Monday, May 15, 2017

በመቀሌ ተደብድበው ይቅርታ እንዲጠይቁ ታግተው የነበሩ የባህር ዳር ከነማ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች ተለቀው ጉዞ መጀመራቸው ተገለጸ




በመቀሌ ተደብድበው ይቅርታ እንዲጠይቁ ታግተው የነበሩ የባህር ዳር ከነማ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች ተለቀው ጉዞ መጀመራቸው ተገለጸ

Thursday, May 11, 2017

ኢህአዴግና ወጣቱ source mereja

የሰሞኑ የህወኃት/ኢህአዴግ ወጣቱን ማማለያ ውይይት ምን ይመስላል ? በሰሞኑ ህወኃት/ኢህአዴግ ‹ትንፋሽ› ለመውሰድ << በ ጥልቁ ተሃድሶ ወጣቱ፣ ሥራ አጥነትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ>> በሚል ከወረዳ እስከ ፌደራል ባሉት የወጣት አደረጃጀት መዋቅሮችና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተከታታይ ውይይት — ተያይዟል፡፡ በመጨረሻም በ27/08/09 ዓ.ም በተጀመረው የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን አገራዊ የውይይት መድረክ/ ጉባኤ ተጠቃሏል፡፡ ካለፈው ወር አጋማሽ ጀምሮ በመንግስት ቴሌቪዥን ካየነው ፣ በኢዜአና ኤፍኤም ሩዲዮኖች ከሰማነው የውይይቱ ዓላማ የታዘብነው በጥቅል የሚከተሉትን ያሳያል፡፡ 1. ህወኃት /ኢህአዴግ ጠያቂና ሞጋች ማኅበረሰብ ፈጠርን ባሉበት አፋቸው ዛሬም ወጣቱን የማያስብና የሚነዳ፣ ጥቅምና ጉዳቱን የማይለይ አድርጎ ፣ ዛሬም ወጣቱን ለማጭበርበር ‹በካድሬ› ወጣቶች ‹ጠያቂና ተሟጋች › ወጣት የተፈጠረ ለማስመሰል. . . እየተጣጣረ መሆኑን ፣ 2. ወጣቱ ‹በውጪ ኃይል ታዛዥ የጥፋት ኃይሎችና የቀለም አብዮት ተሳታፊ የመሆን ሥጋትና እንቅልፍ የነሳው መሆኑን፣ 3. ለሥራ አጡ ወጣት የተለመደውን ‹‹የላም አለኝ በሰማይ›› ቀለብ ለመስፈር እንጂ ለዘላቂ ለውጥ ያልተዘጋጀ መሆኑን፣ 4. ዛሬም ችግርን በሌላው ማላከክ፣ ችግራችሁ ገብቶናል ተቀብለናል፣ መዝግበናል፤ በቀጣይ በምናዘጋጀው መድረክ ኃሳባችሁን እናካትታለን በማለት የክፉ ቀን ለመሻገር የተወጠነ መሆኑን ፤ 5. እንዲሁም ዛሬም ወጣቱ ችግሩንና ጥያቄውን በህወኃት/ኢህአዴግ ዓላማ ዙሪያ ‹ብቻ› ተደራጅቶ ሲያቀርብ መፍትሄ የሚያገኝ ፣ ለራሱ መብትና ጥቅም በራሱ በነጻነት ተደራጅቶ ሊቀርብ እንደማይችል ለማስረገጥ/ለማሳመን ሲታትር፣ ታዝበናል፡፡ ትዝብታችን እናፍታታው፡፡ ሰሞነኛው ውይይት ለ25 ዓመታት ከተለመደው የውይይት መድረክ አመራር የሚለየው በአቀራረብ ብቻ ነው፡፡ በተሳታፊዎች የቀረቡትን ሁሉንም ኃሳብ በሁሉም አወያይ ‹ተቀብለናል› መባሉና የማስፈራሪያ ቃላትና ፍረጃዎች አለመኖራቸው ብቻ ሳይሆን ፣ በምሁራን አወያይነት መታጀቡ ነው ፡፡ ይህም ህወኃት /ኢህአዴግ ጭንቅ ሲለውና ብርክ ሲይዘው ከተለመደው ለየት ባለ አቀራረብ የተለወጠ/ለመለወጥ የተዘጋጀ ለማስመሰል የሚጠቀምበት ማጭበርበሪያ ስልት ነው፣ ክፉው ቀን ሲያልፍ የማያስታውሰው ፡፡ ይህ እውነት ባለበት ወደዚህ ዓይነት ትዝብት የዳረጋቸውን በውይይት መድረኩ የተነሱ አንዳንድ አብነቶችን እንመልከት፡፡ በደቡብ ቴሌቪዥን /ሚያዚያ 24 ቀን 2009/ በተለይ የብዙዎቹን ወጣቶች ኃሳብ በማጠቃለል ያቀረበውና ቀልቤን የሳበው፣ ቴሌቪዥኑም ደጋግሞ ያሳይ የነበረው አንድ ወጣት ያነሳቸውን ነጥቦች እንመልከት፡፡ ወጣቱ አገዛዙን ይህ ሁሉ ተደራራቢ ከአቅማችሁ በላይ የሆኑ ችግሮች ተከማችተው ለጥፋት ሲዳርጉ የት ነበራችሁ፣ አደጋው ከደረሰ በኋላ ፣ ልማትና ፋብሪካ ከወደመ፣ ት/ቤት ለወራት ከተዘጉ በኋላ ፣ አስቸኳይ አዋጅ 6 ወር ቆይቶ ከተራዘመ በኋላ፣…… ዛሬ ከየት መጣችሁ ? ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ፣ በተለያዩ መድረኮች በህዝብና ወጣቱ የተነሱ ጥያቄዎችና ሂሶችን ተቀብለናል ካላችሁ ለምን መፍትሄ አልሰጣችኋቸውም ነበር ? የተለየ ኃሳብ የሚያቀርበውን ወጣት በተቃዋሚነት እየፈረጃችሁ ሲታሸማቅቁ ከነበረበት ለመለወጥ የቱን ያህል ተዘጋጅታችኋል ? ተቀብለናል በማለት ያለፋችኋቸው ወይም ‹ይፈታሉ› እያላችሁ ስታዘናጉ የነበሩ ችግሮች መቼ አልተፈቱም ፣ሃሳቦችም አልተስተናገዱም በቀጣይ እንዴትና መቼ እንደሚፈቱና እንደሚስተናገዱ የትናንቱ እንደማይደገም ምን ማስተማመኛ አለ ? በማለት ወጣቶቹ ጠይቀዋል፡፡ እንደመፍትሄም የቀረቡ ኃሳቦች ሲጠቃለሉ፡- ‹‹ እዚያ በማዕከል /ፌደራል ደረጃ ተቀምጦ የሚደረስበት ውሳኔም ሆነ የሚሰራጭ ፕሮፖጋንዳ መፍትሄ አላመጣም፣ ከጥፋት አልታደገንም፡፡ ችግሩም ሆነ መፍትሄና ሥራው ያለው ታች በወረዳ ደረጃ ነው፡፡ እዚህ ብቻ ወይም በአንድ ዞንና ክልል ብቻ ሳይሆን በመላው አገሪቱ ከዳር ዳር በወረዳና ቀበሌ ወርዶ የህዝቡን ትክክለኛ ጥያቄ ሳትረዱ ከካድሬዎች የሃሰት ሪፖርት ተነስቶ የሚደረስ ማጠቃለያ ውጤትና ለውጥ አላመጣም፣ አያመጣም፡፡ እስከዛሬ ህዝቡ የሚያምናቸውን የምወዳቸውንና የሚያከብራቸውን ሳይሆን ለእናንተ ታማኝ የሆኑትን ስትሾሙና ስትሽሩ በመኖራችሁ – አሁን መንግስትና ኢህአዴግ ከህዝቡ ጋር ተራርቆ ነው ያለው ፡፡ በቀጣይ ለመልካም አስተዳደር በሉት በህዝብ ተቀባይነት ለማግኘት በህዝብ ክብር፣ ተቀባይነትና ታማኝነት ያላቸውን ቢጣሩ አቤት የሚባሉ፣ ቢሸመግሉና ቢናገሩ የሚደመጡ፣ አመራሮችን ወደፊት አምጡ እንጂ የተለመደው መንገዳችሁ መፍትሄ አያመጣም፡፡ ዩኒቨርሰቲዎችን ት/ቤቶችን ተከትለው ጫትና ሺሻ ቤት፣ የምሽት ክለብ፣ ፑል ቤት ….. በዩኒቨርስቲና ሁለተኛ ት/ቤቶች ዙሪያ እየተስፋፉ ተማሪውን/ወጣቱን ለሱስና አደንዛዥ እጾች አጋልጠው ሲያደነዝዙና ከትምህርት ገበታው ሲያርቁ የመከላከል እርምጃ ሳትወስዱ፣ ስለወጣቱ ባህሪይ መበላሸት ፣ የሥራ ፈጣሪነት መላሸቅና የትምህርት ጥራት፣ የተመራቂዎች ልቀትና ተወዳዳሪነት መውደቅ …. ስትናገሩ እስከዛሬ በህዝቡ ውስጥ አልነበራችሁም እንደማለት ነውና ወጣቱን /ተማሪውን ከነዚህ ዓይነት የጥፋት ድጊቶች ተጋላጭነት የመከላከል የማያዳግም እርምጃ መውሰድ እንጂ ችግሩን መዘርዘር አያዋጣምና በቀጣይ አስቡበት፡፡ ከዚህ በፊት