሚሰራ ፓሪኪንግ ተመረቀ (አጠገቡ ያሉ ኢንተርኔት ቤቶች በኤሌክትሪክ መጥፋት ስራቸውን እንደተዉ ከንቲባው ሳይሰማ ለአድቬንቸር ብሉ የ85ሚሊዮን የብረት ሼልፍ ይመርቃል)… ሌላም ብዙ ብዙ፡፡
ወደ ትራንስፖርት ቢሮው ልመለስና የከተማው ነዋሪ ያለበትን የትራንሰፖርት ችግር ለመቅረፍ አዲስ ተቋም ያስፈልጋል በሚል የትራንስፖርት ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት በሚል እንዲቋቋም ይደረጋል፡፡ ይታያቹህ ለዝርፊያው ያመች ዘንድ መጀመሪያ የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ተብሎ የነበረው ፅ/ ቤት ባንዴ እንጣጥ ብሎ የፕሮግራም ማሰተባበሪያ ሆነ! እውነቱ ግን በየትኛውም አለም የተለያዩ ፕሮግራሞችን ማሰተባበር አይቻልም … የእውር መንገድ ለመሆኑና ለመዝረፍ ተብሎ በሜቴክና በከንቲባው የተቀናበረ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንደ ፀጉራም ዉሻ አግዝፈው ትልቅ በጀት ለመመደብ እንደሆነ ለሁሉም ባለሞያ ግልፅ ነበር፡፡ የሆነውም ይህንን ተቋም እንዲመራ በብ/ጀ ክንፈ ዳኜው የተመደበው የመከላከያ ዩንቨርሲቲ ምሩቁና የቀድሞ የመረጃ ደህንነት ሰራተኛ የነበረው ዶ/ር ሰለሞን ኪዳኔ ሲሆን ከመጀመሪያውኑ የሜቴክን አላማ ለማሳካት የተተከለ ወታደር ነው፡፡

በመጀመሪያ አዲስ የሚቋቋሙትን ተቋማት ከመደበኛ የሲቪል ሰርቪስና የፋይናንስ ቢሮክራሲ በማስወጣት በቦርድ እንዲተዳደር ማድረግ ሲሆን የቦርድ አባላቱም ባብዛኛወቹ አብሮ በላተኞችና በዶ/ሩ የተመረጡና የቀድሞ የመከላከያ ምሩቃንን የሚያጠቃልል ነበር፡፡ ከንቲባውም ቦርዱን አንድ ቀን ሳይሰበስበው ዶ/ሩ ሁሉን የሚያዝ ሆነ፡፡ ከዚህ በኃላማ ማን ይመልሰው……ልጁ ቀማኛ …አባቱ ዳኛ ሆነው እርፍ! የከተማይቱ ነዋሪ የሚፈልገው ግማሽ ኪሎሜትር ከሚደርሰውን የታክሲ ወረፋ የሚገላግለው ሆኞ ሳለ ባለ 15 ፎቅ ፓርኪንግ፣ ደብል ዴክ የአቶቢስ ማቆሚያ፣ ተርሚናሎች፣ የማይሰሩ የትራፊክ መብራቶች በየአደባባይ መትከል….ብቻ በአጠቃላይ ሜቴክ እንደሚያረገው ጉፋያውን መንፋት ብቻ ሆነ፡፡ ለዚህም ከከንቲባውና ምክትሉ አቶ አባተ ስጦታው ጋር ልዩ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ነባሩን አንበሳ አውቶቢስን (ከአፄው ጊዜ ጀምሮ የነበረ) እንደማጠናከር ፋንታ ሌላ በዚሁ ትራንስፖርት ቢሮ ስር የሚተዳደር አዲስ ሸገር አውቶቢስ የሚባል በመፍጠርና ሜቴክን በአውቶቢስ ግዢ ማክበር ሆነ ዋነኛው አላማ፡፡ በአምባሳደር ሱለማን ደደፎ ደብዳቤ ላይ እንደተገለፀው አዲስ የመርከብ ንግድ ሊጀምሩ እንዳሰቡት ማለት ነው!
ለዚህም ከመስተዳድሩ የሚበጀትና ከአለም ባንክ ሊገኝ ከታሰበው ከ300 ሚሊዮን ዶላር አብዛኛው ለሜቴክ አውቶቢስ መግዢያና ለትራፊክ መብራት መትከያ የሚውል ሲሆን ሜቴክ እስከ አሁን ወደ 1000 አውቶቢስ አገር ዉስጥ ገጣጥሞ ለመስተዳድሩ ያስረከበ ሲሆን አሁን ደግሞ የ750 አውቶቢስ አዲስ ውል አስሯል፡፡ እንደ ሪፖርተር ጋዜጣ ሃተታ ሜቴክ አንዱን አውቶቢስ በ3.6 ሚሊየን ብር ሲሸጥ ሌላው በግል የሚተዳደረው አልያንስ ባስ ደግሞ ተመሳሳይ አውቶቢስ በ 1.6 ሚሊየን ከቻይና ያለቀለት ያስመጣል፡፡ ልዩነቱ የአልያንስ አውቶቢስ ካሜራ ስላልተገጠመለት ብቻ ነው!! በጣም አስቂኝና የሜቴክ- ከንቲባው ድብቅ አላማ ፍንትው አድርጎ ያሳያል፡፡ ይሄም ሜቴክ አደናጋሪ ቃላት በሲቨል መስሪያቤቶች በወተፋቸው ወታደሮቹ እያስነገረ ህዝቡን ማደኸየትና መሰረታዊ ለውጥ በማሓከለኛው ሃገር እንዳይመጣ በማድረግ የፖለቲካዊ አላማውን ያስፈፅማል፡፡ ሌላው የሜቴክ ዘመዶች ደግሞ የተሳተፉበት የሰብ-ኮንትራት ቢዝነስ በትራፊክ መብራት በመትከል ሰበብ ዘመዶቻቸውን ዊስኪ ጨብጠው ለሊቱን እንዲያነጉ ያደረጓቸዋል፡፡ ለዚህም ወደ 170 ሚሊየን ዶላር አዲስ የተመደበ የወንበዴው ወርልድ ባንክ ብድር መንገድ ላይ ነው፡፡ ለዚሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወንድም አቶ ገነቱ ደሳለኝን ስራ አስኪያጅ አድርጎ ዝርፊያውን መሸፋፈንና አጋላጭ እንዳይኖር ማድረግ ነው፡፡
ይህን ሁሉ ስናይ እነዚህ ሰዎች ሁዋላ ከማን ጋር ሊኖሩ ነው የሚለው የሚያስጨንቅ ጥያቄ በአምሮየ ይመላለሳል …..ውይይይ… ሰው ልቦና ከሌለው ለምንም አይሆንም…ለልጆቻቸው ግን ወየዎላቸው……..ግፉ ሲበዛ በሃይለኛው መልሶ ይገፋችኃል፡፡ በ 1960ዎቹ የተማሪ ንቅናቄ ጊዜ የምንለው ነበር……ነቅናቂው ተነቃናቂውን ሲነቀንቀው ተነቃናቂው ነቅናቂውን መልሶ ነቀነቀው!! …..ሰው እያወቀ ነው ዝም ያለው……. ልብ ግዙ ነው ምክሬ!!!! በሚቀጥለው ደግሞ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ኤጀንሲን ላይ አስነብባቹሃለሁ፡፡
ሠላም ሁኑ!

