Friday, September 15, 2017

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ጥቃት አሁንም እንደቀጠለ ነው source zhebsha

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እየፈጸመ ያለው ጥቃት አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉ ታወቀ፡፡ ከተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንዳመለከቱት፣ በሶማሌ ክልል እና በኦሮሚያ አዋሳኝ ድንበሮች ላይ ከባድ ውጥረት አለ፡፡ ውጥረቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መሔዱን የገለጹት የአካባቢው የዓይን እማኞች፣ በተለይ በሶማሌ ክልል የሚኖሩ የኦሮሞ ተወላጆችን የማፈናቀል ድርጊት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን እማኞቹ አክለው ተናግረዋል፡፡

ልዩ ኃይል የተባለው የሶማሌ ክልል ፖሊስ ህወሓት ለክልሉ ፕሬዚዳንት ለአቶ አብዲ በሚሰጠው ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሚመራ ሲሆን፣ ልዩ ፖሊሱ በንጹኃን ሰዎች ላይ ግድያ እንዲፈጽም እየተደረገ ያለውም በህወሓት ሴራ ሆን ተብሎ እንደሆነ ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ህወሓት በኦሮሞ እና በኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝብ መካከል ግጭት እንዳለ በማስመሰል የፖለቲካ ጨዋታ ለመጫወት እየሞከረ መሆኑንም ታዛበዎች ይናገራሉ፡፡ ‹‹ድርጊቱ የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ ውጤት ነው፡፡›› ያሉት ታዛቢዎቹ፣ ህወሓት በመጨረሻው ሰዓት በሀገሪቱ ላይ የእርስ በእርስ ግጭት እንዲፈጠር እንደሚፈልግም ያክላሉ-ታዛቢዎቹ፡፡

በምስራቅ ኢትዮጵያ ሐረርጌ ልዩ ስሙ ሜኢሶ በተባለው አካባቢ ያለው ውጥረት አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይልም ደረስ መጣ እያለ ጥቃት እንደሚፈጽም ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ግጭት ተከስቶባቸዋል በተባሉ የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልል አዋሳኝ ድንበሮች ላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ሰፍረዋል ቢባልም፤ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ግን አሳቻ ሰዓት እየጠበቀ ጥቃት እንደሚፈጽም ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

የህወሓት አጋዚ ወታደሮች ሐረር ውስጥ ግድያ ፈጸሙ source zhebesha

በሐረር የተሰማራው የህወሓት አጋዚ ሰራዊት ግድያ ፈጸመ፡፡ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እየፈጸመ ያለውን አሰቃቂ ጥቃት ለመቃወም በሐረር ከትላንት ጀምሮ ህዝባዊ ተቃውሞ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ዛሬም ቀጥሎ የዋለውን የህዝብ ተቃውሞ ተከትሎ የአጋዚ ወታደሮች ወደ ተቃውሞ አቅራቢዎች በቀጥታ በመተኮስ የሰው ህይወት መቅጠፋቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ የሟቾች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ አልታወቀም፡፡

ከሟቾች በተጨማሪም በጥይት ተመትተው የቆሰሉ ንጹኃን ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት መረጃዎች፣ ሐረር በከባድ ውጥረት ውስጥ እንደምትገኝም ተናግረዋል፡፡ በተለይ ሸዋ በር ተብሎ የሚጠራው የሐረር አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ሲሰማ እንደነበር ከዓይን እማኞች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ እስከ ምሽት ድረስ የቀጠለው የተኩስ ድምጽ ሐረርን የጦርነት ቀጠና እንዳስመሰላት የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በጅጅጋ ይኖሩ በነበሩ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ በፈጸመው ጥቃት ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ህይወት ተቀጥፏል፡፡ በዛሬው ዕለትም የሟቾች አስከሬን ወደ ሐረር ሲጓጓዝ እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ ትዕዛዝ ከጅጅጋ የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች ወደ ሐረር እየተወሰዱ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችም ሐረር ያለመጠለያ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት የሆነው ህወሓት፣ የሀገሪቱን ህዝብ እርስ በእርስ ለማባላት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ የገለጹት አስተያየት ሰጪዎች፣ ፈታኝ ጊዜ ላይ በመሆናችን በአንድነት ልንቆም ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
BBN news September 14, 2017