ከህወኃት/ኢህአዴግ የተለየ ኃሳብ የሚያቀርበውን ወጣት በተቃዋሚነት እየፈረጃችሁ በግልጽና ተዘዋዋሪ መንገድ ስትቀጡ የመኖራችሁ ሃቅ ከዚህ ህዝባዊ እምቢተኝነት አድርሷችኋል ፤ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅና ማራዘም አስከትሏል ፡፡ አሁንም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተጠቅማችሁ ትክክለኛ የችግሩን መንሥኤ ከሥረ መሰረቱ ለመረዳትና ዘላቂ መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ ችግሩን ወደሌላ ውጪ ኃይል በማላከክ ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ለማፈን ነው የምትሞክሩት ፣ አሁን ዬሚያስፈልገው ለጥያቄዎቹ የፕሮፖጋንዳ መልስ ሳይሆን ዘላቂ መፍትሄ ነውና ከተለመደው መንገድ ውጪ ካላሰባችሁ የተለየ ውጤት አትጠብቁ፤ የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም እንደሚጠናቀቅ ፣ ዘላቂ መፍትሄ ካልተበጀ የተጀመረው ህዝባዊ እምቢተኝነት እንደሚቀጥል አትጠራጠሩ፡፡ ›› የሚሉ ናቸው፡፡ በዚህ ላይ የወጣቱን ተስፋ የማጣት ስሜት የሚያረጋግጡና በአስገዳጅ ሁኔታ ውስጣ ሆኖም ከየስደት አገራት ወደአገር ቤት ላለመመለስ ከሚያሰማው ውሳኔ ውስጥ ወጣቱ በአገሩ ‹ሰው ለመሆን› ላለመቻሉ የደረሰበትን ድምዳሜና ፣ በግዳጅ ቢመለስም ባየውና ባለፈበት ከሞት ጋር ግንባር ለግንባር የሚያጋፍጥ ሁኔታ ውስጥ ዳግም ለስደት መዳረጉን አስታውሰን ወደ ቀጣዩ ክፍል እንሸጋገር ፡፡ በአወያዮች / የወጣቶች ፌደሬሽን ተወካይ ፣የኢህአዴግ የከተማና ገጠር ፖለቲካ አደራጆችና ‹ምሁራን. / የቀረበው ምላሽን ስንመለከት ደግሞ የሚከተለውን ሥዕል እናገኛለን ፡፡ የወጣቶች ፌደሬሽን ተወካዮች በአብዛኛዎቹ መድረኮች ተመሳሳይ ‹‹ ወጣቱን ከጠላት ኃይል ተጋላጭነትና የቀለም አብዮት አራማጅነት ለመከላከልና ለመመከት ብቻ ሣይሆን የልማትና ዲምክራሲና መብት ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በዘላቂነት በተጨባጭ ለማረጋገጥ ምሁራንን በመጠቀም/በማሳተፍ ስለህገመንግስት ሰነድ እናዘጋጃለን፣ ወጣቱን የሚያካትትና ተጠቃሚነቱን በተጨባጭ የሚያረጋግጥ የልማት ፖሊሲ እናዘጋጃለን፣ የወጣቱን ሃሳብ ለመፍትሄው ግብዓትነት እንጠቀማለን፣ ለዚህም ተከታታይና ቀጣይነት ያለው የምክክር መድረክ እናዘጋጃለን ፣ እናወያያለን … ፡፡ ›› በማለት ምላሽ የሰጡ ሲሆን ይህም መልስ እንጂ መፍትሄ ካለመሆኑም ከህወኃት/ ኢህአዴግ ፈቃድ/ይሁንታ ውጪ በወጣቱ ፌዴሬሽን ስላለው/ ስለፈለገ ተፈጻሚነቱ አጠያያቂ ነው ፡፡ ለዚህ ደግሞ በደቡብ ክልል በተደረገው ውይይት ምሁሩ አወያይ የዲላ ዩኒቨርስቲ ም/ፕሬዝዳንት — ወጣቶች ከገለጹት ችግሮች በተቃራኒ ‹‹ ለዲሞክራሲና መልካም አስተዳደር የቆረጠ ፣ በውጪ ለሚታዘዝ የጠላት ኃይልና የቀለም አብዮት አራማጆች የማይነበረከክ….. መንግስት አለን፡፡ ›› በማለት ያቀረቡት መወድሰ-መንግስት ህወኃት/ኢህአዴግ መድረኩን