Wednesday, August 9, 2017

“የባህር ዳሩ ዕልቂት አይረሳም.. ሕዝቡ ሰማዕታቱን ሲያስብ አደራቸውን መርሳት የለበትም” – አክቲቭስት ሙሉነህ ዮሐንስ (ጠቃሚ መረጃዎችን የያዘ ቃለምልልስ) sorce zehabesha

“…በባህር ዳር በአንድ ቀን የፈሰሰው የንጹሃን ደም የሚረሳ አይደለም:: ሕዝቡ ሰማዕታቱን ሲያስብ አደራቸውን መርሳት የለበትም…የለውጥ ፈላጊው ተቃዋሚ እርምጃን በተለይ የእውነተኛ ትብብር አለመኖር አንዱ ከአንዱ ጋር ተባብሮ ያለመስራቱን በተመለከተ በተለይ ሚዲያው ግልጽ ውይይት የሚደረግበትን የህዝቡ ትግል በእውነት የሚደገፍበትን ለለውጡ የሚደረገው እንቅስቃሴ ትርጉም ያለው እንዲሆን ሀላፊነት ያለባችሁ ይመስለኛል…”  አክቲቪስት ሙሉነህ ዮሐንስ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከሰጠን ማብራሪያ (ቀሪውን ያድምጡት)






Tuesday, August 8, 2017

የብአዴን ነገር ( ግዛው ለገሰ ) source zehabesha

የብአዴን መስራቾች አንድማን እንደሆኑ ለሚያውቅ ሰው ብአዴን የአማራ ብሄርተኛ ድርጅት አለመሆኑን ለማወቅ ቀላል ነው:: የዘር ስብጥሩን  ስሌት ትተን የትግል መስመራቸውን ስናይ ቢያንስ ቢያንስ ኢትዮጵያ የብሔሮች እስር ቤት ናት የሚለው የዋለልኝ መኮንን የሞቅ ሞቅ ደቀመዛሙርት  መሆናቸውን እናያለን።
ስለሆነም የስልጣን ማንነታቸው ምሶሶ ለህወሓት ያላቸው ታማኝነት እንጂ የአማራ ብሄርተኝነት አይደለም:: የብሄርተኝነት መገለጫዎች የበላይነት ስነልቦና ፣ የታሪክ ማጋነን፣ የግዛት ማስፋፋት፣ የተጠቂነት  ትረካን ናቸው:: እነዚህ እሴቶች “እኛ” እና “እነሱ”፣ ወዳጅና ጠላት የሚለውን አጥር ይስራሉ:: ስለሆነም የ”አኛ” ቅርጫት ውስጥ ያለው በጭፍንነት የምታደርገውን ሁሉ ይደግፋል፣ ”እነሱ” ቅርጫት ውስጥ ያለውን በጠላትነት፣ በጥርጣሬ ይመለከታል። ይህ የህውሃት አርባ ዓመት አካሄድ ሲሆን አብዛኛው የግራይን ወጣት እና ምሁራን በከሏል::
ብአዴን በዚህ ሲለካ ባዶ ነው። መሪዎቹም፣ ተከታዮቹም፣ አብዛኛው ካድሬዎችም ብሄርተኞች አልነበሩም:: ግን ሰው በመሆናቸው ራሳቸውን መከላከል ተፈጥሯዊ ግዴታቸው ሊሆን ይገባ ነበር:: የዛሬ ዓመት በጎንደር እና በጎጃም የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ተከትሎ የትግራይ ብሄርተኞች በብአዴን ላይ ከፍተኛ ቅስቀሳ በቀጣይነት እያኬያሄዱ ነው። አሁን አሁን የቅስቀሳው ስፋት እና ጥልቀት ህወሓት በማንፈስቶው ያስቀመጠው ታሪካዊ ተጠቂነት ትረካ ደረጃ ላይ የደረሰ ይመስላል። በመሆኑም ይወል ይደር እንጂ ህወሓት የገዛ ፍጡሩን ብአዴንን እንደገና ሊጠፈጥፈው መሆኑ ግልጽ ነው::
አመላካች ከሆኑት ክስተቶች አንዱ አሁን አሁን የአገሪቱ ችግሩ በሙሉ የብአዴን በ”ትምክህት” አስተሳሰብ መበከል ውጤት መሆኑ በህውሃት መዳፍ ስር በሚገኙት ሚድያዎች (EBC፣ ፋና፣ ዛሚ፣ ENN፣  Reporter፣ ሰንደቅ) እና በማህበራዊ ሚድያዎች እየተነገረ ነው።

ሙስና ብአዴን፣ መልካም አስተዳደር ብአዴን፣ የ”ጥልቅ ተሃድሶ” አዝጋሚነት ብአዴን፣ ሕዝባዊ አመጽ ብአዴን  ወዘተ  ሁሉም ነገር የብአዴን ችግር።
ሰሜን ጎንደር ውስጥ ስር እየሰደደ ያለው የመሳሪያ ታግል የብአዴን ቸልተኝነት፣ የወልቅይት ማንነት ጥያቄ የብአዴን ትምክህተኝነት፣ የኮሎኔል ደመቀ ጀግንነት የብአዴን አመራር ከጸረ ስርዓቱ ጋር ተባባሪነት ተደርገው እየተነገሩ ነው::
አሁን ደግሞ በጠራራ ጸሃይ በባህር ዳር በአልሞ ተኳሽ የተገደሉ ወጣቶች የብአዴን ሰለባዎች ተደርገው እየቀረቡ ነው። በህወሃት ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ ነን በሚሉ የትግራይ ተወላጆች  ለምሳሌ አስራት አብርሃም፣ አብርሃ ደስታ ወዘተ።
ይህ ሁሉ እየሆነ ለምንድነው ብአዴን ዝምታን የመረጠው? ድርጅቱ/መሪዎቹ ብይናገር/ሩ  አገር ቤትም ውጭም ያሉ ደገፊዎቹ ለምን መልስ አይሰጡም? የብአዴን ምሁራንስ ለምና ዝም አሉ? እውንስ ብአዴን ብሔርተኛ ቢሆን ይህን ሁሉ ጥቃት በዝምታ ያልፈዋል? ብአዴን ነጻ ድርጅት ቢሆን ኖሮ የሚደርደርበትን ወንጀል አይከላከልም?
የነዚህ ጥያቄዎች መልስ በብአዴን ውስጥ እውነተኛ ኢትዮጵያውያን እንደአሉ እውቅና ሰጥተን የሚቀጥለው ግንዛቤ መድረስ እንገደዳለን::
ብአዴን ብሔርተኛ አይደልም፣ ብአዴን የአማራ ድርጅት አይደለም፣ ብአዴን ነጻ አይደልም፣ ብአዴን ራዕይ የለውም። ብአዴን በህወሓት የተጸነሰ፣ በህወሓት የሚያስብ፣ በህወሓት የሚተኩስ፣ በህወሓት የሚወጣ፣ በህወሓት የሚወርድ የደካማ ግለሰቦች ይዞታ ነው:: ብአዴን አማራ ክልልን አይገዛም፣ ኦህዴድ ኦርምያን አይገዛም፣ ኢህአዴግ ኢትዮጵያን አይገዛም።
የሁሉም ገዢ ህወሓት ነው:: ህውሃት ሲሸነፍ፣ ብአዴን፣ ኦህዴድ ወዘተ ይሸነፋሉ:: ስለዚህ ሁሉም አይኖች ወደ ህወሓት!!

Monday, August 7, 2017

ባህርዳር የቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማው በተሳካ ሁኔታ ተጀመረ | ንግድ ሱቆች ዝግ ናቸው | የከፈተ እርምጃ ይወሰድበታል እየተባለ ነው source zehabesha


(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት መንግስት የዛሬ ዓመት ነሐሴ 1 የገደላቸውን ከ50 በላይ ንጹሃን የባህርዳር ነዋሪዎችን ለማሰብ በዛሬው ዕለት የተጠራው ከቤት ያለመውጣት አድማ በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ መጀመሩን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ::
የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከባህርዳር እንደገለጹት ሕዝብ ቤቱ ቁጭ ያለ ሲሆን ዛሬ በአድማ እንደሚውል ገልጸዋል:: ሱቆቻቸውን አንዳንዶች ከፍተው የነበረ ቢሆንም ማስጠንቀቂያ ሲደርሳቸው ወዲያው ዘግተው እንደሄዱም ከባህርዳር የመጣልን መረጃ ይጠቁማል::

Wednesday, August 2, 2017

ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን ወደ ኋላ በካቴና ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ source abbay media

ታዋቂው ፖለቲከኛና የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን ወደ ኋላ በካቴና ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ።
በዘረፋ የታሰሩ እንዲሁም ነፍስ ያጠፉ ግለሰቦች ላይ የማይፈጸም ድርጊት ዶክተር መራራ ላይ መከሰቱ አነጋጋሪ ሆኗል።
ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን ወደ ኋላ በካቴና ታስረው ፍርድ ቤት የማቅረቡ ርምጃ እሳቸውን በማዋረድ የደጋፊዎቻቸውን ቅስም ለመስበር ነው የሚለው የበርካቶች እምነት ነው። ርምጃው ደግሞ ቁጣን የሚቀሰቅስ መሆኑን የፖለቲካ ምሁራን ይናገራሉ።
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ሚና ይዘው የቆዩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፕሬዝዳንት ዶክተር መራራ ጉዲና በአውሮፓ ሕብረት ግብዣ ቤልጂየም ብራስልስ መገኘታቸውን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጥሰሃል በሚል መታሰራቸው ሲታወስ ቆይቶ ክሱ ወደ አሸባሪነት መለወጡ ይታወቃል።
ከሩብ ክፍለ ዘመን በላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያስተማሩትና ከዛሬ 40 አመት በፊት ጀምሮ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትግል ውስጥ ተሳታፊና የለውጥና የመብት አቀንቃኝ የሆኑት ዶክተር መራራ ጉዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያለጊዜያቸው በጡረታ እንዲወጡ ያደረጋቸው ሲሆን አስፈላጊውን መመዘኛ አሟልተው የፕሮፌሰርነት ማእረግ እንደተነፈጉም ለኢሳት መግለጻቸው ይታወሳል።
ለረዥም ጊዜ ከኖሩበት ቤት መባረራቸውንም ተከትሎ አዲስ አበባ ጫፍ ላይ ተጀምሮ ወዳላለቀ ቤት መግባታቸውን ማስታውስ ተችሏል።
ዶክተር መራራ ጉዲና ሁለት እጃቸውን በካቴና ወደኋላ ታስረው ፍርድ ቤት የቀረቡት ዛሬ ማክሰኞ ሐምሌ 25/2009 እንደሆነም ታውቋል።
በነፍስ ማጥፋት፣በዘረፋ፣እንዲሁም በተራ ስርቆትም ሆነ በሌላ ወንጀል እንዲሁም በፖለቲካ ጭምር የታሰሩ በአብዛኛው በካቴና በማይታሰሩበት ሁኔታ እኚህን ታዋቂ ምሁርና ፖለቲከኛ በካቴና አስረው ፍርድ ቤት ያቀረቡበት ምክንያት አልታወቀም።

የአማራው ነገድ ኢትዮጵያዊ ብኩርናው ላይ መቼም ቢሆን አይደራደርም! [በወንድወሰን ተክሉ] source abbay media

ለዶ/ር አቤል ዮሴፍ መልስ የተጻፈ
[በወንድወሰን ተክሉ]
ውድ የአማራው ነገድ ሆይ ከአይሁዶቹ ታሪክ የምንማረውን እና የማንማረውን ለይተን እንወቅ
**አንድ- የዶ/ሩ የወቅቱ የነገደ አማራ አደረጃጀት ንጽጽር ከጀርመኖቹ አይሁዶች ጋር ያቀሩቡት ተወራራሽነት እና ተያያዥነት በሌላቸው ጉዳዮች የመሆኑ ፋላሲ።
በቅድመ ሁለተኛው ዓለም ጦርነት በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ያሉ አይሁዳውያን በ1880ዎቹ መገባደጃ ላይ በአሜሪካዊው አይሁድ ሄርዝል የተቃቃመውን ዓለም አቀፍ የአይሁዳውያንን ማህበር በሁለተናዊ መልኩ ከመቀላቀልና እና ተደራጅተው ከመታገል ይልቅ ከአምስት እስከ አስር ትውልዳቸው በተወለደበት “ሀገራቸው” ሆላንድ፣ሩሲያ፣ፈረንሳይ..ወዘተ ይበልጥ ይሰማቸው ነበርና ድጋፋቸው እጅግ ውስን ወይም ከእነ አካቴውም ገለልተኛ ሆኖ ይታይ እንደነበረ ግልጽ ነው።
የናዚው ሂትለር ሰይፍ ይህንን ቸልተኝነት፣ዳተኝነትና ገለልተኝነትን ጠራርጎ ሊያጠፋባቸው ያስቻለን ሁሉን አቀፍ ጥቃት/ፍጅት/በማንነታቸው ላይ ያነጣጠረ በመፈጸሙ ሁሉም አስበውትና አምነውበት የማያውቁትን የጽዮናዊነትን መንፈስና እምነት እንዲላበሱ በማድረግ በ1948 ለተቃቃመችው አይሁዳዊታ የእስራኤል ሀገር መመስረት የማእዘን ድንጋይ ሚናን በመጫወት ታላቅ ተጋድሎና መስዋትነትን ሊከፍሉ ችለዋል።
ይህ የእነሱ ታሪክ ነው።የአማራው ወቅታዊም ሆነ የወደፊት ህልውናዊ እጣፈንታው ከአውሮፓውያኑ አይሁዶች ቅድመ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጋር አንዳችም አይነት ተዛማችነትን የምንይበት ክስተት ስለመኖሩ ያየነውና የኖርነው ነገር እንደሌለ የገሃድ እውነታ ነው። አይሁዶቹ ከሁሉም በላይ ጭፍጨፋውና ጥቃቱ [In Human Discrimination ]የተፈጸመባቸው የራሳቸው በሆነው ምድር/ሀገር ሳይሆን እንደ መጤ በሚቆጥራቸው የሰው ሀገር ሲሆን በቅድመ ጭፍጨፋው ከአይሁድነታቸው ይልቅ ጀርመናዊነታቸውን፣ሆላንዳዊነታቸውን፣ፈረንሳዊነታቸውን..ወዘተ ይበልጥ የመረጡበት ሁኔታ ከአምስትና ከዚያ በላይ ትውልድ በተወለደበት ሀገር የዜግነት እና የሀገራዊ ብሔርተኝነት ስሜታቸው ማየሉ ሳይሆን ጥፋት የሚሆነው ያንን ስሜትና እምነት ባይኖራቸው ነበር እንደጥፋት የሚቆጠረው።
አይሁዶቹ በየሀገራቱ እንደዜጋ ሳይሆን እንደመጤ በዝባዥና ዘራፊ ተደርገው ታዩና ለጥቃት ተጋለጡ።በማን ሀገር? በ”ሰው” ሀገርና ምድር ማለት ነው።መገለሉ መጠቃቱና እንደመጤ መታየቱ በጀርመን ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን እንደየ ደረጃው በተበተኑበት ምድር ሁሉ የተፈጸመ ነበር።
የነገደ አማራው ታሪክ ከአይሁዳውያን ታሪክ ጋር ተመሳሳይ ክስተት ተፈጽሞበታልን?
በፍጹም።ምንም የሚያመሳስለን ክስተት በታሪካችንም ሆነ በአሁኑ ሰዓትም አልተፈጸመብንም-ሊፈጸምብንም አይችልም።
በእርግጥ ነገደ አማራ ህልውና ላለፉት 40ዓመታት በጥቃት ስር ያለ ነገድ ሲሆን የጥቃቱ መጠን እና ይዘት በዘመነ ህዋታውያን አድጎና ተለውጦ ለህልውናው መጥፋት ስጋት ደረጃ መድረሱ እውነት ነው።
ማንም ሊያስተባብለው የማይቻለው እውነታ የነገደ አማራ ህልውና በከፍተኛ አደጋ ላይ የመገኘቱ እውነታ ሲሆን ይህ ጥቃት እየተፈጸመ ያለው ግን እንደ አይሁዶቹ በሰው ሀገር እንደ መጤና ዘራፊ በሚያያቸው ህዝብና ስርዓት ሳይሆን አማራው ከ3400ዓመት በላይ እትብቱ በተቀበረበት የግል እርስቱና ሀገሩ ላይ በአቻ የሀገሩ ተወላጅ የመሆኑ እውነታን የተለያዩ ክስተቶች እንደሆኑ እናያለን።
አማራው በምድሩ ነው የተጠቃው-እየተጠቃም ያለው። አይሁዶቹ በመጤነታቸው በሰው ሀገር የተጠቁ ሲሆን አማራው ግን በራሱ ምድር በታሪክ ውስጥ ኢትዮጵያን በመመሰረት፣በመጠበቅ ሂደት ውስጥ ነገዱ በሀገሪቱ ውስጥ በመሰረተው ፓለቲካዊ የስልጣን የበላይነት፣የባህል፣የቃንቃ፣የኢኮኖሚ የበላይነቱን ሚናን በእጅጉ በጠሉና በቀኑበት አቻ ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ሃይሎች የተከፈተበት ጥቃት እንደሆነ እናያለን።
በኢትዮጵያዊው የአማራ ነገድ ላይ የጠላትነትን መንፈስና እምነት ምንጩ የደደቢት በረሃ ተወላጁ ህወሃት እና ህወሃት ብቻ እንደሆነ ከሁሉም በፊት በጥልቅ ልንረዳውና ልናውቀው ይገባል።
የአማራው ነገድ ከህወሃት በስተቀር በሌሎች ሃይሎች ተጠቅቶ አያውቅም እያልኩ እንዳልሆነ ከግንዛቤ ሊያዝልኝ ይገባል።ምንም እንካን የኦ.ነ.ግ ኦ.ብ.ነ.ግ እና ሻእቢያ ሃይሎች ለአማራው ነገድ ፍቅር ያላቸው ሃይሎች ናቸው የሚያስብል የጥላቻ ስሜትና ቅስቀሳን የሚያደርጉ መሆናቸውን ብናውቅም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በድርጅቱ መተዳደሪያ ፕሮግራም ላይ “ጨቃኛ የአማራ ብሔር የመደብ ጠላታችን ናት”ብሎ አርቅቆና አጽድቆ እየተንቀሳቀሰ ያለ ሃይል የመጀመሪያም ሆነ የመጨረሻውም ህወሃትና ህወሃት ብቻ እንደሆነ እናውቃለን።
ህወሃት እንደ ነገደ አማራ ኢትዮጵያዊ ነው ሃይል ነው።ግን ጸረ-አማራ ሆኖ እራሱን በአማራ ጠላትነት ያደራጀና ለመንግስትነት የበቃ ሃይል ነው። ባለው የጸረ አማራ እምነቱ እና ባለው የአናሳ ነገድ ተወላጅነቱ የተነሳ በሀገሪቱ ውስጥ ካሉት 81 ነገዶች ውስጥ በሕዝብ ብዛቱ በሁለተኛ ደረጃ ያለውን የአማራ ነገድ ተጽእኖ ብቻውን መመከት አይቻለውምና ሌሎችም ነገዶች ጸረ-አማራ እምነትና አመለካከት እንዲኖራቸው ለማድረግ ላለፉት ሁለት ዓስርተ ዓመታት ውስጥ በመንግስታዊ አቅሙ ከፍተኛ የሆነ ፕሮፖጋንዳን ዘራ። አማራውን እንደ ጨቃኝና በዝባዥ በማድረግ ከፍተኛ ቅስቀሳን አደረገ።ሌሎችንም በጸረ አማራነት አደራጅቶ አስታጠቀ ብሎም አማራውን እራሱም መትቶ በሌሎችም አስመታ። የህወሃት ጸረ-አማራ ፕሮፖጋንዳ ሰለባ በመሆን ጸረ አማራ አቃም ያሳዩና ብሎም ያራመዱም ይኖሩ ይሆናል ግን ጸረ አማራነታቸው የራስ ወለድ የሆነ ሳይሆን ህወሃት ወለድ በመሆኑ ለጠላትነታቸው መሰረት ያላቸው ሆነው አናያቸውም።
ይህ ክስተት የነገደ አማራውን ክስተት ከአውሮፓውያኑ አይሁዶች ክስተት ጋር ፈጽሞ የማይገናኝበትን ሂደት ያየንበት ነው።
**ሁለት-የአማራው ነገድ አደረጃጀት ከዚህ በፊት የተደራጁትን እንደነ የጎንደር ህብረት፣የጎጃም ህብረት፣የወሎ ህብረት፣የሸዋ ህብረት እና በኢትዮጵያዊነት ስር የተደራጁትን ሃይሎች እንደ የአማራው ጠላትና ጸረ-አማራዊ ሃይል አድርጎ የሚያይ ከሆነ መሰረት በሌለው ዓየር ላይ እራሱን ለአማራ ተቆርቃሪ ድርጅት አድርጎ የሚያይ መፍትሄ ያለው ተደራጅ ሃይል ሳይሆን በቅዥት አለም የሚቃዥ አሊያም የአማራውን እውነተኛ የመደራጀት ግብን ለማጨናገፍ የተነሳ ቅቡል ሃሳብ ነው ብዪ ለመናገር እችላለሁ።
እስቲ ከምን እሳቤና ፍልስፍና ነው ለአማራው ነገድ ተቆርቁሬያለሁ ብሎ እራሱን እያስተዋወቀ ያለ ግለሰብም በሉት ቡድን ወይም ድርጅት በጎንደር፣በወሎ፣በጎጃም፣በሸዋ ያሉትን አማሮች ከደረሰባቸው ጥቃት ለመታደግ ተደራጅተው የበኩላቸውን ታላቅ ተጋድሎን እና ድጋፍን እያበረከቱ ላሉት የጎንደር ህብረት፣የጎጃም ህብረት፣የሸዋ ህብረት እና የወሎ ህብረትን የአማራው ነገድ ጠላቶች ናቸው ለማለት የተቻለው?
ዶ/ር አቤል ዮሴፍ በሚያስደንቅ ድፍረት እነዚህን ድርጅቶች የወያኔን አላማ አስፈጻሚዎች ናቸው እስከማለት የወረደ አመለካከት አራምዳል። በእርግጥ እሱ አማራ ከሆነ ከአንድ አማራ በሌላው አማራ ላይ ሊሰነዘር የማይገባን ጸያፍ ቃላትን በመጠቀም መፍትሄ አቅራቢ ሳይሆን ልዩነትን እና ክፍፍልን ፈጣሪና አስፋፊ ሆኖብኝ ታይቶኛል።
በአስቸካይ መቆም አለበት። ራእይ አለኝ ባይ አማራ ሌላውን አማራ ካልተከተልከኝ ይሁዳ ነህ የሚል እንጭጭ ድምዳሜን ከመስጠት መቆጠብ ይጠበቅበታል።
እንደ ባለራእይነቱ ደግሞ ራእዩን በጥራትና በትጋት ማስተማር እንጂ መጫን ከቶም አይገባውም። ከሁሉ በፊት የአማራው መደራጀት በጸረ የኢትዮጵያ አንድነት ሃይሎች፣በጸረ ኢትዮጵያዊነትና ብሎም ለአማራዊው ሀገር ምስረታ ላይ መሰረት ያደረገ ከሆነ የሚካበው ድርጅት ከእንባይ ካብም የባሰ መሰረት የለሽ እንደሆነ ወደደም ጠላም ማወቅ አለበት። ዶ/ር አቤል ዮሴፍ በጎንደር ህብረት፣በአግ7 እና በኢትዮጵያን አንድነት ላይ ያላቸው የጠላትነት አመለካከትና አቃም ሎጂካል ሆኖ አላየሁትም-ምክንያታዊነት ያለው ሳይሆን ስሜታዊነትና ብሎም ግላዊ ጥቅምና ፍላጎት ላይ የተመረኮዘ እንጂ የአማራውን ነገድ ጥቅምና ፍላጎት ከግንዛቤ ውስጥ ያስገባ እንዳልሆነ ልረዳ ችያለሁ።
**ሶስተኛ-ኢትዮጵያዊው የአማራ ነገድ ከአይሁዶቹ የሚማረው እውነታ ምንድነው?
በወርሃ ግንቦት 1948 እስራኤል የተባለች የአይሁድ መራሽ መንግስት በቀድሞዋ ፍልስጥኤም በተመስረተች ማግስት የዓረብ ሀገራት በአጭሩ ለመቅጨት ከየአቅጣጫ ወረራ ፈጸሙ። አዲሲታ ሀገርም ምድራችን ብለው ያመኑበትን የከነዓንን ምድር አሳልፎ ላለመስጠት ተፋለሙ። ሁሉንም መስዋእትነትን ከፍለው ምድራችን ያሉትን የከነዓንን ምድር እስራኤል በሚል መጠሪያ የሰየሙትን ሀገር ተከላከሉ። አይሁዳውያኑ በጀርመን እና አውሮፓ እያሉ እጅግ ዘግናኝ የሆነ አሰቃቂ ጥቃት ቢደርስባቸውም እራሳቸውን ለመከላከል ያደረጉት ፍልሚያ አልነበረም። ያሉት በሰው ሀገር ነውና።
ኢትዮጵያዊው አማራ ከአቻው የኦሮሞ ነገድ እና ሌሎች ጋር የኢትዮጵያ የበኩር ነገድ የሆነ ህዝብ ነው። ኢትዮጵያን እንደ ሀገር በመገንባት ደረጃ ከ3ሺህ በላይ በፈጀው ተጋድሎና ግንባታው አማራ በታሪክ ተጽፎ ያለን ታላቅ መስዋእትነትን የከፈለበት ውድ ሀገሩ ኢትዮጵያ ነች።
ይህ ታላቅ ሚናውም እንደ ህወሃት ያሉትን ጠባብ ሃይሎች በነገዱ ላይ የመረረ ጥላቻና የጠላትነት መንፈስ እንዲያውጁ አድርጎዋቸዋል። አማራው ነገድ ልክ እስራኤላውያኑ በእርስታቸው ከነዓን ምድር እየተጋደሉና እየተማማቱ እንዳለው እሱም በኢትዮጵያዊነቱ በኢትዮጵያ ደረጃ ያለውን ሚና እና ድርሻውን ለግዜውም ቢሆን መንጠቅ ለቻለው የህወሃት ሃይል አሳልፎ በመስጠት ኖሮበትና ዓይቶትም ሆነ አልሞት የማያውቀውን የአማራ አነስተኛ ግዛት ሀገር እፈጥራለሁ ብሎ ሊማማት አይችልም -አይገባውምም።
እኛ የበኩር ልጆች ነን-ብኩርናችንን ደግሞ ልክ እንደ ኤሳው በምስር ወጥ እንደሸጠው እኛም ኢትዮጵያዊ ብኩርናችንን በአባት አማራ መሰል ክልላዊ ሀገር ልንሸጥ አንችልም-አይገባንምም።
[ይቀጥላል]

የፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ውሎ source zahabsha

 

     


የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ፕሮጀክት እንደዘገበው:  ዶ/ር መረራ ለዛሬ ሃምሌ 25/2009 ተቀጥረው የነበረው በክሱ ላይ በማስረጃ ዝርዝር የተጠቀሱ የአቃቤ ህግ ምስክሮችን ዝርዝር ለተከሳሽ (ዶ/ር መረራ) ማሳወቅን ወይም አለማሳወቅን በተመለከተ የፌደሬሽን ምክር ቤትን ምላሽ (ትርጓሜ) ለመስማት ነበር።
ሆኖም የ19ኛ ችሎት ዳኞች ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ምላሽ እንዳላገኙ በመግለፅ፤ ፌደሬሽን ምክር ቤት ለህገመንግስት አጣሪ ኮሚቴ ትርጓሜውን እንዲሰራ የላከው ደብዳቤ ግልባጭ እንደደረሳቸው ተናግረዋል።

የዶ/ር መረራ ጉዲና ጠበቃዎች የሚከተለውን ሃሳብ አንስተው ተከራክረዋል። ደንበኛችን ከታሰሩ 9ወር ሆኗቸዋል፤ የተፋጠነ ፍትህ የማግኘት መብታቸው እየተከበረ አይደለም፤ ፌደሬሽን ምክር ቤት የተላከው የትርጉም ጉዳይ ፍ/ቤቱ በራሱ የሚወስነው ነገር ስለሆነ ችሎቱ ራሱ ቢወስን፤ ተመሳሳይ ወንጀሎችን የሚያየው 4ኛ ችሎት ተመሳሳይ ጉዳዮችን ችሎቱ በራሱ ነው የሚወስነው፤ ደንበኛችን ከቆዩበት ጊዜ አንፃር፣ ከእድሜያቸው፣ ካበረከቱት አስተዋፅኦ እና ከጤናቸው አኳያ ክሳቸው በክረምትም እንዲታይ እና አጭር ቀጠሮ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

በሌላ በኩል የዶ/ር መረራ ጠበቃ ዶ/ር ያእቆብ ሃ/ማርያም፤ “የታደሰ የጥብቅና ፈቃድ እና ውክልና እያለኝ ወህኒ ቤቱ ደንበኛዬ ዶ/ር መረራን እንዳላገኝ ከልክሎኛል። ስለሆነም ፍርድ ቤቱ በህገመንግስቱ አንቀፅ 21 መሰረት ደንበኛዬን እንዳገኝ ለወህኒ ቤቱ ትእዛዝ እንዲሰጥልኝ አመለክታለሁ።” ሲሉ አቤቱታቸውን አቅርበዋል።
ዳኞችም የሚከተለውን ውሳኔ ሰጥተዋል። የምስክሮች ጥበቃ አዋጅ እና በፀረሽብር ህጉ አንቀፅ 32 ላይ የተደነገገው ህገመንግስታዊ ትርጉሙ አሻሚ መሆኑን የገለፁት ዳኞች፤ ተከሳሽ የአቃቤ ህግ ምስክሮች የመቅረብ ያለመቅረብን በተመለከተ ያቀረቡትን መቃወሚያቸውን ውድቅ ሚያደርጉ ካልሆነ በስተቀር የፌዴሬሽን ምክርቤትን ትርጓሜ መጠበቅ ግድ መሆኑን ገልፀዋል። 4ኛ ችሎት ተመሰሳሳይ ጉዳዬችን በራሱ ይሰራዋል የተባለውን ጉዳይ በተመለከተ፤ ለሌሎች ችሎቶች ገዢ የሚሆነው ሰበር ሰሚ ችሎት የሚሰጠው ውሳኔ ብቻ መሆኑን ጠቅሰዋል— ዳኞቹ። ክሱ በክረምት እንዲታይ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ የፍርድ ቤቱ የእረፍት ጊዜ በመቃረቡ እና የዛሬ አመት ክስ የተመሰረተበት መዝገብ ጉዳይ እስከ ነሃሴ 12, 2009 ስለሚያዩ፤ የእነ ዶ/ር መረራን መዝገብ በክረምት ማየት እንደማይችሉ ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት የፌዴሬሽን ምክርቤትን ምላሽ ለመጠባበቅ ለጥቅምት 6/2010 ቀጠሮ ሰጥተዋል። የጠበቃ ዶ/ር ያእቆብን አቤቱታ በተመለከተም ለቃሊቲ ማረሚያ ቤት ደንበኛቸውን እንዲያገናኟቸው ትእዛዝ እንዲወጣ ተብሏል።