ለዛሬ ተቀይሮ የነበረው የኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የፍርድ ቤት ቀጠሮ ለስድስተኛ ጊዜ ወደ መስከረም 18 ቀን 2009 ዓ.ም. ተዛወረ። በጎንደርና በባህር ዳር በቤት ውስጥ የመዋል አድማው እደቀጠለ ነው።
ከኮሎኔል ደመቀ ቀጠሮ ጋር ተያይዞ የግፍ ሒደቱን [የፍርድ ሒደቱን ላለማለት ነው] ለመከታተል የወጡ የጎንደር ወጣቶችን ለመግደልና ለማሳደድ የትግራይ TPLF ወታደሮች ከተማውን አጥለቅልቀውታል።
በተያያዘ ዜና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፋሽስት ወያኔ ሊያካሂደው የነበረው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ጉባኤ ሳይካሄድ ቀርቷል። ጉባኤው የተቋረጠው ሁሉም የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህራን ስብሰባውን ቦይኮት በማድረጋቸው ነው። ሁሉም አማራ በአንድነት የአባቶቹን የጀግንነት ታሪክ ይደግማል። ከታች ያለው ፎቶ የትግራይ ነፍሰ በላ ወታደሮች በጎንደር ከተማ የንጹሀንን ደም ለማፍሰው ሲዘዋወሩ የሚያሳይ ነው።
No comments:
Post a Comment