ለምን እንዳዘጋጀው የሚያመለክት ብቻ ሳይሆን የወጣቶች ፌደሬሽን ምሁራንን አሳትፈን/ተጠቅመን የተለያዩ የወጣቱን መብትና ጥቅም የሚያረጋግጡ ‹ሰነዶች› ይዘጋጃሉ ያሉን እኒህ ዓይነቶቹን ‹ምሁራን › ከሆነ የሰነዶቹን ይዘት ምን ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ ያሳያል ፡፡ በተጨማሪ ፕ/ት ዶ/ር ሙላቱ ተሸመ ደግሞ እንዲህ ይሉናል ( ኢቢሲ 27/08/09) ‹‹ ……የተጀመረው ህዳሴ በአስተማማኝ መሰረት ላይ እንዲቆም የኢትዮጵያ ወጣቶች ፈዴሬሽን ድርሻ የጎላ ነው›› ፡፡ ልብ አድርጉ የተባለው የኢትዮጵያ ወጣቶች ፈዴሬሽን እንጂ የኢትዮጵያ ወጣቶች አይደለም፤ ስለዚህ ወጣቱ የጎላ ድርሻ እንዲኖረው በኢህአዴግ ሥር መደራጀት አለበት ወይም በኢህአዴግ ፌደሬሽን አልደራጀም ያለ ወጣት ብልጭ ብሎ በህወኃት ድርግም እንደተደረገው እንደትናንቱ ‹‹የባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር›› በነጻ ተደራጅቶ ድርሻውን ማበርከት አይችልም ማለት ነው፡፡ ይህ በመንግስት ለወጣቱ የተቀመጠለት አቅጣጫ የት እንደሚያደርስ በጊዜ ውስጥ የምናየው ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ ከሰሞኑ ከወጣቱ ጋር ከተደረጉ የውይይት መድረኮች የታዘብነውና አዋጪና ዘላቂው መፍትሄ ሲጠቃለል ፡- በ26 የህወኃት/ኢህአዴግ የአገዛዝ ዘመናት ወጣቱ ከዲሞክራሲው ሥርጸት፣ ከባለሁለት ዲጂቱ ዕድገት፣ ከዕውቀት በረከትና የፖለቲካ ሰበካው ሣይሆን ከኑሮውና ከተለመደው ‹‹ ላም አለህ በሰማይ ›› የፕሮፖጋንዳ የተስፋ ዳቦ ( ከሥራ አጥ ወጣቶች ቁጥር አንጻር በወጣት ከመቶ ብር ከማያልፈው 10 ቢሊየን ብር መመደብ ጨምሮ ) በተቃራኒ በተጨባጭ በህይወቱ ካገኘው ተሞክሮ ከጠያቂና ሞጋችነት አልፎ ወደ ‹አብዮታዊ ታጋይነት › ተሸጋግሯል፡፡ የተለመደውን የህወኃት ፕሮፖጋንዳና እየተራመደ ያለው የዘር ፖለቲካና የከሸፈ አመራር ፣ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ … ‹በቃኝ› ብሏል፡፡ ከዚህ በኋላ በህይወቱ በቀጣይነት በማይጨብጠው የተስፋ ዳቦ አስገማጭ ዕቅድ/ፖሊሲና በቴሌቪዥንና የፕሮፖጋንዳ መድረኮች በሚቀርብለት ‹ብፌ› እንዲሁም በየስብሰባው በሚቀርብለት የ50 ብር አበል፣ ቁራጭ ማስታወሻ፣ ምሳ፣ የታሸገ ውሃና ኩኪስ ሊታለል እንደማይችል እንረዳለን ፡፡ በመሆኑም ዘላቂ መፍትሄው ደጋግመን እንዳልነው የቁጩ ‹‹ጥልቅ ተሃድሶና ድርድር›› ሥም የሚከናወን የፕሮፖጋንዳ ውይይት ገለመሌ አይደለም፤ ብቸኛውና ዘላቂው መፍትሄ የወጣቱ መብትና ፍላጎት በወጣቱ የሚንጸባረቅበት በአገሪቱ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ የፖለቲካ ሃይሎች፣ የማኅበረሰብ ነጻ አደረጃጀቶችና የህዝብ ተወካዮችን በሙሉ አካታች – አሳታፊ የብሄራዊ መግባባትና ዕርቅ መድረክ መክሮና ዘክሮ የሽግግር መንግሥት መመስረት ›› መሆኑን እንረዳለን፡፡ ግርማ በቀለ ወ/ዮኃንስ፡፡ ግንቦት 02/2009 ዓ.ም›