Tuesday, September 5, 2017

ጀዋር መሐመድ መንግስት በቴዲ አፍሮ ላይ እየወሰደ ያለውን ተደጋጋሚ ክልከላ አወገዘ source zhabesha

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ዳይሬክተር ጀዋር መሐመድ አምባገነኑ የሕወሓት መራሹ መንግስት በቴዲ አፍሮ ላይ በተደጋጋኢ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አወገዘ::
“ገዥው አካል ለቴዲ አፍሮ የሚያቀርበውን ትርዒት በተደጋጋሚ በመሰረዙ ተገቢ ያልሆነ እና ኢፍትሃዊ ውሳኔ ነው” ያለው ጀዋር በቴዲ ላይ መንግስት የሚወስደው ክልከላ “ይህ ሁሉ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነትን እና ዒላማው የኪነጥበብ ጥቃትን ስለሚያካትት ሁሉም ሊያወግዘው ይገባል” ሲል በፌስቡክ ገጹ ላይ ጽፏል::
ይህ የመንግስት ኪነጠብን የማፈን ተግባር አዲስ ነገር አይደለም አይደለም ያለው ጀዋር “መንግስት ከማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል የበለጠ ስነ-ጥበብ እና አርቲስቶችን ይፈራል::” ካለ በኋላ ሥርዓቱ በኦሮሞ አርቲስቶች ላይም ከስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የወሰደውን ጥቃት ጠቅሷል::

እንደጀዋር ገለጻ ሕወሓት መራሹ መንግስት ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ብዙ የኦሮሞ አርቲስቶችን ገድሏል፣ አስሯል እና ከሃገር እንዲሰደዱ አድርጓል::

ኦነግ በኦሮሚያ የሚደረገውን አድማና ትግል እየመራ መሆኑን አስታወቀ source zhabesha

ዋዜማ ራዲዮ- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በቅርቡ የተደረገውን ቤት የመቀመጥ አድማ ጨምሮ በኦሮሚያ ወጣቶች በአፋኙ ስርዓት ላይ የሚያደርጉትን ትግል ከፊት ሆኜ እየመራሁት ነው ሲል አስታወቀ።
ድርጅቱ በኤርትራ አስመራ ለአስር ቀናት ያደረገውን ጉባዔ ሲያጠቃልል ባወጣው መግለጫ የኦነግ ክንፍ የሆነው የኦሮሞ ወጣቶች ክንፍ (ቄሮ) እያካሄደ ያለው ትግል ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡን አስምሮበታል።
ኦነግ ለቄሮ የሚያደርገውን ድጋፍ በሶስት እጥፍ በማሳደግ በቀጣዮቹ ወራት በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት ለማስወገድ እንደሚንቀሳቀስ ተናግሯል።
ለኦሮሞ ነፃነት የሚታገሉ ድርጅቶች ሁሉ ከጎኑ እንዲሰለፉ የጠየቀው ኦነግ የኦሮሞ ነፃ አውጪ ጦርን ወደተግባር ለማስገባት የገንዘብ የቁሳቁስና የሰው ሀይል አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ለማሰደግ እየሰራሁ ነው ብሏል። ደጋፊዎቹም ለዚህ እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል።
የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ የጠየውቀው መግለጫው ከሌሎች ከተጨቆኑ የኢትዮጵያ ብሄሮች ጋር ለመተባበር ዝግጁ ነኝ ብሏል።
አስመራ የሚገኘው ኦነግ ከሶስቱ ዋና ዋና የኦነግ አንጃዎች አንዱ ሲሆን በአቶ ዳውድ ኢብሳ ይመራል።
በቅርቡ በኦሮሚያ የተደረገውንም ሆነ ሌሎች አድማና አመፃችን በማስተባበር በውጪ ሀገር ያሉ አክቲቪስቶች በተለይም የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አስኪያጅ ጃዋር መሀመድ ሀላፊነቱን ወስዶ ሲሰራ መቆየቱ ይታወቃል።