Friday, December 22, 2017

የኦሮምያ ክልል በአ/ አ ከተማ ላይ ያለውን ልዩ ጥቅም በሚመለከት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ በኦህዴድ አባላት ተቃውሞ ምክንያት ለሌላ ጊዜ ተዛወረ።

የኦሮምያ ክልል በአ/ አ ከተማ ላይ ያለውን ልዩ ጥቅም በሚመለከት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ የህዝብ አስተያየት ለማሰባሰብ በዛሬው ዕለት የተጠራው ስብሰባ በዋንኛነት በኦህዴድ አባላት ተቃውሞ ምክንያት ለሌላ ጊዜ ተዛወረ።

ዛሬ ጠዋት የፓርላማው የህግና ፍትህ አስተዳደር እና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቋሚ ኮምቴዎች የህዝብ አስተያየት ለማሰባሰብ የጠሩት ሲሆን አብዛኛዎቹ የኦህዴድ አባላት ህዝባችን ችግር ላይ ባለበትና ከስር ጀምሮ በቂ ውይይት ባልተደረገበት ሁኔታ ይህ ስብሰባ መጠራት የለበትም የሚል አቋም በመያዛቸው በሻይ ዕረፍት ስም ስብሰባው ከአንድ ሰዓት በላይ ተቋርጦ ለማግባባት ቢሞከርም ሳይሳካ ቀርቷል።
በስብሰባው ላይ የተገኙትና የመጀመሪያውን የተቃውሞ ደምጵ ያሰሙት የኦሮምያ ኮምኒኬሽን ጵ/ ቤት ሀላፊ አቶ አዲሱ አረጋ ባደረጉት ንግግር ከ600 ሺህ በላይ ህዝባችን በኦሮምያና ሶማሌ ግጭት በተፈናቀለበትና በየቦታው ግጭቶች በቀጠሉበት፣ ረቂቅ አዋጁም ህዝባችን ባልተወያየበት ሁኔታ ይህ ስብሰባ መጠራት እንደሌለበት በመጥቀስ ለሌላ ግዜ እንዲተላለፍ ጠይቀዋል። ይህን የአቶ አዲሱ ንግግር አብዛኛው የኦህዴድ የፓርላማ አባላት በጭብጨባ ድጋፍ ሰጥተዋል።
ከኢህአዴግ ስብሰባ አቋርጠው በድንገት የተገኙት አቶ አባዱላ ገመዳ ከአብዛኛው የኦህዴድ አባላት በተቃራኒ ስብሰባው እንዲቀጥል ሀሳብ ሰጥተዋል። ረቂቅ አዋጁ የቀረበው ለማዳበር እንጅ ለማጵደቅ አለመሆኑን፣ ሌሎች መድረኮች ወደፊት እንደሚኖሩና መወያየቱ ጥቅም እንጅ ጉዳት እንደሌለው ያደረጉት ገለጳ የአባላቱን የጉምጉምታ ተቃውሞ አስከትሎአል።
እንደአቶ አባዱላ ስብሰባ አቋርጠው የተገኙት አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ ባቀረቡት ሀሳብ መሰረት ስብሰባው ለሻይ ዕረፍት ተበትኖ ከአንድ ሰአት በላይ ቆይቷል። በዝህ ሰዓት የኦህዴድ የፓርላማ አባላት አቶ አባዱላ ባሉበት በኦሮምኛ ቋንቋ የማግባቢያ ስብሰባ የተደረገ ቢሆንም አባላቱን ሀሳባቸውን ማስቀየር አልተቻለም።
በአካሄድ ውዝግብ እስከጠዋቱ 5:30 ሰአት በመቀጠሉ ጊዜም ስለሌለ በሚል የቋሚ ኮምቴው ሰብሳቢ ወደሌላ ቀን እንዲዛወር ያቀረቡት ሀሳብ ተቀባይነት በማግኘቱ ስብሰባው ተበትኗል

