Saturday, September 24, 2016

የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሉ ኣምባገነንና ኣሮጌ ስርዓቶችን ለማስወገድ ኣዲስ ኣይደለም። ሕወሓት መራሹን ኣገዛዝ እስካልጣልን ዘንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሰላምና ነጻነት አናገኝም።



ሕዝቤ ሆይ :- ሕወሓት መራሹን ኣገዛዝ እስካልጣልን ዘንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሰላምና ነጻነት አናገኝም። የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሉ ኣምባገነንና ኣሮጌ ስርዓቶችን ለማስወገድ ኣዲስ ኣይደለም።
Image may contain: 3 people , text
ሕዝቤ ሆይ :- ሕወሓት መራሹን ኣገዛዝ እስካልጣልን ዘንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሰላምና ነጻነት አናገኝም።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ሕወሓት ወንጀለኛ ነው። ነጋሪ ኣንፈልግም። አሁን የሚያስፈልገው ሕዝቡን በጋራ ኣያይዞ ሕወሓት የሚባለውን ማፊያ መሰሪ በቀለኛ ጸረ ሰላምና ጸ ሕዝብ ሰው በላ ኣገዛዝ ማስወገድ ብቻና ብቻ ነው። ለዚህም ነው የስርዓት ለውጥ ያስፈልጋል ብለን እየጮኽን ያለው።ለዚህም ነው ሕዝባዊ መንግስት ያስፈልጋል ብለን እየጮኽን ያለነው።ለዚህም ነው በዘርና በመንደር መቧደን ቆሞ በጋራ የሕዝቦች እኩልነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያ ትመስረት እያልን የምንጮኸው።ለዚህም ነው በኣንድነት በባንድራ በሃገር ወዳድነት ሽፋን ሕዝብ እንዳይረገጥ በጩኸት በማስፈራራት ከኛ በላይ ላሳር የሚል ስሜታዊ የጡዘት ፖለቲካ ይቁም እያልን ኣምባገነነኦችን ለሜጣል ላሌመፍጠርም እየታገልን ያለነው። ለዚህም ነው ኢትዮጵያውያን በመላው ሃገሪቱ ተዘዋውረው የመስራት መብታቸው ይከበት ብሌን የምንታገለው።ለዚህም ነው ግድያና እስር ቆሞ በመከባበርና በመቻቻል ፖለቲካ ኣገር ትመራ ብለን የምንጮኸው በኣጠቃላይ ለሕዝብ ነጻነትና መብት መከበር ስኬት ለፖለቲካና ኢኮኖሚ ሰላም መረጋገጥ ሕወሓት መወገድ ኣለበት።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሉ ኣምባገነንና ኣሮጌ ስርዓቶችን ለማስወገድ ኣዲስ ኣይደለም። በደሃው ገበሬ ላብ ሲኖር የነበረውን የጥቂት መሳፍንቶችና የራስ ተፈሪ መኮንንን ፊውዳላዊ ጨካኝ የሆነ ኣገዛዝ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከዳር በመንቀሳቀስ ራሱን ንጉስ ኣድርጎ የሾመውን ኣገዛዝ ያስወገደ ቢሆንም በጣልቃ ገብነት የመጡት ወታደራዊ መኮንኖችም ለሃገርና ለወገን ይጠቅማሉ የተባሉ ዜጎችን ደም በመጠጣት በማሰር በማሳደድ ታሪክ ይቅር የማይለው ግፍ በመስራት በሃገር ኣንድነትና በባንድራ ሽፋን በግዳጅ ወጣቱን ለስልጣናቸው ማቆያ በመማገድ ሲተጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዝም ብሎ ኣላየም በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በተከፈሉ መስዋትነቶች ደርግ ላይነሳ የተንኮታኮተ ሲሆን ይህን ተከትሎ ስልጣን ላይ የወጡት ዘረኛ ዘራፊ መንደርተኛ ተሳዳቢ ገዳይ እጅግ ጨካኝና በመሳሪያ ብቻ የሚተማመኑ የሕወሓት ኣምባገነን ኣመራሮች ስልጣኑን ተቆጣጥረው በዲሞክራሲና በልማት ሽፋን ሕዝቦችን ለከፍተኛ ሰቆቃ ከመዳረጋቸውም በላይ ኢትዮጵያ በዘመኗ ተፈራርቀው የነበሩ መንግስታት ያልሰሩትን ወንጀሎች በሕወሓት እየተሰሩ ታሪክ ይቅር የማይለው ግፍ በዘረኞች እየተፈጸመ ነው።
ስለዚህ እነዚህም ጨካኖች በሰለጠነ ዘመን ያልሰለጠኑ ዘረኞችን ተባብረን ማስወገድና ለመጭው ትውልድ መብት ነጻነት እና እኩልነት የተረጋገጠባትን ኢትዮጵያ ለማስረከብ የዜግነት ድርሻችንን እንወጣ። #ምንሊክሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment