Monday, July 24, 2017

አቶ አርከበ እቁባይ ለህክምና ጀርመን መግባታቸው ተሰማ source zhabesha


(ዘ-ሐበሻ) የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከፍራንክፈርት እንደገለጹት የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ አርከበ እቁባይ ታመው ጀርመን ፍራንክፈርት በህክምና ላይ ይገኛሉ::
አቶ አርከበ እቁባይ የህመማቸው ምንነት ያልታወቀ ሲሆን ፍራንክፈርት ኤርፖርት የሚሰሩ ወገኖች በዊልቸር ሲሄዱ እንዳዩዋቸውና ህክምና ላይ እንደሚገኙ ገልጸውልናል::
አንዳንድ ምንጮች አቶ አርከበ የደረሰባቸው አደጋ ከደረጃ ወድቀው ነው ሲሉ ይናገራሉ::

Tuesday, July 18, 2017

ለመተራመስ መቸኮል ምንድነው? (ዮሃንስ ሰ. )

1. የዞረበት ዘመን…
• ተመራቂ ወጣቶች ሲበራከቱ፣ መፍራትና መጨነቅ ሳይሆን፣ ‘ብሩህ ዘመን እየመጣ ነው’ የሚል ስሜት
ሊፈጠርብን ይገባ ነበር። ግን፣ በዓመት ለ1 ሚሊዮን ወጣቶች፣ በየት በኩል ተጨማሪ የስራ እድል ይከፈት ይሆን?
2. የዞረበት አገር…
• ለተመራቂ ወጣቶች ብዙ ሺ የስራ እድል የሚፈጥሩ፣በዚህም ከአደጋ የሚያድኑን ኢንቨስትመንቶች
እንዲበራከቱና እንቅፋት እንዳይገጥማቸው ከመጣርና ከመዝመት ይልቅ፤ በኢንቨስትመንቶች ላይ እንዘምታለን።
በ1 ዓመት……
====================================
በዲግሪ ተመርቀው ስራ የሚፈልጉ ወጣቶች              120 ሺ
====================================
ከቴክኒክና ሙያ ተመርቀው ስራ የሚፈልጉ ወጣቶች     400 ሺ
====================================
10ኛ ክፍል አጠናቅቀው ስራ የሚፈልጉ ወጣቶች          500 ሺ
====================================
የተማሩ-የተመረቁ ስራ ፈላጊ ወጣቶች – የ1 ዓመት     ከ1 ሚሊዮን በላይ
===================================
ይሄ በየዓመቱ ነው። ከ10ኛ ክፍል እስከ ዲግሪ ድረስ የተማሩ 1 ሚሊዮን ወጣቶች፣ በየዓመቱ ስራ ይፈልጋሉ።
ስለ ትምህርትና ስለ ተመራቂዎች ስናወራ፣ የእውቀትን ሃያልነትና የወጣትነትን የስራ ብርታት እያሰብን ስሜታችን በብሩህ ተስፋና በጉጉት የተሞላ መሆን ነበረበት። እንዲሆን ማድረግም ይቻላል። ሕይወትን የሚያሻሽል፣ ድንቅ የብልፅግናና የስልጣኔ ለውጥ የምናመጣበት የስኬት ጎዳና ሊሆንልን ይችላል – ትክክለኛውን የመፍትሄ ሃሳብ ከጨበጥን።
አሁን ግን፣ የዞረበት ዘመን ሆነና፤… የተመራቂ ተማሪዎች ቁጥር እየጨመረ የመምጣቱን ያህል፣… ሃሳባችንም ጭንቀትና ፍርሃት ያጠላበት ሆኗል (ለማሰብ ፈቃደኛ ከሆንን ማለቴ ነው)። በአንድ በኩል፣ የስራ እድልና ተስፋ ብዙም የለም። በሌላ በኩል ደግሞ፣ የተማሩና የተመረቁ 1 ሚሊዮን ተጨማሪ ወጣቶች፣ በየዓመቱ!
መዘዞቹ፤… የስራ እጦትና የኑሮ ችግር፣ ቅሬታና ስደት፣ ቀውስና ትርምስ… ያስጨንቃሉ! ያስፈራሉ።
አዎ፤ “ምንም የተፈጠረ አዲስ ነገር የለም” ብለን ራሳችንን ለማታለል እንሞክር ይሆናል። በእርግጥም፣ የስራ እጦትና የኑሮ ችግር፣ ለዓመታት አብረውን ኖረዋል። በዓመት 100ሺ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች፣ በጂቡቲና በሶማሊያ አቅጣጫ ሲሰደዱ አይተናል – ለዚያውም በጦርነት በምትታመሰው በየመን በኩል። ቅሬታና ቀውስም ከዓመት ዓመት ሲከማች፣ ዓመፅና ትርምስም… በየጊዜው ሲፈነዳ ተመልክተናል (የአምናው አስፈሪ ቀውስ ጭምር)። ነገር ግን፣ የእስከዛሬዎቹ ቀውሶችና ትርምሶች፣ ከወደፊቱ አደጋዎች ጋር ሲነፃፀሩ፣… ኢምንት ናቸው፤ ወይም የሕፃናት ጨዋታ ቀልለው የሚታዩ ይሆናሉ።
አዲስ የተፈጠረ ነገር አለ?
እስቲ ጥቂት መረጃዎችን ልጥቀስላችሁ።
1. የቴክኒክና ሙያ
ከ10 ዓመት በፊት፣ የቴክኒክና ሙያ ተመራቂዎች ቁጥር፣ 80ሺ ገደማ ነበር።
ዛሬ፣ 400ሺ ደርሷል – በየዓመቱ።
2. የዩኒቨርስቲ ተመራቂዎች
ከ20 ዓመት በፊት፣ እስከ 1990 ዓ.ም ድረስ፣… የየዓመቱ የዩኒቨርስቲ ተመራቂዎች ቁጥር፣ ከ2500 ገደማ አይበልጥም ነበር። እስከቅርብ ጊዜ ድረስ፣ ማለትም ከዛሬ 10 ዓመት በፊት እንኳ፣ የዲግሪ ተመራቂዎች ቁጥር 7ሺ አይሞላም ነበር። በአስር ዓመት ውስጥ፣ በዲግሪ የሚመረቁት ወጣቶች ከ50 ሺ አይበልጡም ነበር።
በአማካይ በዓመት 5ሺ ያህል ማለት ነው!
ዛሬስ? በዓመት 120ሺ ወጣቶች ይመረቃሉ። ከ20 እጥፍ በላይ እንደሆነ ልብ በሉ።
3. የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች
የዛሬ 20 ዓመት ጠቅላላ የዩኒቨርስቲ የዲግሪ ተማሪዎች ቁጥር፣ 20ሺ ነበር።
ዛሬ፣ ከ1 ሚሊዮን በላይ ነው። 50 እጥፍ ማለት ነው። ታዲያ፣ ምንም አዲስ ነገር አልተፈጠረም? ተፈጥሯል እንጂ። አዎ! የትምህርቱ ጥራት ራሱ፣ በጣም አሳሳቢ መሆኑ ባንዘነጋም፣ የተማሪዎችና የተመራቂዎች ቁጥር በሃምሳ እና በሃያ እጥፍ መጨመሩን፣… እንደ ስኬት ልናየው ይችላል። ያው፤ የመማርና የማወቅ እድል ያገኘ ወጣት በርክቷል፤.. ቁጥሩ፣ በእጅጉ ጨምሯል።
ታዲያ፣ በዚያው ልክ…
“ለትምህርቴ የሚመጥን፣ ደህና የስራ እድልና የኑሮ ደረጃ ማግኘት አለብኝ” የሚል አወንታዊ ስሜት የተላበሰ ተመራቂ ወጣትም፣ ቁጥሩ በእጅጉ ጨምሯል።
ተምሮ የተመረቀው ወጣት፣ በአብዛኛው… “ይገባኛል” ብቻ ሳይሆን፤ “ይግገባኛል” ባይ ነው። “ገብቶኛል፣ አውቄያለሁ” ብቻ ሳይሆን፣ “ለኔ ተገቢ የሆነው የስራ አይነት፣ ኑሮን የሚያሻሽል መሆን ይገባዋል” የማለት ዝንባሌን፣ ወይም ‘የይገባኛል ስሜት’ን የያዘ ነው – አብዛኛው ተመራቂ ወጣት።
በሌላ አነጋገር፣ እንደድሮው፣… ነባር የድህነት ኑሮን አሜን ብሎ ለመቀበል፣… በዝምታ ለመሸከምና እንደ እጣፈንታ እድሜውን በችጋር ለመግፋት፣ ብዙም ፈቃደኛ አይደለም። ይሄ ሁሉ፣ ጥሩ ለውጥ ነው።
ችግር የሚፈጠረው፤ ኑሮን የሚያሻሽል ዘዴና የስራ እድል ሲያጣ ነው። ያኔ፣… አንዳንዱ፣ በስሜትም ሆነ በስሌት ከስደት ጎርፍ ጋር ይቀላቀላል። አንዳንዱ፣ እዚሁ ሆኖ፣ መሰናክል በበዛበትና ተዘጋግቶ መፈናፈኛ በሚያሳጣ አገር፣ የቻለውን ያህል ለመንቀሳቀስ ይፍጨረጨራል፤ ይለፋል – ሌላ ጥሩ አማራጭ በማጣት። አንዳንዱ፣ አየርባየርም እየተቅለበለበ አልያም ከስር እየተሽሎከለከና እየሰረሰረ፣ የማምታታትና የማጭበርበር አቋራጭ መንገድ ለማግኘት ይቅበዘበዛል።
ከፊሉ ተስፋ ቆርጦ፣ ይላወሳል።
ከፊሉ ደግሞ፣ በቅሬታና በእሮሮ ተወጥሮ፣ “አንዳች ለውጥ” ይመጣ እንደሆነ ለማየት፣ ግራ ቀኝ ይወራጫል፣ ፊትና ኋላ እየተፈናጠረ ይደናበራል። ያምፃል፣ ይራበሻል።
አላወቀም እንጂ፣ ‘አንዳች ለውጥ’ ለማየት እየተደናበረ ሲራበሽ፣… ረብሻ የሚናፍቁ ነውጠኞች ይመቻቸዋል። ነውጠኞቹ፣ ሰበብ አያጡም። በዘር አልያም በሃይማኖት ማቧደን፣ በአገር አልያም በብሔርብሔረሰብ መፈክር፣ በባለስልጣንነት አልያም በተቃውሞ መሪነት፣ ሰማይ ምድሩን ያምሱታል። ባለፈው ዓመት እንዳየነው፣ የዘመናችን ቀውሶች በምን ሰበብ እንደሚጀመሩ፣ በየት አቅጣጫ ተባብሰውና ተቀጣጥለው አስፈሪ ደረጃ ላይ እንደሚደርሱ ለመተንበይ አስቸጋሪ ነው። በእርግጠኝነት መናገር የምንችለው ነገር ምንድነው?
የተጠራቀመ የኑሮ ቅሬታ ሲበዛና ትክክለኛ የመፍትሄ ሃሳብ ሲታጣ፣ ቀውስ መፈጠሩ አይቀሬ ነው – ቀውሱን የሚለኩስ ሰበብ ሞልቷል።
እንደሚባባስና መያዣ መጨበጫ እንደሚያጣም፣ አያጠራጥርም። ውጥንቅጡ እየወጣ፣ በሰው ሕይወት ላይ ጉዳይ እየደረሰ፣ ብዙም ሳይቆይ ወደ አስፈሪ ትርምስነት ይንደረደራል። ትክክለኛ የመፍትሄ ሃሳብ እስካላወቅን ድረስ፣ የቀውሱ መልክ እየተዘበራረቀ አገሬውን በነውጥ ለማዳረስ ከተስፋፋ በኋላ፣ ከመንታ አማራጮች ውጭ መሄጃ መንገድ ይጠፋል። ወይ፣ በበርካታ አገራት እንዳየነው፣ ‘ምንነቱ ያልታወቀ አንዳች ለውጥ ለማምጣት’ እየተደናበርን፣ አገሬው ወደለየት ትርምስና ለዓመታት መውጫ ወደሌለው እንጦሮጦስ ይወርዳል። አልያም፣… ‘ከትርምስ አድናችኋለሁ’ የሚል መንግስት፣ ከወትሮም በላይ በጉልበት የመግነን እድል ያገኛል። ይህም በበርካታ አገራት ታይቷል። ከእያንዳንዱ ቀውስና ብጥብጥ በኋላ፣ በጉልበት መግነን የሚፈልጉ ባለስልጣናት፣ እንዳሻቸው የመሆን ተጨማሪ ስልጣን ያገኛሉ – አገርን ለማረጋጋትና ከትርምስ ለማዳን።
በእርግጥም፣ ፈላስፋዋና ደራሲዋ አየን ራንድ እንደገለፀችው፣ ትክክለኛ የመፍትሄ ሃሳብ ሲጠፋ፣ መንታዎቹ የጥፋት አቅጣጫዎች… በአንድ በኩል ወደለየለት ትርምስ የሚያመራ አመፅ፣ በሌላ በኩል እየገነነ የሚሄድ መንግስት ናቸው። ደግሞስ፣ ትክክለኛ የመፍትሄ ሃሳብ ለመያዝ ያልቻለ ሰው፣ ምን ሌላ አማራጭ አለው? ያው፣ በትርምስ ዓመፅ ስንደናበር፣ በስልጣን መግነን ለሚፈልግ መንግስት እንመቸዋለን – “አገር ለማረጋጋት፣ በስልጣን መግነን ያስፈልጋል” ይላል። መንግስት በገነነ ቁጥር ደግሞ፣ የትርምስ ዓመፅ ማቀጣጠልና አገር-ምድሩን ማደበላለቅ ለሚፈልግ ነውጠኛ ይመቸዋል – “አንዳች ለውጥ ለማምጣት እንታገል” ይላል – (ምንነቱ የማይታወቅ ‘አንዳች ለውጥ’ ማለት፣ ከትርምስ ውጭ ትርጉም ባይረውም)። የትርምስ ዓመፅና ገናና መንግስት… እነዚህ ሁለቱ፣ እርስበርስ ‘ተመጋጋቢ’ ናቸው።
ለዚህም ነው፣ መፍትሄ ሃሳብ የሌለና የማይገኝ በመሰለበት በዛሬው ግራ የተጋባ ዘመን፣ መጠኑ ቢለያይም፣ በየአህጉሩ የአለማችን አገራት እየተቃወሱ የሚገኙት። አንዳንዶቹ፣ ለይቶላቸዋል – መውጫ በሚያሳጣ ትርምስ እየተጫረሱ ናቸው (ከሶማሊያ እስከ ሶሪያ፣ ከየመን እስከ ሊቢያ ወዘተ…)። አልያም መፈናፈኛ የሚያሳጣ መንግስት ከቀን ወደ ቀን እየገነነባቸው ነው – (ከግብፅ እስከ ራሺያ፣ ከቬኔዝዌላ እስከ ፊሊፒንስ… ወዘተ)። የኛ አገር፣… ሁለቱንም የጥፋት መንገዶች እየሞካከረች፣ በየጊዜው የትርምስ ዓመፅንም እየቀመሰች፣ ከዚሁ ጎን ለጎን መንግስት እየገነነ የሚመጣበትንም ጊዜ እያየች ቆይታለች። ግን፣ ገና አልለየላትም። ይሄ፣ መፅናኛ ሊሆን ይችላል። ለጊዜ ብቻ!
ለማለት የፈለግኩትን በአጭሩ ለመግለፅ ይህንን እላለሁ፡
የኑሮ ቅሬታ በበዛበትና ትክክለኛ የመፍትሄ ሃሳብ የመያዝ ፈቃደኝነት በጠፋበት ዘመን፣… በተለይ ኢትዮጵያን በመሳሰሉ ኋላቀርና ድሃ አገራት ውስጥ፣… በነውጠኛ የትርምስ ዓመፅ እንዲሁም እየገነነ በሚሄድ መንግስት… ወደለየለት ጥፋት የመማገድ አደጋ እንደሚያጋጥም አትጠራጠሩ።
ታዲያ፣ ከዚህ አስፈሪ አደጋ ለመዳን፣ መጣጣር የለብንም?
ትክክለኛ የመፍትሄ ሃሳብ ለመጨበጥ፣ መመርመርና ማሰብ የለብንም?
እስከዚያው፣ የአደጋውን ፍጥነትና ጉዳት ለመቀነስ፣ የቻልነውን ያህል መሞከር፣… በተለይ ደግሞ፣ እስካሁን የዘረጋናቸውን መሰናክሎችና የተከልናቸው ጋሬጣዎችን በማስወገድ፣ ዜጎች ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ መንገዱን ለመክፈት መረባረብ የለብንም?
(በተቃራኒው፣ ‘የካርቦን ልቀት’ ለመከላከል በሚል አስቂኝ የተሳከረ የቅዠት ሃሳብ፣ የፋብሪካዎችና የስራ ግንባታዎች ሲታገዱ ዜና እንሰማለን – በአዲስ አበባ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አማካኝነት)።
የተማሩ ተመራቂ ወጣቶች፣… የየራሳቸውን ሕይወት በየራሳቸው ጥረት ከማሻሻል የበለጠ አንዳችም ቅዱስ ተግባር እንደሌለ እንዲገነዘቡና፣ ለስራ ፈጠራ እንዲተጉ ማነሳሳትና ማበረታታት የለብንም?
(ተማሪዎች ለስራ አለም እንዲዘጋጁ ከማድረግ ይልቅ፣ ‘የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን የሚስተካከል ቅዱስ ነገር የለም’ በሚል መፈክር፣ 8 ሚሊዮን ተማሪዎች ለወደፊት የስራ ዓለም ምንም ፋይዳ በሌለው የክረምት ስምሪት እንዲጠመዱ ‘ትልቅ’ ዘመቻ ሲካሄድ እናያለን)።
ስራ የመፍጠር ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ወጣት ተመራቂዎች፣ በጥረት አለማቸውን እንዲያሳኩ መመኘትና በነፃነት እንዲሰሩ ማበረታታት ተገቢ የመሆኑን ያህል፤… በዚያው ልክ ለተመራቂ ተማሪዎች፣ ብዙ ሺ የስራ እድል መፍጠር የሚችሉ ኢንቨስተሮችንም ማድነቅ፣ ማክበር፣ ያለመሰናክል በነፃነት የሚሰሩበት የሕግ የበላይነትን ለማስፋፋት መጣጣርስ የለብንም?
(በተቃራኒው፣ ኢንቨስተሮችንና የቢዝነስ ሰዎችን በጅምላ፣… ‘ኪራይ ሰብሳቢ’፣ ‘አጭበርባሪ’ እያልን ያለፋታ የውግዘት ዘመቻ እናካሂድባቸዋለን። ባሰኘን ጊዜ፣ የዋጋ ቁጥጥር እናውጅባቸዋለን። ባለ10 ፎቅ የቢሮ ሕንፃ የመገንባት ግዴታ ካሸከምናቸው በኋላ፣ ትንሽ ቆይተን ደግሞ፣ የቢሮና የመኖሪያ አገልግሎትን ካላቀላቀልክ፣ ህንፃ መገንባት አትችልም ብለን በድንገተኛ መመሪያ እንጠፍራቸዋለን። እንደ ስኳር ፕሮጀክት በመሳሰሉ የመንግስት ቢዝነሶች አማካኝነት በርካታ ቢሊዮን ብሮች በየዓመቱ ሲባክን ብዙም አያስጨንቀንም፤ በየዓመቱ ተጨማሪ ታክስ በኢንቨስተሮችና በነጋዴዎች ላይ መጫን ግዴታ እንደሚሆን አይገባንም። የሲሚንቶ ቢዝነስ ለዓመታት መንግስት በሞኖፖል (በጉልበት) ስለያዘው፣ ሲሚንቶ ብርቅ የነበረ ጊዜ ሩቅ አይደለም። በስድስት ወር ወረፋም አይገኝም፤ በዚያ ላይ ዋጋው ጣሪያ ሲነካ እናስታውሳለን። የሲሚንቶ እጥረት፣ በኢንቨስተሮች አማካኝነት ነው፣ ‘የድሮ ተረት’ የሆነው፤… ዋጋውም በግማሽ የቀነሰው። በዚህ ምክንያት፤ ስንትና ስንት ግንባታዎች እንደተሳኩ፣ ለስንትና ስንት ወጣቶች የስራ እድል እንደፈጠ ማሰብ ይቻላል። ታዲያ፣ እነዚህ ፋብሪካዎች ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ ማካሄድ ነበረብን? ልንዘምትባቸው ይቅርና፣ ጨርሶ በሕልማችን ዝር ማለት ነበረበት? ‘በግዴታ፣ ለወጣቶች የስራ እድል ስጡ’ በሚል ዘመቻ፣ ለወጣቶች የስራ እድልን የሚፈጥሩ ኢንቨስትመንቶችን መሸርሸር!)
ያስገርማል።
የተማሩና የተመረቁ ወጣቶች ሲበራከቱ፣ መፍራትና መጨነቅ ሳይሆን፣ ብሩህ ዘመን ይመጣል የሚል ስሜት ሊፈጠርብን ይገባ ነበር።
ለወጣቶች ብዙ ሺ የስራ እድል የሚፈጥሩና ከአደጋ የሚያድኑን ኢንቨስትመንቶች እንዲበራከቱና እንቅፋት እንዳይገጥማቸው ከመጣርና ከመዝመት ይልቅ፤ በኢንቨስትመንቶች ላይ እንዘምታለን።
ይሄ፣ ይሄ… ከአደጋው በላይ፣… ይበልጥ ያስፈራል፤ ያስጨንቃል

