Friday, September 23, 2016

መስከረም 11—2009 ዓ/ም— በደ/ብርሃን ዩኒቨርስቲ የአድሀሪው ወያኔ መድረክ መሪዎች በእምባ ሲራጩ የዋሉበት ቀን




Bilderesultat for debre berhan university






መስከረም 11—2009 ዓ/ም— በደ/ብርሃን ዩኒቨርስቲ የአድሀሪው ወያኔ መድረክ መሪዎች በእምባ ሲራጩ የዋሉበት ቀን 3ኛ ቀኑን ያስቆጠረው የወያኔ የከፍተኛ ት/ት ተቋማት ምሁራንና ሰራተኞችን አትኩሮት የማስቀየስ የውይይት መድረክ ዛሬ ብዙዎችን በእምባ ሲያራጭ ውሏል።
በተለይም በደ/ብርሃን ዪኒቨርስቲ በወያኔ ካድሪዎችና አጎብጓቢዎች የተመራው መድረክ ሳያምኑበትና ውስጣቸው ሳይቀበለው በአረመኔዎቹ የድርጅቱ ከኛ በላይ ላሳር ባዮች የተሰጣቸውን ተልዕኮ በዪኒቨርስቲው ማህበረሰብ ላይ ለመጫን የሚሞክሩትን የመድረኩመሪዎቹን ሳይቀር አስለቅሷል።
ነገሩ እንዲህ ነው በዪኒቨርስቲው የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ስር በተማሪዎች መኝታ ቤት ኦፊሰርነት የምትሰራው ወጣት መልካም በአማራነቷ የምትኮራ በትውልዷ ጎጃሜ ናት።ሆኖም ይህን እንዝህላል መንግስት/መንግስት ስለው ይከብደኛል ይህን የደደብ ራስ ወዳዶች የዘራፊ ባንዳዎች ጥርቅም/ተቃውመው የህብረተሰቡን ጥያቄ አንግበው ወደ አደባባዮች የወጡ 4 ወንድሞቿ 4 የአጎቶቿ ልጆች በድምሩ 8 የቤተሰቧ አባላት የደረሱበት አልታወቀም።
ይህንንናሌሎች መብታቸውን ለመጠየቅ በሚል ወደ አደባባይ ወጥተው የነበሩ የህዝብ ልጆች በህዝብ ደም በደነደነው ወያኔ ሰለባ መሆናቸውን ጠቅሳ ፍረዱኝ ቤተሰቦቼን መልሱልኝ ፍትህ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማለቷ ነበር መላውን ተሰብሳቢ በእንባ ያራጨው። መድረኩን ሲመሩ የነበሩት የዩኒቨርስቲው ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ባዪ ጌታሁን እና የጤና ኢንስቲቲዪት ዳይሬክተርና መምህሯ ወይዘሮ ሶደሬም ሲቃ እየተነነቃቸው የእንባ ዘለላ ከፊታቸው ዱብ ዱብ ሲል ታይተዋል።
ከ110 በላይ ተሰብሳቢዎችን ሲመሩ የነበሩት እነዚሁ ሰዎችም መሪ ተብዬው ደንባራው ኃ/ማሪያም/ስሙን ሞት ይጥራውና/በግብታዊነት የተናገረውን የእርምጃ ይወሰድ ትዕዛዝ ከማውገዝም በሻገር አንቀበለውም እኛም አናምንበትም ሲሉ አቋማቸውን አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያውያን ደም መቼም ደመ ከልብ ሆኖ አይቀርም!!! እንዋጋለን በዳዮቻችንን እንፋረዳለን!!! ትግሉ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!! ድል ለሰፊው የሃገሬ ህዝብ!!!

No comments:

Post a Comment