ቴዲ አፍሮ ከኢትዮኒውስፍላሽ እና ኤፒ ሪፖርተር ኤልያስ መሰረት ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅ source zhabesha

ቴዲ አፍሮ ከኢትዮኒውስፍላሽ እና ኤፒ ሪፖርተር ኤልያስ መሰረት ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅ

ጥያቄ: የአዲሱ ‘ኢትዮጵያ’ አልበምህ ዋና መሰረት እና ለመዳሰስ የሚሞክራቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ምንድን ናቸው?
ቴዲ: አርእስቱ ‘ኢትዮጵያ’ እንደመሆኑ መጠን ዋናው አላማ ኢትዮጵያዊነትን ከአደጋ ማዳን ነው። ይህ አልበም በዚህ አይነት ሀሳብ ላይ እንዲያተኩር የፈለግኩበት ምክንያት አንድነታችን አስፈላጊ ስለሆነ ነው። ብዙ አመት ተደክሞበታል። አሁን እንደሚታወቀው በሀሳብ ከመደራጀት ይልቅ በዘር መደራጀት ይታያል። ያ ደግሞ አዝማሚያው ወደ አደጋ ያመጣው ይመስላል። እና ከምንም በላይ ኢትዮጵያዊነትን ማዳን አላማ አድርጎ ነው የተሰራው።
ጥያቄ: እንዳልከው አንዳንዶቹ ስራዎችህ በኢትዮጵያውያዊነት እና በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ያጠነጥናሉ። እዚህ ላይ በጣም ትኩረት ለማረግ የፈለግክበት የተለየ ምክንያት ምንድን ነው?
ቴዲ: አገር እንግዲህ ብዙ ግዜ የሚቆመው ለሀገር ባለውለታ በሆኑ ሰዎች እና ብዙ የህብረተሰቡ አካላት በሚሰሯቸው ተግባራት ነው። እንደሚታወቀው ኢትዮጵያዊነት በነፃነት የመኖር ምልክት ነው። ድል ለማግኘት ምኒሊክን የመሰለ ጥሩ መሪ ያስፈልጋል። እንደገና ደግሞ እንደ ሀይለስላሴ ያሉ ትላልቅ ነገስታት ከአለም መንግስታት ጉባኤ ጀምሮ ያደረጓቸው አስተዋፆዎች እና የነበራቸው ተቀባይነት፣ ለሀገራቸው የሰሩት ተግባር ሳይደመር ኢትዮጵያ የምንላት ሀገር ልትኖር አትችልም። ይህ እንዳለ ሆኖ ምንግዜም ነገስታት የሚወክሉት ህዝብን እንደመሆኑ መጠን ከስሮቻቸው ደግሞ ያሉ ብዙ ባለውለታዎቻችንን እብሮ ለማየት የሚያስችል ትልቁ መስኮት ከፊት ያሉት ሰዎች ናቸው። በዚህ መሰረት ምልክቶች ካልተበረታቱ እና የሚገባቸውን ክብር ካላገኙ የሚቀጥለው ትውልድ ጥሩ ተግባር ለመፈፀም የሚያነቃቃ መሳርያ አያገኝም። ሁለተኛ ደግሞ ባለፉት ጥቂት አመታት ታሪክ የሚባለው ነገር እና ብሄራዊ ስሜት በብዙ ሁኔታ ፈተና ውስጥ ወድቋል። ስለዚህን ይሄንን አጠናክሮ ያለውን ክፍተት ለመሙላት የትውልድ እንቅስቃሴ ያስፈልጋል። እኔ ደግሞ የዚህ ትውልድ አካል እንደመሆኔ መጠን ያንን ተግባር ለመፈፀም ነው የሞከርኩት። አፄ ቴዎድሮስ ደግሞ እንደሚታወቀው በአንድ ወቅት ዘመነ መሳፍንት በሚባለው እና ኢትዮጵያ በጎሳ መሪዎች እና በጎበዝ አለቆች ተከፋፍላ በነበረችበት ወቅት ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ ህልም ይዞ ተነስቶ ከውጪ ብቻ ሳይሆን ከውስጥም በገጠመው ብዙ የመረዳት ችግር ባክኖ የወደቀ ትልቅ ጀግና ነው። ከምንግዜውም በላይ ደግሞ የእርሱ መንፈስ አሁን አስፈላጊ ነው ብዬ አምናለሁ ምክንያቱም አስተሳሰባችን አገር ማከል አለበት።
ጥያቄ: በርካታ ሰዎች አዲሱ አልበምህ ምናልባትም ኢትዮጵያ ውስጥ ከተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች በብዙ ረገድ የገዘፈ እና በሽያጭ ረገድም ሪከርድ የሰበረ ነው ይላሉ። ምን ያህል አልበም ታተመ እና ተሸጠ? አንተስ ይህንን ያህል ተቀባይነት ገምተህ ነበር?
ቴዲ: እውነት ለመናገር ከተለመደው ውጪ ይመስላል። ምን ያክል ኮፒ እንደተሸጠ ግን ለመግለፅ የሚችሉት አሳታሚዎቹ ናቸው። እና ስራው ወደ 600,000 ኮፒ አካባቢ ታትሞ እንደነበር አውቃለሁ። ይሁንና አሁን ያለውን ያክል ተቀባይነት ያገኛል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር።
ጥያቄ: ሁላችንም እንደምናውቀው ኢትዮጵያ በአሁን ሰአት ለየት ባለ የፖለቲካ ሁኔታ ላይ ትገኛለች። ብዙ ሰዎች ደግሞ ቴዲ አፍሮ በቀደምትም ይሁን በአሁን ስራዎቹ የፖለቲካ መልእክቶችን አስተላልፏል ይላሉ። በስራዎችህ ላይ እነዚህን መልእክቶች አስተላልፈሀል? ከሆነስ እነዛ መልእክቶች ምንድን ናቸው?
ቴዲ: በኔ እምነት ብቻም ሳይሆን አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ማንም ሰው ከፖለቲካ ውጪ ሊሆን አይችልም። የፖለቲካዊ ጉዳይን ማንሳት ደግሞ እንደ ኩነኔ የሚታይ ነገር መሆን የለበትም። ሁላችንም ጉዞአችን አንድ እንደመሆኑ መጠን የኢኮኖሚያዊም ሆነ ፖለቲካዊ ጉዳይ እንደ ዜጋ ይመለከተናል። በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ማተኮር መለመድ እና መበረታታት አለበት። የነገሮቹ ጥልቀት በአልበሙ ላይ በዝርዝር ተጠቅሰዋል።
…ይቀጥላል

Tuesday, May 9, 2017

የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ገበሬዎች የተገፈፉትን መሣሪያ አስመለሱ

ከሙሉቀን ተስፋው
በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ መልካ ጅሎ አሞራ ቤት በተባለው አካባቢ የአገዛዙ ወታደሮች ሚያዚያ 16 ቀን 2009 ዓ.ም በአልታሰበ ሰዐት መጥተው 27 የክላሽንኮፍ መሣሪያዎችን መግፈፋቸው የሚታወስ ነው፡፡ የመሣሪያ ገፈፋው ከፍተኛ የሆነ የገበሬዎችን ቁጣ ቀስቅሶ ገበሬዎቹ ለወረዳው አስተዳደርና ለኮማንድ ፖስቱ መሣሪያቸው በአስቸኳይ ካልተመለሰ እርምጃ እንደሚወስዱ ከአስጠነቀቁ በኋላ የወረዳው አስተዳዳሪዎች አፋጣኝ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
በሽማግሌዎች ድርድር ከተደረገ በኋላ ሃያ ሰባቱም ክላሽንኮፎች ሚያዚያ 27 ቀን 2009 ዓ.ም. ተመልሰውላቸዋል፡፡ ከተወሰደው ጥይት የጎደለ ስለነበር ከ600 ብር ካሣ ጋር ተቀብለናል ብለውናል፡፡