በኦሮሚያ ወረዳዎች የተነሳዉ ህዝባዊ የግብር ይቀነስ ጥያቄ ምላሹ ጠመንጃ ለምን ሆነ ? source zhabesha


በአንቦ፣ወሊሶ ፣በጉደር፣ጊንጪ ተገቢ ያልሆነ የንግድ ግብርን በመቃወም ህዝብ ጥያቄ ማቅረቡ ለምን ወንጀል ይሆናል? ለምንስ በጥይት ያስደበድባል?
ያልተጻፈዉ የወያኔ ህግ ብዙ ነዉ::ምንም ጥያቄ ህዝቡ ቢጠይቅ በጥይት ይደበደባል:: አስደብዳቢዎቹ ደግሞ በኦሮሞ ህዝብ ስም የኦሮሞ ብሄረተኘነትን እናራምዳለን እያሉ የሚያናፉት እነ ኦህዴድ ናቸዉ::

አንድ ጊዜ በወልመራ ወረዳ የሚኖሩ ገበሬ የኦህዴድ ካድሬዎችን እንዲህ ሲሉ አፋጠዋቸዉ ነበር::”እናንተም ገደላችሁን ወይም ትግሬም ገደለን ያዉ ለእኛ ሞት ነዉ::ኦህዴድ ለምንድን ነዉ ከኦሮሞ ህዝብ ጎን ቆሞ የኦሮሞን ህዝብ ጥያቄ የማያደምጠዉ?የወያኔን ትዕዛዝ ለመፈጸም ከምትራወጡ የህዝብ ጮህት ለምን አትሰሙም::”
ዛሬ የኝህ አርሶ አደር ጥያቄ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ነዉ::
በኢትዮጵያ ህዝብ ዉስጥ ከመቶ በላይ በብሄር የተደራጁ ፓርቲዎችን ወያኔ ቀፍቅፋለች::እነዚህ በዬብሄሩ የተደራጁ ፓርቲዎች ግን ዋና ስራቸዉ በስሙ የተደራጁትን ህዝብ ማስፈጀት እና ማሳረድ ነዉ::የወያኔም ዋናዉ ግቡ የገደለህ የራስህ ብሄር ድርጅት ነዉ ብሎ እጁን በዉሃ ታጥቦ በመጨረሻዋ ሰዓት ፊቱን አዙሮ እብስ ማለት ነዉ::
ህዝብ ከህዝብ ቢተላለቅ: ኢትዮጵያ በሳት ብትያያዝ: ብሎም አጠቃላይ የሰበአዊነት ቀዉስ በዚያች ሀገር ዉስጥ ቢፈጠር ወያኔ ግድም አይሰጠዉ::ስልጣን ላይ እስካለ አንዴ በግብር: አንዴ በኢንቨስትመንት: አንዴ በድብቅ የሚዘርፈዉን ሀብት ማግበስበሱ ብቻ ነዉ አንድ ቁጥር አላማዉ::
አምቦ የአውቶቡስ መናኸሪያ እንዲህ ተጨናንቋል::

በኦሮሚያ ወረዳዎች የተነሳዉ ህዝባዊ የግብር ይቀነስ ጥያቄ ምላሹ ጠመንጃ ለምን ሆነ ? ብለን የጠየቅን እንደሆነ መልሱ አንድ ነዉ::ከወያኔ ባህሪ የሚመነጭ ነዉ::ይሄ ጥያቄ በየትኛዉም የሀገሪቱ ክፍል ቢነሳ መልሱ ጠመንጃ ነዉ::በየትኛዉም የሀገሪቱ ወረዳ ወይም ቀበሌ እንዲህ አይነት የእዉነት ህዝባዊ ጥያቄ ከተነሳ መልሱ የሚሆነዉ ጠመንጃ ነዉ::

ለምን? ወያኔ ህዝባዊ መሰረት ስለሌለዉ ህዝባዊ ጥያቄዎችን ማስተናገድ አይችልም::ገዳይ እና አስገዳይ አድርጎ የመለመላቸዉ እና በዬብሄረሰቡ ስም ያደራጃቸዉ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ህዝባዊ መሰረት ስለሌላቸዉ የህዝቡን ጥያቄ የሚያደምጡበት ጆሮም የላቸዉም::የወያኔን ትዕዛዝ ተቀብለዉ ህዝቡን ለመግደል ግን ቁርጠኛ ናቸዉ::
በእጅጉ የሚያሳዝነዉ ደግሞ በተቃዉሞ ጎራዉ የተሰለፈዉ ሀይልም ከግል ስሜቱ እና የፖለቲካ እይታዉ ከረጢት ዉስጥ ወጥቶ በጋራ በመምከር ሀገራዊ መፍተሄ የሚያመጣ እርምጃ ላይ ላለመስማማት ያለዉ ቁርጠኛ አቋም ነዉ:: ህዝቡ ግን ብዙ ህዝባዊ ጥያቄዎች አሉት::እያንዳንዱን ህዝባዊ ጥያቄዉን ባነሳ ቁጥር ደግሞ በወያኔ የሚያስገድለዉ ነዉ::

አጠቃላይ የኢትዮጵያ ህዝብ ህዝባዊ ጥያቄ ግን በአንድ ማዕቀፍ ዉስጥ የሚፈታዉ እና ህዝቡም እፎይታ አግኝቶ ወደ ብልጽግና መገስገስ የሚችለዉ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን በእዉነት መፍጠር ከተቻለ ብቻ ነዉ:: ወደዚህ ግብ የሚሰሩ ተቃዋሚ ሀይላት እስካልተፈጠሩ ድረስ ኩነቶች ይቀጥላሉ::
ለጊዜአዉ እንኳን በጠባብ ፍላጎት አብጠዉ የሚመጡ ሀይላት አሸናፊ ቢሆኑም አስተማማኝ እና ሁል አቀፍ ህዝባዊ ምላሽ መስጠት አይችሉም::ትርምስ እና ትርምስምሱ ይቀጥላል::ህዝብ ግን ከዚህ መከራ የግድ መዳን አለበት::ኢትዮጵያ ከዚህ ሁሉ ህመም መዳን አለባት::

Thursday, July 13, 2017

ፍርድ ቤቱ በእነ ጉርሜሳ አያና መዝገብ ላይ ብይን ሰጠ • 5 ተከሳሾችን በነፃ አሰናብቷል • አቶ በቀለ ገርባ በወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ተከላከል ተብሏል source mereja.com

ፍርድ ቤቱ በእነ ጉርሜሳ አያና መዝገብ ላይ ብይን ሰጠ
• 5 ተከሳሾችን በነፃ አሰናብቷል
• አቶ በቀለ ገርባ በወንጀለኛ መቅጫ ህጉ ተከላከል ተብሏል
(በጌታቸው ሺፈራው)

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሀምሌ 6/2009 ዓ.ም በዋለው ችሎት በእነ ጉርሜሳ አያና መዝገብ በተከሰሱት 22 ተከሳሾች ላይ ብይን ሰጥቷል፡፡ ተከሳሾቹ ሁለት ክስ ቀርቦባቸው የነበር ሲሆን ከ1ኛ እስከ 13ኛ ያሉት ተከሳሾች ኦሮሚያ ውስጥ ተከስቶ በነበረው ህዝባዊ አመፅ ‹‹በቀጥታ በመሳተፍ፣ ከውጤቱም ተካፋይ ለመሆን›› የሽብርተኝነት ወንጀል ፈፅመዋል በሚል በፀረ ሽብር አዋጁ አንቀጽ 3 ስር የተደነገገውን ተላልፈዋል ተብለው ክስ ቀርቦባቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይ በሁለተኛ ክስ ከ14ኛ እስከ 22ኛ ያሉት ተከሳሾች በማንኛውም መልኩ በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ ተሳትፎ በማድረግ በሚል በፀረ ሽብር አዋጁ አንቀፅ 7(1) ስር ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ዛሬ በዋለው ችሎት በቀጥታ በሽብር ወንጀል ተሳትፈዋል ተብለው ተከሰው ከነበሩት መካከል 1ኛ ተከሳሽ ጉርሜሳ አያና፣ 2ኛ ተከሳሽ ደጀኔ ጣፋ፣ 3ኛ ተከሳሽ አዲሱ ቡላላ፣ 5ኛ ተከሳሽ አብደታ ነጋሳ፣ 6ኛ ተከሳሽ ገላና ነገራ፣ 8ኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ፣ 11ኛ ተከሳሽ በየነ ሩዳ እና 12ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ሊበን ተመስርቶባቸው ከነበረው በቀጥታ የሽብር ወንጀል መፈፀም በሽብርተኝነት ድርጅት ውስጥ መሳተፍ ወደሚል ተቀይሮ ከፀረ ሽብር አዋጁ አንቀፅ 3 በዚሁ አዋጅ አንቀፅ 7(1) ስር ተቀይሮ ይከላከሉ ሲል ክሳቸውን አሻሽሏል፡፡
በተመሳሳይ አቶ በቀለ ገርባ ላይ የቀረበው ማስረጃ የሽብር ወንጀልን የሚያቋቁም ስላልሆነ ከፀረ ሽብር አዋጁ ወጥቶ በወንጀለኛ መቅጫ ህጉ አንቀፅ 257 (ሀ) ስር የተደነገገውን ግዙፍ ያልሆነ መሰናዳትና መገፋፋት ክስ ተቀይሮ እንዲከላከል በይኗል፡፡ በሌላ በኩል በ1ኛ ክስ በጸረ ሽብር አዋጁ አንቀጽ 3 ስር ተከሰው ከነበሩት መካከል 7ኛ ተከሳሽ ጭምሳ አብደሳ፣ 9ኛ ተከሳሽ ፍራኦል ቶላ፣ 10ኛ ተከሳሽ ጌታቸው ደረጀ እና በማንኛውም መልኩ በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ ክስ ተመስርቶበት የነበረውና በዜግነት ኬንያዊ የሆነው 22ኛ ተከሳሽ አልካኖ ቆንጨራ የቀረበባቸውን ክስ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ወስኗል፡፡
በዚሁ መዝገብ በማንኛውም መልኩ በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በመሳተፍ ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት 14ኛ ተከሳሽ ደረጀ መርጋ፣ 15ኛ ተከሳሽ የሱፍ አለማየሁ፣ 16ኛ ተከሳሽ ኢካ ተክሉ፣ 17ኛ ተከሳሽ ገመቹ ሻንቆ፣ 18ኛ ተከሳሽ መገርሳ አስፋው፣ 19ኛ ተከሳሽ ለሚ ኢዴቶ፣ 20ኛ ተከሳሽ አብዲ ታምራት እና 21ኛ ተከሳሽ አብዲ ኩምሳ ተከሰውበት የነበረውን አንቀጽ 7(1) ስር የተጠቀሰውን እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል፡፡ አቶ በቀለ ገርባ ይከላከሉ የተባሉበት አንቀፅ ዋስትና የሚያስፈቅድ በመሆኑ ዋስትና እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው በኩል ጥያቄ አቅርበው የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ‹‹በፅሁፍ አስገቡ›› ሲል ለጥያቄው ውሳኔ ሳይሰጥ አልፎታል፡፡ ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን የመከላከያ ምስክር ለመስማት ከነሃሴ 8-12/2009 ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

የአገዛዙ ደኅንነቶች የኮሎኔል ደመቀን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ለመጥለፍ ሙከራ አደረጉ source mereja.com

የአገዛዙ ደኅንነቶች የኮሎኔል ደመቀን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ለመጥለፍ ሙከራ አደረጉ፤
 በኮሎኔሉ ላይ 9 የሰለጠኑ ምስክሮች ቃላቸውን ሰጥተዋል Muluken Tesfaw

በጀግናው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ቤተሰቦች ላይ የደኅንነቶች ጫና ተባብሶ መቀጠሉ ተሰማ፡፡ የኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የክስ ሒደት እየታየ የተዘጋጁ ምስክሮች ፍርድ ቤት ቃላቸውን በሚሰጡበት ሰዐት ሐምሌ 3 ቀን 2009 ዓ.ም. የአገዛዙ ደኅንነቶች የኮሎኔሉን የ5 ዓመት ሕጻን ልጅ ጠልፈው ለመውሰድ ሲሞክሩ በሕዝብ ርብርብ መክሸፉን በአካባቢው የነበሩ እማኞች ገልጸውልናል፡፡ እድሜያቸው በ20ዎቹ ውስጥ የሚገመቱ ወጣት የደኅንነት አባላት በዕለቱ ጠዋት ጀምሮ የኮሎኔል ቤተሰቦች በሚኖሩበት ቤት በር አካባቢ ቆመው መዋላቸውን የሚገልጹት ምንጮች ምን እንደሚፈልጉ ሲጠየቁ ‹‹ሰው እየጠበቅን ነው›› የሚል መልስ በትግርኛ ቅላጼ ባለው አማርኛ እንደመለሱላቸው ገልጸው ለረዥም ሰዐታት በአካባቢው መቆማቸው እንዳጠራጠሯቸው ተናግረዋል፡፡ ከሰዐት በኋላ የኮሌኔሉን ልጅ ጠልፈው ለመውሰድ በማባበል ላይ እያሉ የኮሎኔል ደመቀ የቅርብ ዘመድ የድረሱልኝ ጩኸት በማሰማቷ በአካባቢ የነበሩ ጥቂት ሰዎች ተሰባሰቡ፤ ከዚያም እነማን ናችሁ መታዎቂያ አሳዩን የሚል ጥያቄ ከተሰበሰቡት ጥቂት ወጣቶች ሲቀርብላቸው ወደ ማስፈራራት እንደገቡና በኋላ የሰው ቁጥር እየጨመረ ሲሔድ በተሸከርካሪ በፍጥነት መሰወራቸውን የዐይን እማኞች ገልጸዋል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ ከሐምሌ 3 እስከ 5 ቀን 2009 ዓም ድረስ በኮሎኔል ላይ 9 የሚሆኑ የሰለጠኑ ምስክሮች ፍርድ ቤት ቀርበው መመስከራቸውን ሰምተናል፡፡ አብዛኛዎቹ ምስክሮች ከትግራይ ፊታቸውን ተሸፋፍነው በጥቁር መኪና በፖሊስ ታጅበው ፍርድ ቤት እንደገቡና ወዲያውኑ ወጥተው እንደተሰወሩ የፍርድ ሒደቱን የተከታተሉ ሰዎች ገልጸዋል፡፡ ዛሬ በዋለው ችሎት የዐማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ ኃላፊ የነበረውና ሸፍቻለሁ በማለት ለአገዛዙ ሲሰራ የነበረው ኮማንደር ዋኘውን ጨምሮ እነ ኮማንደር ማሙየ መመስከራቸውን አውቀናል፡፡
የዐማራ ተጋድሎ አብሳሪው የጀግናው ኮሎኔል ደመቀ የፍርድ ሒደት ሆን ተብሎ የዐማራ ተጋድሎ አንደኛ ዓመት በሚታሰብበት ቀን እንደተደረገ የሚገልጹት ምንጮች የኮሎኔሉን ሞራል ለመጉዳት የታሰበ ቢሆንም ጀግናው ግን የበለጠ የተረጋጋና አስፈሪ ግርማ ሞገስን ተላብሶ እንደነበር ፍርድ ቤት የነበሩ ግለሰቦች ገልጸውልናል፡፡ 8 የመከላከያ ምስክሮች ከሐምሌ 25 እስከ 27 ቀን ድረስ እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ አዟል

Friday, July 7, 2017

አማራውንና ኦሮሞውን ለመከፋፈል ወያኔ ያወጣው አዋጅን የኦሮሞ ድርጅቶች እየተቃወሙት ይገኛሉ source zehabesha

የፍኖተ ዴሞክራሲ ዜናና ኃተታ – 
#ርዕሰ ዜና

#ተመድ ከ800 ሺ ዜጎች በላይ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል አለ
#አነስተኛ ነጋዴዎች ከመጠን በላይ የተቆለባቸው ታክስ እያስመረራቸው ነው
#በአፍሪካ ቀንድና በየመን የተከሰተው የኮሌራ በሽታ ወደ አውዳሚ ደረጃ እየተዛወረ ነው
#እስራዔል የአፍርካ ስደተኞችን ሁኔታ አባባሰች ተባለ
#አማራውንና ኦሮሞውን ለመካፋፈል ወያኔ ያወጣው አዋጅ የኦሮሞ ድርጅቶች እየተቃወሙት ይገኛሉ
#የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች ለቀ.ኃ.ሥ ሃውልት ለመስራት ሲወስን ወያኔ ለመለሰ ካልተሰራ በማለት እያስቸገረ ነው

##ዝርዝር ዜናዎች##
#የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ባሰባሰባው መረጃ መሰረት በድርቁ ምክንያት በኢትዮጵያ 843ሺ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያዎች የሚኖሩ መሆናቸውን ገልጿል። 36,750 የሚሆኑ ዜጎች በኮሌራ በሽታ መያዛች ገልጾ ከዚሁ ውስጥ 780 መሞታቸውን መረጃ የደረሰው መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፤ 110 680 የሚሆኑ ህጻናትም በተመጣጣኝ የምግብ እጥረት እየተሰቃዩ መሆናቸውና እስካሁን ድረስ የነበረው የበልግ መኸር በበርካታ አካባቢዎች በጣም አነስተኛ መሆኑን ገልጾ በዘንድሮ ክረምት በአንዳንድ አካባቢዎች ከአማካዩ ከፍ ያለ ዝናም መዝነሙ የተመዘገበ ቢሆንም በደቡብና በደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች የጣለው ዝናም አነስተኛ በመሆኑ የረሃቡ ችግር ሊቀጥል እንደሚችል ይገመታል ብሏል።
#የቀን ገቢ ግምት በሚል ፈሊጥ የወያኔ አገዛዝ በማንአለብኝነት በአነስተኛ ነጋዴዎች ላይ የቆለለው ታክስ ብዙዎችን ያስቆጣና ያስመረረ መሆኑ ከዚህ በፊት የተዘገበ ሲሆን ታክሱ በዝቷል በሚል አቤቱታ በሚያቀርቡ ነጋዴዎች ላይ የአገዛዙ ባለስልጣኖች ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ እየሰጡ መሆናቸው ተገልጸ። በነሲብና በማን አለብኛነት ይህን ያህል ገቢ አለህ፤ ይህን ያህል ታተርፋለህ በማለት በእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ በዘፈቀደ የተቆለለው ታክስ አግባብ አይደለም በማለት ነጋዴዎቹ ቅሬታቸውን እያሰሙ ሲሆን በቡድን በመሆን ቅሬታ ማሰማት አይቻልም፤ ታክስ ሰብሳቢዎችን አመናጭቃችኋል ፤ አስፈራርታችኋል በማለት በነጋዴዎች ላይ ክስ መስርተውውባቸዋል። ነጋዴዎቹ በግለሰብ ደረጃ ቅሬታ እንዲያቀርቡ ቢነገራቸውም ታክሱን ከመክፈል እንደማይድኑም ታውቋል።
#በአፍሪካ ቀንድና በየመን ያለው የረሃብን የበሽታ የኮሌራ ወረርሽኝ ሁኔታ ከአስደንጋጭ ወደ አጥፊና አውዳሚ ደረጃ እየተሸጋገረ ነው ሲሉ ታዛቢዎች አስጠነቀቁ ። በደቡብ ሱዳን ባለው ቀውስ በመንግስት ግድ የለሽነት ሚሊዮኖች ለሞት አደጋ ተጋልጠዋል ያሉ ክፍሎች ኮሌራ በደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያና በየመን በመስፋፋት ላይ ነው ሲሉ ጠቁመዋል ። ወያኔን በመደገፍ የሀገር ኤኮኖሚ እያደገ ነው የሚሉ ክፍሎች በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሃብ አቅልለው እያቀረቡ ቢሆንም በአፋር፤ኦጋዴን፤ሰሜን ሸዋ ፤ደቡብ ኢትዮጵያ ወዘተ ረሃቡ መግደል ከጀመረ ውሎ አድሯል እየተባለም ነው ። የግልገል ግቤ 3 ግድብ አርሶ አደሮችን የሚያርሱት መሬት ማሳጣቱም ለችግሩ አስተዋጾ አድርጓል የተባለ ሲሆን ብዙ ሳይነገርለትም የተጀመረው የግልገል ግቤ 4 ግድብ ስራ በአካባቢውና አልፎም በኬንያ ችግር ፈጣሪ መሆኑ አይቀሬ መሆኑ ተዘግቧል ። እየተደበቀ ያለውን የአስከፊ ረሃብ ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማጋለጥ የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው በሚልም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
#በጨካኝና ዘረኛ ጸረ ስደተኛ አቅዋሟ ውግዘት የደረሰባት እስራኤል ከዓለም አቀፍ ትኩረት በተሸፈነ መንገድ የአፍሪካ ስደተኞችን መከራ አባብሳ ትገኛለች በሚል ተወገዘች ። ይህ ውግዘት የተመሰረተው እስራኤል የሱዳንና ኤርትራ ስደተኖችን በመደለልም ሆነ በማስገደድ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ ወስዳ መጣል ላይ ስለተሰማራች ነው ተብሏል ። በምትሄዱበት ጥገኝነትን ታገኛላችሁ የሚባሉት ስደተኞች በኪጋሊ እንግልት እየደረሰባቸውና ከዚያም ወደ ዩጋንዳ በገንዘብ ክፍያ ተወስደው እንደሚጣሉ ሊታወቅ ተሏል ። እስካሁን እስራኤል ወደ 2 ሺ የሚጠጉ ስደተኞችን ማባረሯ ታውቋል ። የእስራኤል ባለስልጣኖች በአሳፋሪ ዘረኝነት የአፍሪካ ስደተኞችን ካንሰር በሽታ ብለው መሰየማቸውና ዘግናኝ ዘረኝነትንም ማንጸባረቃቸው የተሰማና የታየ ነው ያሉ ታዛቢዎች በዩጋንዳና ሩዋንዳ ስደተኞቹ መነገጃ ሆነው ለአስከፊ ስቃይ የተዳረጉ መሆናቸው ታውቋል ብለዋል ። እስራኤል ለርዋንዳና ዩጋንዳ የተወሰነ ገንዘብ ከፍላ ተጨማሪ ስደተኞችን ልታጓጉዝ ተዘጋጅታለችም ተብሏል ።
#ወያኔ ኦሮሞና አማራን መከፋፈል በሚለው መርሁ መሰረት በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ ያወጣው መሰሪ አዋጅ በአብዛኛው የኦሮሞ ድርጅቶችና ቡድኖች በሰፊው የተወገዘ መሆኑ ተዘግቧል ። ኦሮሞዎችን በዚህ መንገድ ደልዬ እጠቀምባቸዋለሁ ብሎ በንቀት የተነሳው ወያኔ ከወዲሁ ዕቅዱ ስለከሸፈበት ልዩ ስብሰባ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ማድረጉም ተጋልጧል ። ታዛቢዎች በማስተር ፕላን ሽፋን የሕዝብን መሬት ሊቀማ ተነስቶ የከሸፈበት ወያኔ በዚህ አዋጅም የሕዝብን መሬት በራሱ እጅ ሊያስገባ እንጂ ለማንኛውም ሕዝብ ሊጠቅም ተነስቶ አይደለም ሲሉ አጋልጠውታል ። የወያኔ ተንኮል ከወዲሁ ከሽፏል ሊባል ይቻላልም ተብሏል ። በመጪው የሕዝብ ቆጠራ ወያኔ አብዛኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ ትግሬ ነው ብሎ እንደ ወልቃይት ጠገዴ ከተማይቷን የትግራይ ከማለት የሚመለስ አይደለም ሲሉ አንዳንድ ክፍሎች ተችተዋል ።
#በርካታ የአፍሪካ መሪዎችና የፖለቲካ ሀይሎች ከአፍሪካ ህብረት መስራቾች አንዱ ለሆኑት ለአጼ ኃይለስላሴ ሀውልት ይቁማላቸው ማለታቸው ታወቀ; ወያኔ በዚህ አስታኮ ለከሀዲውና የባዕዳን ቅጥረኛ ለሆነው ለመለስ ዜናዊም በተጽዕኖ ሀውልት ሊያቆም መወሰኑ ተወግዟል ። አጼው ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራቾች አንዱ ሲሆኑ መለስ ዜናዊ ግን ለአፍሪካ የቆመ ሳይሆን ኢትዮጵያና አፍሪካን ለምዕራባውያን የሸጠና የኢምፔሪያሊዝም ቅጥረኛ የነበረ በመሆኑ ሀውልት ሊሰራለት ቀርቶ በጸረ አፍሪካነት መወገዝ ያለበት ከሀዲ ነው ሲሉ ብዙዎች በጥብቅ ተቃውመዋል።
#የአፍሪካውያን ቁጥር ጨምሯልና መቀነስ አለበት ባዩ የአሜሪካው የጠገበ ሀብታም ቢል ጌትስ ውድቅ የወያኔ የጤና ተቋሞችን ቢያዳንቅም ሆነ ድህነት በስተፋፋበት ሀገር ኤኮኖሚ ተመነደገ ተብሎ ቢዋሽም በተደረጉ ጥናቶች በወያኔ አገዛዝ ስር ትምህርት ሳይሆን ድንቁርና መስፋፋቱ ተጋልጧል ። አንደኛ ደረጃ ትምህርት ጨርሰው ማንበበና መጻፍ በሚገባው ደረጃ የማይችሉ ብዙዎች ናቸው ያሉ ክፍሎች በየእርከኑ የተመደቡ አስተማሪዎችም ቢሆን ብቃታቸው አጠያያቂ ነው ብለዋል ። ወያኔ ብቃይ ያላቸውን አስተማሪዎች መንጥሮ ማባረሩ አይረሳም ያሉ ክፍሎች የአስተማሪዎችንም ታሪካዊ ማህበር አፍርሶ ለዘረኛ ፖለቲካው በሚያመች ደረጃ ትምህርትን አዳክሟል ሲሉ ከሰዋል ። ይህ ሕዝብ ሁሉየሚያውቀው ሀቅ በባዕዳንም ጥናት ዛሬ እየተረጋገጠ በመሆን ውግዘት መቀበል የተገደደው ወያኔ በውሸቱ በመቀጠል ከ97 በመቶአ ያላነሱ ሕጻናት ትምህርት ቤት መግባታቸው ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት ባልታየ ደረጃ የማንበብ መጻፍ ችሎታ ያለው ሕዝብ ቁጥር እጥፍ ድርብ ጨምሯል በሚል ቅጥረኞቹን እያስዋሸ ነው በሚልም ተጋልጧል ።
የፍኖተ ዴሞክራሲ ዜናና ኃተታ – ሰኔ 28 ቀን 2009 ዓ.ም. #ርዕሰ ዜና #ተመድ ከ800 ሺ ዜጎች በላይ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል አለ #አነስተኛ ነጋዴዎች ከመጠን በላይ የተቆለባቸው ታክስ እያስመረራቸው ነው #በአፍሪካ ቀንድና በየመን የተከሰተው የኮሌራ በሽታ ወደ አውዳሚ ደረጃ እየተዛወረ ነው #እስራዔል የአፍርካ ስደተኞችን ሁኔታ አባባሰች ተባለ #አማራውንና ኦሮሞውን ለመካፋፈል ወያኔ ያወጣው አዋጅ የኦሮሞ ድርጅቶች እየተቃወሙት ይገኛሉ #የአፍሪካ ኅብረት መሪዎች ለቀ.ኃ.ሥ ሃውልት ለመስራት ሲወስን ወያኔ ለመለሰ ካልተሰራ በማለት እያስቸገረ ነው ##ዝርዝር ዜናዎች## #የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ ባሰባሰባው መረጃ መሰረት በድርቁ ምክንያት በኢትዮጵያ 843ሺ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያዎች የሚኖሩ መሆናቸውን ገልጿል። 36,750 የሚሆኑ ዜጎች በኮሌራ በሽታ መያዛች ገልጾ ከዚሁ ውስጥ 780 መሞታቸውን መረጃ የደረሰው መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፤ 110 680 የሚሆኑ ህጻናትም በተመጣጣኝ የምግብ እጥረት እየተሰቃዩ መሆናቸውና እስካሁን ድረስ የነበረው የበልግ መኸር በበርካታ አካባቢዎች በጣም አነስተኛ መሆኑን ገልጾ በዘንድሮ ክረምት በአንዳንድ አካባቢዎች ከአማካዩ ከፍ ያለ ዝናም መዝነሙ የተመዘገበ ቢሆንም በደቡብና በደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች የጣለው ዝናም አነስተኛ በመሆኑ የረሃቡ ችግር ሊቀጥል እንደሚችል ይገመታል ብሏል። #የቀን ገቢ ግምት በሚል ፈሊጥ የወያኔ አገዛዝ በማንአለብኝነት በአነስተኛ ነጋዴዎች ላይ የቆለለው ታክስ ብዙዎችን ያስቆጣና ያስመረረ መሆኑ ከዚህ በፊት የተዘገበ ሲሆን ታክሱ በዝቷል በሚል አቤቱታ በሚያቀርቡ ነጋዴዎች ላይ የአገዛዙ ባለስልጣኖች ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ እየሰጡ መሆናቸው ተገልጸ። በነሲብና በማን አለብኛነት ይህን ያህል ገቢ አለህ፤ ይህን ያህል ታተርፋለህ በማለት በእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ በዘፈቀደ የተቆለለው ታክስ አግባብ አይደለም በማለት ነጋዴዎቹ ቅሬታቸውን እያሰሙ ሲሆን በቡድን በመሆን ቅሬታ ማሰማት አይቻልም፤ ታክስ ሰብሳቢዎችን አመናጭቃችኋል ፤ አስፈራርታችኋል በማለት በነጋዴዎች ላይ ክስ መስርተውውባቸዋል። ነጋዴዎቹ በግለሰብ ደረጃ ቅሬታ እንዲያቀርቡ ቢነገራቸውም ታክሱን ከመክፈል እንደማይድኑም ታውቋል። #በአፍሪካ ቀንድና በየመን ያለው የረሃብን የበሽታ የኮሌራ ወረርሽኝ ሁኔታ ከአስደንጋጭ ወደ አጥፊና አውዳሚ ደረጃ እየተሸጋገረ ነው ሲሉ ታዛቢዎች አስጠነቀቁ ። በደቡብ ሱዳን ባለው ቀውስ በመንግስት ግድ የለሽነት ሚሊዮኖች ለሞት አደጋ ተጋልጠዋል ያሉ ክፍሎች ኮሌራ በደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያና በየመን በመስፋፋት ላይ ነው ሲሉ ጠቁመዋል ። ወያኔን በመደገፍ የሀገር ኤኮኖሚ እያደገ ነው የሚሉ ክፍሎች በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሃብ አቅልለው እያቀረቡ ቢሆንም በአፋር፤ኦጋዴን፤ሰሜን ሸዋ ፤ደቡብ ኢትዮጵያ ወዘተ ረሃቡ መግደል ከጀመረ ውሎ አድሯል እየተባለም ነው ። የግልገል ግቤ 3 ግድብ አርሶ አደሮችን የሚያርሱት መሬት ማሳጣቱም ለችግሩ አስተዋጾ አድርጓል የተባለ ሲሆን ብዙ ሳይነገርለትም የተጀመረው የግልገል ግቤ 4 ግድብ ስራ በአካባቢውና አልፎም በኬንያ ችግር ፈጣሪ መሆኑ አይቀሬ መሆኑ ተዘግቧል ። እየተደበቀ ያለውን የአስከፊ ረሃብ ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ማጋለጥ የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው በሚልም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። #በጨካኝና ዘረኛ ጸረ ስደተኛ አቅዋሟ ውግዘት የደረሰባት እስራኤል ከዓለም አቀፍ ትኩረት በተሸፈነ መንገድ የአፍሪካ ስደተኞችን መከራ አባብሳ ትገኛለች በሚል ተወገዘች ። ይህ ውግዘት የተመሰረተው እስራኤል የሱዳንና ኤርትራ ስደተኖችን በመደለልም ሆነ በማስገደድ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ ወስዳ መጣል ላይ ስለተሰማራች ነው ተብሏል ። በምትሄዱበት ጥገኝነትን ታገኛላችሁ የሚባሉት ስደተኞች በኪጋሊ እንግልት እየደረሰባቸውና ከዚያም ወደ ዩጋንዳ በገንዘብ ክፍያ ተወስደው እንደሚጣሉ ሊታወቅ ተሏል ። እስካሁን እስራኤል ወደ 2 ሺ የሚጠጉ ስደተኞችን ማባረሯ ታውቋል ። የእስራኤል ባለስልጣኖች በአሳፋሪ ዘረኝነት የአፍሪካ ስደተኞችን ካንሰር በሽታ ብለው መሰየማቸውና ዘግናኝ ዘረኝነትንም ማንጸባረቃቸው የተሰማና የታየ ነው ያሉ ታዛቢዎች በዩጋንዳና ሩዋንዳ ስደተኞቹ መነገጃ ሆነው ለአስከፊ ስቃይ የተዳረጉ መሆናቸው ታውቋል ብለዋል ። እስራኤል ለርዋንዳና ዩጋንዳ የተወሰነ ገንዘብ ከፍላ ተጨማሪ ስደተኞችን ልታጓጉዝ ተዘጋጅታለችም ተብሏል ። #ወያኔ ኦሮሞና አማራን መከፋፈል በሚለው መርሁ መሰረት በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ ያወጣው መሰሪ አዋጅ በአብዛኛው የኦሮሞ ድርጅቶችና ቡድኖች በሰፊው የተወገዘ መሆኑ ተዘግቧል ። ኦሮሞዎችን በዚህ መንገድ ደልዬ እጠቀምባቸዋለሁ ብሎ በንቀት የተነሳው ወያኔ ከወዲሁ ዕቅዱ ስለከሸፈበት ልዩ ስብሰባ በከፍተኛ አመራር ደረጃ ማድረጉም ተጋልጧል ። ታዛቢዎች በማስተር ፕላን ሽፋን የሕዝብን መሬት ሊቀማ ተነስቶ የከሸፈበት ወያኔ በዚህ አዋጅም የሕዝብን መሬት በራሱ እጅ ሊያስገባ እንጂ ለማንኛውም ሕዝብ ሊጠቅም ተነስቶ አይደለም ሲሉ አጋልጠውታል ። የወያኔ ተንኮል ከወዲሁ ከሽፏል ሊባል ይቻላልም ተብሏል ። በመጪው የሕዝብ ቆጠራ ወያኔ አብዛኛው የአዲስ አበባ ነዋሪ ትግሬ ነው ብሎ እንደ ወልቃይት ጠገዴ ከተማይቷን የትግራይ ከማለት የሚመለስ አይደለም ሲሉ አንዳንድ ክፍሎች ተችተዋል ። #በርካታ የአፍሪካ መሪዎችና የፖለቲካ ሀይሎች ከአፍሪካ ህብረት መስራቾች አንዱ ለሆኑት ለአጼ ኃይለስላሴ ሀውልት ይቁማላቸው ማለታቸው ታወቀ; ወያኔ በዚህ አስታኮ ለከሀዲውና የባዕዳን ቅጥረኛ ለሆነው ለመለስ ዜናዊም በተጽዕኖ ሀውልት ሊያቆም መወሰኑ ተወግዟል ። አጼው ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራቾች አንዱ ሲሆኑ መለስ ዜናዊ ግን ለአፍሪካ የቆመ ሳይሆን ኢትዮጵያና አፍሪካን ለምዕራባውያን የሸጠና የኢምፔሪያሊዝም ቅጥረኛ የነበረ በመሆኑ ሀውልት ሊሰራለት ቀርቶ በጸረ አፍሪካነት መወገዝ ያለበት ከሀዲ ነው ሲሉ ብዙዎች በጥብቅ ተቃውመዋል። #የአፍሪካውያን ቁጥር ጨምሯልና መቀነስ አለበት ባዩ የአሜሪካው የጠገበ ሀብታም ቢል ጌትስ ውድቅ የወያኔ የጤና ተቋሞችን ቢያዳንቅም ሆነ ድህነት በስተፋፋበት ሀገር ኤኮኖሚ ተመነደገ ተብሎ ቢዋሽም በተደረጉ ጥናቶች በወያኔ አገዛዝ ስር ትምህርት ሳይሆን ድንቁርና መስፋፋቱ ተጋልጧል ። አንደኛ ደረጃ ትምህርት ጨርሰው ማንበበና መጻፍ በሚገባው ደረጃ የማይችሉ ብዙዎች ናቸው ያሉ ክፍሎች በየእርከኑ የተመደቡ አስተማሪዎችም ቢሆን ብቃታቸው አጠያያቂ ነው ብለዋል ። ወያኔ ብቃይ ያላቸውን አስተማሪዎች መንጥሮ ማባረሩ አይረሳም ያሉ ክፍሎች የአስተማሪዎችንም ታሪካዊ ማህበር አፍርሶ ለዘረኛ ፖለቲካው በሚያመች ደረጃ ትምህርትን አዳክሟል ሲሉ ከሰዋል ። ይህ ሕዝብ ሁሉየሚያውቀው ሀቅ በባዕዳንም ጥናት ዛሬ እየተረጋገጠ በመሆን ውግዘት መቀበል የተገደደው ወያኔ በውሸቱ በመቀጠል ከ97 በመቶአ ያላነሱ ሕጻናት ትምህርት ቤት መግባታቸው ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት ባልታየ ደረጃ የማንበብ መጻፍ ችሎታ ያለው ሕዝብ ቁጥር እጥፍ ድርብ ጨምሯል በሚል ቅጥረኞቹን እያስዋሸ ነው በሚልም ተጋልጧል ።