* የስልክዎ ባትሪ ቶሎ እያለቀ ተቸግረዋል? – መፍትሄውን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ቴዎድሮስ አድሃኖም እና የጎደለው ብር… ለማየት እዚህ ይጫኑ

* የሁለቱ ጀነራሎች ወግ… ለማየት እዚህይጫኑ

ፕሮፌሰር መሐመድ ጣሂሮ ስለቴድሮስ አድሃኖም – “የጠፋው ብር” | ሊታይ የሚገባው በሳዲቅ አህመድ የተዘጋጀ ትንታኔ




ፕሮፌሰር መሐመድ ጣሂሮ ስለቴድሮስ አድሃኖም – “የጠፋው ብር” | ሊታይ የሚገባው በሳዲቅ አህመድ የተዘጋጀ ትንታኔ

Wednesday, May 3, 2017

በማዕከላዊ እስር ቤት በዶ/ር ጋሹ ክንዱ ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰትንና በህክምናው ላይ የተጋረጠን ሌላኛውን እሾክ በድጋሜ ስለማውገዝ፤

በማዕከላዊ እስር ቤት በዶ/ር ጋሹ ክንዱ ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰትንና  በህክምናው ላይ የተጋረጠን ሌላኛውን እሾክ በድጋሜ ስለማውገዝ፤
ከዐማራ ሀኪሞች ማኅበር Branna MediA
ዶ/ር ጋሹ ክንዱ የህክምና ዶክትሬት ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት የተመረቀ ወጣት የዐማራ ሀኪም ነው። ከተለያዩ ሀገራት የህክምናና የመሪነት ልምድን አካብቷል። ብዙ የግል ጥቅሞችን በመተው ወደሚያፈቅረው ገጠራማ የዐማራ ክፍል በመሔድ አገልግሏል። የቡሬ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ነው። የዐማራ ሃኪሞች ማኅበር ግንባር ቀደም መስራችና ፕሬዚዳንት ነው። እርዳታ በሚያስፈልጋቸው የተለያዪ የዐማራ ክፍሎች የሕክምና አገልግሎት ሰጥቷል። ጥሪ በተደረገበት ቦታ ሁሉ በአፋጣኝ በመድረስ ብዙ ህይወትን ታድጓል።  የዐማራዉን ስር ሰደድ ድህነት፣ የሕክምና እጦትና መፍትሄዎች በበርካታ የዳሰሳና የምልከታ ጥናቶች አስደግፎ ለታዳሚው የሚያስተምር ምስጉን ሀኪም ነው።  አዋጭ የጤና ፖሊሲዎችን የሚተነትን ባለራዕይ የዐማራው ተስፋ ነው።  ምክንያቱም የዐማራ ሕዝብ  የጤና ሁኔታ ከሀገራችንና ከዓለማችን ጋር ሲነጻጸር እጅግ ዝቅተኛው ነው:: በዚህ ታላቅ ነባርና ቀደምት ሕዝብ  ላይ ከባድ የበሽታ ሸክም ተንጃቦበታል፤ የጤና ሽፋን መጠኑ ከ42 በመቶ አይበልጥምና።  ባለው የደህንነት ስጋትና ቀውስ ምክንያት ዐማራው የሕክምና ባልሞያ  እንደልብ የማይገኝበት ነው።  ሁኔታውን ከባድና አሳሳቢ የሚያደርገው ሌላኛው ክስተት የህክምና ስነ-ምግባርን የጣሰ፣ ሀኪምን በእስር ቤት ማሰቃየት ነው፤  ዶ/ር ጋሹ ክንዱ ከወራት በፊት በኮማንድ ፖስት ከባህር ዳር ታፍኖ ወደ አዲስ አበባ ማዕከላዊ እስር ቤት የተወስደ መሆኑ ይታወቃል። ያለምንም ፍርድ ለ3ኛ ጊዜም ተቀጥሯል።
በራሱ አንደበት የተነገረ ና የሚታይ አካላዊና ስነ- ልቦናዊ ኢሰብዓዊነት እየተፈፀመበት ነው።  ይህ ድርጊት ከ ‘ሜዲስን ፎር ፒስ’ (MFP, Cruelty and Denial, Medical Evidence for State-Sponsored Torture in Ethiopia ) ሪፖርት የተለየ አይደለም፤ በማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ አካላዊ ማሰቃያ ስልቱ በህቡዕና በብሄራዊ ደረጃ መዋቀሩን ያትታል፤ አብዛኞቹ ምሁራን  መሆናቸውንና እስከ 52%ቱ ዐማራ በመሆናቸው ብቻ መታሰራቸውን ይገልጻል። ከ50 በመቶ በላይ ከድብደባ እስከ ‘ፋላንጋ’ ና ‘ቴሌፎኖ ‘  የማሰቃያ ዘዴዎች እንደሚደርሱባቸው የተረጋገጠ ነው።  በዶ/ር ጋሹ ክንዱ ላይ ከዚህ የተለየ እጣ ፋንታ አልተለየዉም።
ዶር ጋሹ ከላይ በተገለፀው ማንነቱ የሚታወቅ እና የዐማራው ሁለገብ የጤና ቀውስ የሚያሳስበው እንጅ ለእስራት የሚያበቃ መረጃ አልተገኘበትም። ይህ ዶክተርን ፣ ቤተሰቡንና ተገልጋዩን የሚጎዳ አፋኝ እርምጃ መሆኑን የዐማራ ሀኪሞች ያምናሉ።
ህክምና በሞያው ፀባይ የሕዝብ  መሪ ማድረጉ አሁን ላይ ለመንግስት ፖለቲካዊ ስጋት አሳድራል።  የህክምና ባለሞያን ማጥቃት መዘዙ ብዙ መሆኑ ሁልጊዜ ም መታወቅ አለበት። የሰው ልጅ በበሽታ እንዲሰቃይና ሞቱ እንዲፋጠን ምክንያት ይሆናል። ህይወትን የማዳን ሩጫው እንዲገታ ይደረጋል።  በተባበሩት መንግስታት የጸደቀውና በሁሉም የህክምና ማህበራት የሚተገበረው እኩልና የላቀ ጤና የማግኘት መብት የተጣሰ ይሆናል።  ሀገራት የዜጎቻቸውን የጤንነት ሁኔታ ለመጠበቅ ለሀኪሞች ምቹ የመስሪያ ቦታ እና አስደሳች ጥቅማጥቅሞች እንዲያመቻቹላቸው ይደነግጋል። በሀገር ደረጃም በኢትዮጵያ የህክምና ማኅበር በ 2010 የጸደቁ  የጤና ህግጋቶች አሉ፤  ማህበሩና ተከታይ ሃኪሞች የሚያከብሯቸው የቶኪዮና ጀኔቫ ስምምነቶች ናቸው። በሀኪምና ቤተሰቦቹ ላይ የሚጋረጥባቸውን ማንኛውንም ጭቆና መፍትሄና ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው ይደነግጋል።
ከላይ በተጠቀሱት መረጃወች መሰረት ዶ/ር ጋሹ የህሊና እስረኛ ብቻ ያደርገዋል። በዚህም መሰረት የሚከተሉት ህግጋቶችን በማክበር ሁሉም ሀኪምና ማህበራት የዶ/ር-ጋሹ-ክንዱን እስራትና ስቃይ በአስቸኳይ ለማስፈታት ግዴታቸውን መወጣት እንዳለባቸው የዐማራ ሀኪሞች እናምናለን።
1ኛ. በጅኔቫ የ1949 ዓ.ም አንቀጽ 6.1 መሰረት ሀኪም የህክምና ስነ ምግባርን አክብሮ እስካከመ ድረስ ማንም ይሁን ማን በምንም ምክንያት መቀጣት የለበትም።
2ኛ. የዓለም የህክምና ማኅበር የ1956; 1957 እና 1983 ዓ.ም ደንብ የሀኪም ተቀዳሚ ተግባር ሞያዊ ግዴታውን መወጣት ሲሆን፣  ህሊናውን ብቻ ተገዥ ያደርጋል፤ ይህን በማድረጉ በምንም ሁኔታ ወቀሳን ሊያመጣ አይገባም።
3ኛ. የኢትዮጵያ የህክምና ማኅበር አንቀጽ 7; 2010:  ዶክተር በሽታን ለመከላከልና ጤናን ለመገንባት የሚያስችል መረጃ መሆኑን ካመነበት ለሕብረተሰቡ ማስተማር ይችላል።
የህክምና ስነ-ምግባር መርሆችን በማክበር የሀኪምን እስራትና ስቃይ እንታደግ!
ሚያዚያ 2009 ዓ.ም
ከዐማራ ሀኪሞች ማኅበር
አዲስ አበባ