Thursday, July 6, 2017

በባህርዳር መግቢያ መውጫወች በተለይ በጎንደር መስመር ከፍተኛ ወታደራዊ ፍተሻ እየተደረገ ነው !! source satenewa

ይህ የወያኔ ፍተሻ የሚያገኘው ነገር ኖሮ ሳይሆን በህዝቡ ላይ የፍርሃት ቆፈን በመጫን የስነ ልቦና ጫና ለመፍጠር ያለመ ነው። ህወሓት /ወያኔ ውርደቱን ለመሸፋፈን ያዙኝ ልቀቁኝ አብዝቷል። የደረሰበት መተረማመስና መፈረካከስ ተረጋግቶ እንዲቀመጥ አላደረገውም። የነፃነት ሃይሎች ያልተጠበቀና ምንም መረጃ ባልወጣበት የሚፈፀም ጥቃት ፋታ ነስቶታል። ወደ ጎጃም እየገሰገሰ የሚገኘው የነፃነት ትግል ፋና የውስጡን አለመረጋጋት እና ጎራ ለይቶ እርስ በርሱ በጥርጣሬ መተያየቱን በጉልህ ጥርሱን አግጥጦ እንዲታይ አድርጎታል። በባህርዳር አየር ማረፊያ የተያዘው ተቀጣጣይ ፈንጂ ደግሞ የነፃነት ትግሉ አድማሱን ማስፋቱና ከእጁ እየወጣ የሚገኘው የቀጠናው የነፃነት ታጋዩች እንቅስቃሴ በወታደር ብዛት መግታት እንዳልቻለ ያረጋገጠ ትልቅ ስጋት ሁኖበታል።በዚህም የራሴ የሚላቸውን ሰወች በመጠራጠር እስከ ማሰር እንደደረሰ መረጃወች ይጠቁማሉ። በቀጣይ ይደርስብኛል ብሎ ከሰጋቸው አንኳር ጥቃቶች በመነሳት በለሊት ማንኛውንም የስራ መኪና እንቅስቃሴ በሰሜኑ ቀጠና እስከማገድ እና በኬላወች ለፍተሻ በማስቆም እንዲያድር ያደርጋሉ። በዛሬ ዕለተ ረዕቡ ሰኔ 28/2009 ዓ.ም አነጋግ የጀመረው ፍተሻ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች (ባለማዕረግተኞች)በስምሪት የተሳተፉበት ነበር። በትናንትናው ምሽት በበግ ተራ አካባቢ ሰወች እየታደኑ ይያዙ እንደነበር የአይን እማኞች ይናገራሉ። በወታደሮች እየተያዙ የተወሰዱ ሰወች ትክክለኛ ማንነትና ቁጥር እስካሁን ለማረጋገጥ አልተቻለም። ይህ በህወሓት ወንበዴ ቡድን የሚፈፀም ድንገተኛ የተጋነነ ወታደራዊ ሰልፍና ፍተሻ በመውጫ መግቢያወች ምንም የሚያገኘው ኑሮ ሳይሆን በነዋሪው ህዝብ ላይ የፍርሃት ቆፈን በመደረብ የስነ ልቦና ጫና ለመፍጠር ያለመ ውርደቱን መሸፈኛ ካባ ነው ። ስነልቦናው እንደ አለት በጠነከረ ህዝብ ላይ ጫና ለመፍጠር መሯሯጥ ትርፉ መላላጥ ብቻ ነው። ድል ድል ይሸታል አየሩ ፣ ትርምስምስ ብሏል ጠላት መንደሩ ። ድል ምንጊዜም የህዝብ ነው !! @እንቅዩጳዝዩን የአርበኞቹ ልጂ     

” እኛን ሰዎች ኤርትራን ሸጣችኋታል እያሉ ያሙናል፡፡ ” ኃይለማርያም ደሳለኝ source bbn

ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም እስራኤልን ብቻ መጎብኘታቸው ቅር እንዳሰኛቸው የፍልስጤሙ መሪ ተናገሩ . BBN.

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ፍልስጤምን አለመጎብኘታቸው ቅሬታ እንደፈጠረባቸው የፍልስጤሙ መሪ ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአንድም ሁለት ጊዜ እስራኤልን መጎብኘታቸውን ያስታወሱት የፍልስጤሙ መሪ መሐሙድ አባስ፣ ፍልስጤምን አለመጎብኘታቸውም ቅር እንዳሰኛቸው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደነገሯቸው ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የእስራኤል ጉብኝት ተከትሎ፣ ፍልስጤም የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በተለየ ሁኔታ እየተከታተለችው እንደምትገኝም የፍልስጤሙን መሪ ጠቅሶ ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
ሁለቱ መሪዎች የተነጋገሩት በአዲስ አበባ ሲደረግ በነበረው የአፍሪካ መሪዎች ጉባኤ ኢ-መደበኛ በሆነ ውይይት ላይ ሲሆን፣ በውይይቱም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ተደጋጋሚ ወቀሳ ቀርቦባቸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ፍልስጤም ባቀረበችው ግብዣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሀገራቸውን እንዲጎበኙ የቀረበላቸውን ተደጋጋሚ ግብዣ አለመቀበላቸው ቅር እንዳሰኛቸው የፍልስጤሙ መሪ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያን እንደ አገሬ ነው የማያት፡፡›› ያሉት ፕሬዚዳንት መሐሙድ አባስ፣ ‹‹ከእስራኤል ፕሬዚዳንት ቤኒያሚን ኔታንያሁ ጋር ያለው ችግር የአገሬን ሉዓላዊነትና ደኅንነት እየተፈታተ ነው፡፡›› ማለታቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያ ደሳለኝ ከዚህ ቀደም እስራኤልን የጎበኙት በግላቸው መሆኑን ለፍልስጤሙ መሪ የገለጹላቸው ሲሆን፣ ‹‹ፍልስጤምን መጎብኘት አለመቻሌን ከእስራኤል ጋር አታያይዙት፡፡›› ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም በቅርቡ እንኳን ወደ እስራኤል አቅንተው የነበሩት መንግስታቸውን ወክለው እንደነበር አይዘነጋም፡፡ ሆኖም ‹‹ወደ እስራኤል የሔድኩት በግሌ ነው፡፡›› ማለት ለምን እንደፈለጉ አልታወቀም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ‹‹ኢትዮጵያ ከፍልስጤም ጋር ያላትን ግንኙነት ወደፊት ታጠናክራለች፡፡›› ብለዋል፡፡
አቶ ኃይለ ማርያም ንግግራቸውን ቀጥለው በውይይቱ ላይ ‹‹እኛን ሰዎች ኤርትራን ሸጣችኋታል እያሉ ያሙናል፡፡ እውነታው ግን የሕዝብ ውሳኔ ነው፡፡›› ካሉ በኋላ፣ ‹‹እናንተም ሕዝቦቻችሁን መሠረት አድርጋችሁ በመካከላችሁ ያለውን ግጭት መፍታት ይገባችኋል፡፡›› ሲሉ ለፍልስጤሙ መሪ መሐሙድ አባስ ምክር ቢጤ ለግሰዋል፡፡ መሐሙድ አባስ በበኩላቸው፣ ሀገራቸው ከእስራኤል ጋር ያላትን ቅራኔ ለመፍታት ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ውይይት እያደረጉ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፣ አቶ ኃይለማርያም በበኩላቸው ‹‹በአሜሪካ ፕሬዚዳንት ውሳኔ ዘላቂነት ላይ ጥርጣሬ ቢኖረኝም ጅምሩ ጥሩ ነው፡፡›› ብለዋል፡፡
BBN

Tuesday, July 4, 2017

“ነጭ ኑግ ጥቁር ወተት ውለዱ” – 25 አመታት የሌላውን ሁሉ ውጣ የማትጠረቃው ክልል! ! [ቬሮኒካ መላኩ] source zhebesha

ትናንት ነበር ሌላም ጊዜ እንደማደርገው ለአመታት የጆሮዬ ጓደኛ የሆነውን የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ሰአቱን ጠብቄ ከፍቸው ነበር። የእለቱ የራዲዮ ፕሮግራሙ አስተዋዋቂ ” አድማጮቻችን በዛሬው የፕሮግራማችን ሁለተኛ ክፍል ላይ ኢትዮጵያ በኤርትሪያ ላይ የምትከተለው ፖሊሲ በትግራይ ክልል እየፈጠረ ያለውን ችግር የሚያስረዱ ሁለት እንግዶች ስለሚቀርቡ ይሄን ዝግጅት እንድታዳምጡ እንጋብዛለን> > በማለት ፕሮግራሙን አስተዋወቀ። እኔም ሰአቱን ጠብቄ ፕሮግራሙን መከታተል ጀመርኩኝ ። … የፕሮግራሙ አዘጋጅ የሆነችው አንጋፋዋ ጋዜጠኛ አዳነች ፍስሃዬ ስትሆን የጋበዘቻቸው ሰዎች ደሞ ከወደ ትግራይ እንደሆኑ በሚናገሩት አማርኛ በደንብ መረዳት ይቻል ነበር። ሲጀመር ይሄ ፕሮግራም መቅረብ የነበረበት በቪኦኤ የትግርኛ ፕሮግራም ነበር በአማርኛው ክፍለ ጊዜም ይቅረብ ከተባለ ቢያንስ አንድ አይነት አመለካከት ፣አንድ አይነት አስተሳሰብ ያላቸውን እንግዶች ከማቅረብ በጉዳዩ ላይ የተለየ አመለካከት ያላቸው እንግዶች ቢቀርቡ ፕሮግራሙን ሚዛናዊ ማድረግ ይቻል ነበር። … በነገራችን ላይ አንጋፋውና ተወዳጁ የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ በአንድ ክልል እና ብሄር የእጅ አዙር ቁጥጥር ስር የገባ ይመስላል። ቪኦኤ ከሌላው የኢትዮጵያ ክፍል በተለየ ከትግራይ ክልል የሚዘግብ ዘጋቢ አለው ፣ በትግሪኛ ቋንቋ የሚያሰራጨው በክልሉ ፖለቲካዊ ፣ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና እና ሌሎች ጉዳዮች ብቻ አትኩሮ የሚሰራ የ30 ደቂቃ ፕሮግራም አለው ። ይሄ ሁሉ አልበቃ ብሎ የአማረኛውም ፕሮግራም ብዙ ጊዜውን የሚያጠፋው ስለትግራይ በመዘገብ ነው። … ወደ ዋናው የትናንቱ የቪኦኤ ፕሮግራም ይዘት ስገባ ፕሮግራሙ በሁለት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር: ። በፕሮግራሙ የቀረቡት እንግዶች ጥያቄያቸውን ለጠ/ሚ ሀይለማሪያምና ፌደራል መንግስት ማቅረባቸውንና በጎ ምላሽ እንደሚጠብቁ ገልፀዋል … ሁለቱ የፕሮግራሙ ይዘቶች … 1~ ትግራይ የጦርነት ቀጠና ሆና በልማት እየተጎዳች ስለሆነ ከፌደራል መንግስት ድጎማ እንድደረግላት የሚጠይቅ ሲሆን… … 2~ ኢትዮጵያ በኤርትራ ላይ የምትከተለው No war No peace ፖሊሲ ተቀይሮ ወደ ጦርነት እንድገባ የሚገፋፋ አንድምታ ያለው ነው ። … በሁለቱም ጉዳዮች ላይ ያለኝን አመለካከት አጠር በማድረግ ላስቀምጥ: ….. 1~ “ትግራይ በልማት እየተጎዳች በመሆኑ የፌደራል መንግስት ድጎማ ያስፈልጋታል ” ….. እንግሊዛዊው ባለቅኔና ገጣሚ ዊሊያም ሸክስፒር ” ሀምሌት ” በተባለው ዘመን አይሽሬ ተውኔቱ የሰውን ስግብግብነት ፣ አልጠግብ ባይነት ፣ክፋት ፣ ተንኮል እና ፈጣጣነት በአንድ አረፍተ ነገር ገልፆት ነበር … << O shame, where is thy blush ? Proclaim no shame !! …>> ” ሃፍረት ሆይ !! ይሉኝታ ቢስ ሆይ!! ቅላትሽ ወደት አለ? … አንተ ሀፍረተ ቢስ!! እናንተ ይሉኝታ የለሾች! ! ሃፍረት የሌለህ እንደሆንከ አዋጅ ተናገር >> እያለ ይቀጥላል ። እዚህ ላይ የዊሊያም ሸክስፒርን አባባል መጥቀሴ ለእነዚህ ሰዎች ተገቢና ገላጭ አባባል ሆኖ ስላገኘሁት ነው ። … ይች ኢትዮጵያ የምትባል አገር እስከ መቼ ነው የትግራይ ጥገት ላም ሆና የምትኖረው? አሁንም ከመቶ ሚሊዮን ህዝብ አፍ ላይ ተነጥቆ የእነሱ ክልል እንደ ታይዋን እና ሆንግ ኮንግ እንደሆን ይፈልጋሉ ። ብዙዎች በየቀኑ ከኢትዮጵያዊነት መንበር ሸርተት እያሉ ለመሸፈታቸው ዋናው ምክንያት ” ትግሬ እያጋበሰ የሚኖርባት እና ሌላው በችጋር ተጠብሶ የሚያለቅስባት አገር ፣ የተለያዩ ዜጎች እና ክልሎች በእኩል አይን የማይታዩበታ አገር አታስፈልገኝም ” በማለት ነው። ዛሬ የኢትዮጵያ ሌላው ክልል ዜጎች በርሃብ ፣ በእርዛት ፣ በእስር እና በግድያ የሚሰቃዩባት የትራጂዲያ መድረክ ናት ። እንደ ተራ እንስሳ በመከራ የሚጠበሱ ዜጎች ባሉባት አገር ውስጥ የአንድ ክልል ነዋሪዎች ሌላውን ህዝብ << ጥቁር ወተት እና ነጭ ኑግ ውለድ! >> የሚባለው የአልጠግብ ባዮች ልፈፋ በአስቸኳይ መቆም አለበት ። ቪኦኤስ እንደት ስራ ቢያጣ ነው ይሄን አይነት የለየለት የዘረፋ ፕሮጀክት ሊያቀርብልን የቻለው ? የኢትዮጵያ ምዝብርና ግፉእ ህዝብ ለ25 አመታት የተበዘበዘውና የተመዘበረው አንሶ አሁንም አመታት ቢውጡ ከርሳቸው የማይሞላና የማይጠግቡ ቡድኖች ሲሳይ መሆኑ ማብቃት አለበት ። ይሄ ካልሆነ ግን በአገራችን ይሄ አይነት ሰፍሳፋነትና አልጠግብ ባይነት እስካለ ድረስ በአገራችን ሰላም ሊሰፍን አይችልም ። … 2~ የኢትዮጵያ መንግስት በኤርትሪያ ላይ የሚከተለውን ፖሊሲ በመቀየር አስቸኳይ እርምጃ እንድወስድ ። … በሁለተኛ ደረጃ የአዳነች ፍስሃዬ እንግዶች ያስረዱትና እና ለፌደራል መንግስት አቀረብነው ያሉት ጉዳይ ” ጦርነት ይደረግልን” የሚል አንድምታ ይመስላል። ሀበሻ ሲተርት ” የዘንዶ ጉድጓድ በሞኝ ክንድ ይለካል ” ይላል። እነዚህ ሰዎች እቤታቸው ያለውን የዘንዶ ጉድጓድ በሌላው ኢትዮጵያዊ ክንድ ይለካልን እያሉ እየጠየቁ ይመስላል ። ከአመታት በፊት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣት ወንዶች ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው ወደ ጦር ሜዳ ዘመቱ። እነዚህ ወጣቶች ወደ ጦርነቱ ሆ ብለው የገቡት በወቅቱ ገንኖ በነበረው የብሔራዊ ስሜት ማዕበል ተነድተው እና አገራችን ተወረረች ብለው ነበር ።ይሁንና ብዙም ሳይቆይ ተገኘ የተባለው ድል ወደ ምሬት ተለወጠ። ሰዎች በዘር እየተለዩ እየተመረጡ የፈንጅ ማምከኛ እንደሆኑ ተረጋገጠ ።ምሽግ ውስጥ ሆነው የሚዋጉት ወታደሮች ብዙም ሳይቆይ እውነታው ግልጽ ሆነላቸው። የፖለቲካ መሪዎች ጉድ እንዳደረጓቸው፣እንዳታለሏቸውና የጦር መሪዎቻቸውም አሳልፈው እንደሰጧቸው ተረዱ። … ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች “ደስ እያላቸውና በፈቃደኝነት” ለጦርነት የዘመቱት ወድያውኑ ዘመቻው አንድን ቡድን የበላይነት ለመጠበቅ እንደሆነ ተረዱ ። ህዝቡም አወቀ ።የጦርነቱ ነጋሪት ጎሳሚዎች ጦርነት መኖር ያለበት “ተፈጥሮአዊ ግዴታ” ነው ብለው ያመኑ ይመስሉ ነበር ። BBC በተባለው የዜና ማሰራጫ “Human Wave ” በተባለው የጦርነት ስልት ያለቁትን ብሄሮች ስንሰማ የወያኔ መሪዎች ፊል ዊልያምስ የተባሉት ደራሲ “ማህበራዊ ዳርዊኒዝም” ጦርነት የተወሰኑ ዘሮችን ፣ ብሄሮችን ለማስወገድ” የሚያስችል ትክክለኛ መሣሪያ ነው የሚለውን አስተሳሰብ ተከታዮች እንደነበሩ ተረድተናል ። … ዛሬስ እነዚህ ሰዎች ምን አድርጉ እያሉን ነው? የምን ነጋሪት እየጎሰሙብን ነው? የማሰብ ችሎታ ያላቸው ሰዎች . . . እንዲህ ያለውን እብደት ሊቀበሉ ይችላሉ ወይ? በእርግጥ ዛሬ ሌላ ቀን ነው ። በእርግጥ ልንማረው የሚገባ አንድ ግልጽ ትምህርት አለ። ባለፉት አመታትት የታዩት አሳዛኝ ሁኔታዎች እንዳይደገሙ ከተፈለገ ሊሳሳቱ ከሚችሉት የሰው ልጆች ፍልስፍናዎች ይበልጥ አስተማማኝ የሆነ መመሪያ ያስፈልገናል። ከታሪክ መማር ። “ሰዎች ከታሪክ ሊማሩ ቢችሉ ኖሮ እንዴት ያለ ትምህርት ይገኝ ነበር! ነገር ግን በስሜታዊነትና በወገናዊነት ታውረናል። ተሞክሮ የፈነጠቀልን ብርሃን የጋን ውስጥ መብራት ሆኖብናል!”— ሳሙኤል ቴይለር ኮልሪጅ እንግሊዛዊው ባለቅኔ ሳሙኤል ኮልሪጅ በሰጠው አስተያየት እኔ እስማማለሁ ። ለአንድ የተወሰነ ዓላማ

Sunday, July 2, 2017

ሁከት አንስተዋል የተባሉ እስረኞች ከቅሊንጦ እስር ቤት ወደ ሌሎች እስር ቤቶች ተዛወሩ source zhabesha

file photo
የፍኖተ ዴሞክራሲ ዜናና ኃተታ –
ርዕሰ ዜና

#ሁከት አንስተዋል የተባሉ እስረኞች ከቅሊንጦ እስር ቤት ወደ ሌሎች እስር ቤቶች ተዛወሩ
#አመጽ ቀስቃሽ ግጥሞችን በዩቲዩብ አሰራጭተዋል የተባሉ ጋዜጠኞች ክስ ተመሰረተባቸው
#በጎንደር አንድ የሞርታር ጥይት ፈንድቶ በህይወትና በአካል ላይ ጉዳት አደረሰ
#ሳኡዲ አረቢያ የጣለችውን የቀን ገደብ ለ30 ቀን አራዘመች
#በአገራችን የገባው የተምች መንጋ በከፍተኛ ፍጥነት መስፋፋቱ አሳሳቢ ነው ተባለ
##ዝርዝር ዜናዎች##

#በቅሊንጦ ከሚገኘው የወያኔ እስር ቤት ውስጥ ከ20 የሚበልጡ እስረኞች ወደ ዘዋይ እስር ቤት ቁጥራቸው ያልታወቀ ሌሎች ደግሞ ወደ ሸዋ ሮቢት የተዛወሩ መሆኑ ታውቋል። እስረኞቹ ወደ ሌሎች እስር ቤቶች የተዛወሩበት ምክንያት በመካከላቸው በዘር ላይ የተሰመረተ ግጭት ፈጥረው ሁከት በማስነሳታችው ነው የሚል ምክንያት እየተሰጠ ሲሆን ከተዛወሩት መካከልም ከዚህ በፊት #እስር ቤቱን በማቃጠል የተከሰሱ እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል። ላለፉት ጥቂት ቀናት በቅሊንጦ እስር ቤት ዞን 4 እና 5 ውስጥ የታሰሩ እስረኞች ዘመዶቻቸው እንዳያዩዋቸው የተከለከሉ መሆናቸውም ታውቋል። እስር ቤት ውስጥ የታጨቀው እስረኛ በጣም በርካታ ከመሆኑ የተነሳ እስረኞች በጥበቱ የተማረሩ መሆናቸውን በተደጋጋሚ መግለጻችው ይታወቃል። በ 900 ሚሊዮን ብር እየተሰራ ነው የሚባለውም እስር ቤት ምን ያህል ችግሩን ሊያቃልል እንደሚችል አልታወቀም ተብሏል።
#በጋዘጠኛነት ሙያ ተሰማርተው የነበሩና አመጽ ቀስቃሽ ግጥሞችን በዩቱዩብ አሰራጭታችኋል የተባሉ ሰባት ሰዎች ክስ የተመሰረተባችው መሆኑ ታወቀ። ሰባቱ በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርበው የተሰነሰዘረባቸው ክስ የተሰማ ሲሆን ከተከሳሾች በኩል የሚቀርበውን የመጀመሪያ የመቃወሚያ ሀሳቦችን ለመሰማት ለሐምሌ 7 ቀን ቀጠሮ የተያዘ መሆኑ ታውቋል።
#በጎንደር ከተማ ቅዳሜ ከተማ ውስጥ ልዩ ስሙ አሮጌ ብረት ተራ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የሞርታር ጥይት በመፈንዳቱ ምክንያት ሁለት ስዎች ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውና ሌሎች ሶስት ሰዎች የቆሰሉ መሆናችው ተነገረ። የሞርታር ጥይቱን ለብረት ሙቀጫ ለማዋል በብረት መጋዝ በመቁረጥ ላይ እንዳሉ ጥይቱ በመፈንዳቱ ሰዎቹ ወዲያውኑ ሊሞቱ የቻሉ መሆናቸው ተነግሯል።
#የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ህገ ወጥ ናቸው የሚላቸው ስደተኞች ከአገሩ እንዲወጡ አውጆት የነበረውን የቀን ገደብ ለ 30 ቀናት ያራዘመው መሆኑን ገለጸ። ለቀን ገደቡ መራዘም በሳኡዲ መንግስት በኩል የተሰጠ ማብራሪያ ባይኖርም የወያኔ አገዛዝ እና አንዳንድ ወገኖች ላቀረቡት ጥያቄ የተሰጠ መልስ ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት አለ። በሳኡዲ አረቢያ ከ400000 እስከ 450000 ሺ የሚገመቱ ኢትዮጵያን ስደተኞች በህገ ወጥ መንገድ ይኖራሉ ተብሎ ሲገመት እስካሁን የተመለሱት ቁጥር ከ45000 እንደማይበልጥና የመጓጓዣ ሰነድ ተሰጥቷቸዋል የተባሉት 111 ሺ ብቻ መሆናቸው ተነግሯል።
#በአገራችን የገባው የተምች መንጋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ በመሄዱ ሁኔታው በጣም አሳሳቢ መሆኑ ተነገረ። እስካሁን ድረስ በ35 ዞኖች በ136 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የተዘሩ ሰብሎችን ያበላሸው ይኽው የተምች መንጋ በቅርቡ እስከሁለት ሚሊዮን ሄክታር በሚድርስ ቦታዎች ላይ የተዘሩትን አዝርዕት ሊያበላሽ እንደሚችል ተገምቷል። ይኽም በአገሪቱ ውስጥ ለእርሻ ተስማሚ ከሆኑ መሬቶች መካከል አንድ ስድሰተኛ የሚሆን ሲሆን ተምቹ የሚያደርሰው ጥፋት የረሃቡንና የድርቁን ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ሊያስፋፋው ይችላል ተብሎ ተሰግቷል። ተምቹ በሰዓት ከ 100 ኪሎ ሜትር በላይ የመብረርና በአንድ ጊዜ 1500 እስከ 2000 እንቁላል የመፈልፈል አቅም እንዳለው ባለሙያዎች ይናገራሉ። በወያኔ የእርሻና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስተር ተምቹን ለማጥፋት የተደረገው ጥረት የተወሰነ ውጤት ቢኖረውም ተምቹን ለመቆጣጠር ያልተቻለ በመሆኑ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ይገኛል።

የሕወሓት መንግስትን ከድተው በኤርትራ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ኃይልን የተቀላቀሉት ወታደሮች ምስጢር ማውጣት ጀመሩ source zhabesha



የሕወሓት መንግስትን ከድተው በኤርትራ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ኃይልን የተቀላቀሉት ወታደሮች ምስጢር ማውጣት ጀመሩ