የኢትዮጵያውያን ህይወት ዋጋ ምን ያህል ወርዷል? – ከአንተነህ መርዕድ source zhabesha

በእግዚአብሄር አምሳል የተፈጠረ ሰው ህይወት ክቡር ነው። ከዚያም አልፎ ህይወት ያለውን ነገር ሁሉ በከንቱ አለማጥፋት በተፈጥሮ ህሊናችን ውስጥ ህግ ሆኖ ስለተቀመጠም ነው የሰው ብቻ ሳይሆን የሌላም ፍጥረት ህይወቱ አለአግባብ በጭካኔ ሲቀጠፍ የሚዘገንነን። የሰውን ህይወት ለማጥፋት መጀመርያ የራስን ህሊና ፍርድ መጣስና ማቆሸሽን ይጠይቃል። ዛሬ በኢትዮጵያ በየቀኑ በጭካኔ የሚቀጠፉ ለጋ ወጣቶች፣ ማምለጥ የማይችሉ ህፃናት፣ አዛውንት አባቶችና እናቶችን ለሚመመለከት፣ ብሎም ለሚያስብ ንፁህ ህሊና ላለው እረፍት የሚነሳ ነው።
በተለይ ባለፉት አምሳ ዓመታት በግፍ የጠፋው ኢትዮጵያውያን ህይወት እጅግ የሚዘገንን ነው። አዎ አባቶቻችን የውጭ ወራሪን ለመከላከልና በነፃነት ለመኖር ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍለዋል። አምባገነን የሆኑ የየአካባቢው መሳፍንት ግዛታቸውንና ሃብታቸውን ለማስፋት በሚያደርጉት ጦርነት የብዙ ኢትዮጵያውያን ህይወት ተቀጥፏል፣ ለእድገት ይውል የነበረ ጉልበትና ሃብት ባክኗል። በያዝነው አምሳ ዓመት ግን ሶማልያ ጋር በተደረገው ጦርነት ካለቁት ወገኖቻችን ውጭ በብዙ መቶ ሺህ ያለቁት ለጋ ዜጎች ምክንያት የምናደርገው የእርስ በርስ ፍጅት ውጤት ነው። በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የሰዎች ብቻ ሳይሆን የእንስሳትም ህይወት በህግ በሚከበርበት ዓለም እነሆ በዚች ደቂቃ ብዙ የኢትዮጵያውያን ህይወት በራሳችን ግፈኞች ይቀጠፋሉ። አባቶቻችን ያስጠበቁት ዳር ድንበር ፈርሶ የድንበር ጦርነቱ በሱማልያና በኦሮሞ፣ በአፋርና በአማራ፣ በትግራይና በአማራ በሚል “መከላከያ ሰራዊት” በመሃል የዕብድ ገለጋይ ሆኖ ህዝቡን እየጨረሰና እያጫረሰ ነው።
በ1966 አብዮት ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ጭቆናን አስወግደው ዴሞክራሲና ፍትህ የሰፈነባት አገር እንድትሆን ያደረጉት ምኞትና ትግል ለስልጣን በቋመጡ ቡድኖች ብሩህ ልጆቿ በግፍ ተጨፈጨፉ። ብርቅ ልጆቿን የገደሉና ያስገደሉ የደርግ ባለስልጣናት ሆኑ በተቃዋሚነት ተሰልፈው የነበሩ መካን ፖለቲከኞች በድርጊታቸው መፀፀት ቀርቶ ከደሙ ንፁህ ነኝ የሚል መጽሃፍ እያሳተሙ፣ ግድያውን በሌላ እያላከኩ የተቃዋሚነት ካባ ደርበው ህሊና አጥተው፣አሁንም በፖለቲካው መድረክ አለን ሲሉ ይዘገንናል። ከደርግ ውድቀት ማግስት ሌላ ተስፋ ይኖር ይሆን ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ካለፉት የባሰው ዘረኛና ጨካኝ አገዛዝ ገጥሞት አሁንም አገሪቱ የልጆቿ ደም እንደ ጅረት እየፈሰሰ ነው። የኢትዮጵያውያን ህይወት ወደ ቁጥር ተቀይሮ ይህን ያህል ሰው ሞተ የሚል ዜና መስማት ከመልመዳችን የተነሳ ቁጭት መፍጠሩ ቀርቷል።
ዛሬ የንፁሃን ደም በከፍተኛ ሁኔታ በሚፈስበት ሰዓት ከወደ ዘ ሄግ (The Hague)ብዙ ለጋ ወጣቶችን የጨፈጨፈውና ያስጨፈፀፈው  መቶ አለቃ እሸቱ የእድሜልክ እስራት እንደተፈረደበት ሰምተናል። ወንጀሉ በተፈፀመ በአርባ ዓመቱ ቢያንስ በአንድ ሰው ላይ ፍትህ ተበይኗል። መቶ አለቃ እሸቱ ወንጅሉን አልፈፀምሁም ብሎ እንደጓደኞቹ ክዷል። ለበርካታ ዓመታት በብርቱ ጥንቃቄ ምርመራውን ሲያካሂዱ የነበሩት የሆላንድ ፖሊሶችና የህግ ባለሙያዎች የማያጠራጥር መረጃ በፊቱ አቅርበው፣ ተጠቂዎችና ቤተሰቦቻቸው በሚገባ መስክረውበትም በወንጀሉ አልተፀፀተም። እሱ ጠበቃ ቆሞለት እምነትና ክህደቱን እንኳ እንዲያቀርብ ሲፈቀድለት እሱ በግፍ የጨፈጨፋቸው ወጣቶች ግን በገመድ እየታነቁ አንድ ጉድጓድ ውስጥ ነው የተጣሉት። ቤተሰቦቻቸው እርም ለማውጣት እድል አላገኙም። ብዙዎቹ የተገደሉት በእኔ እድሜ ዙርያ ያሉ አንዳንዶችንም በሚገባ የማውቃቸው ለጋ ኢትዮጵያውያን ናቸው። በጊዜው በቦታው ባለመገኘቴ ብተርፍም ደብረ ማርቆስ ወህኒ ቤት ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጓሮ የጅምላ መቃብራቸውን ለሁለት ዓመት ተኩል በየቀኑ አይቼዋለሁ። በጊዜው ወህኒ ቤት የነበሩ ጓደኞቼና የተገደሉትን እንዲቀብሩ የተደረጉት ነጋ መሃመድና ሁለት የሻንቅላ (ጉሙዝ) ብሄረሰብ አባላት ሰጠኝ ማንጓና ቡሃ ቀኜ የነገሩንን ላካፍላችሁ። እለቱ ነሃሴ 8 ቀን 1970 ዓ ም ነው። ቀን በደብረማርቆስ ወህኒ ቤት ሚካኤል ቤተክርስቲያን ጀርባ አንድ ሰፊ ጉድጓድ ሲቆፈር ዋለ። ሁኔታውን በተጠራጠሩ እስረኞች ገፅታ ላይ የሃዘን ድባብ አጥልቷል። ከቀኑ አስር ሰዓት እስረኛው ሁሉ ወደ ክፍሉ እንዲገባ ተደረገ። ሁሉም ጀሮውን አቅንቶ ይጠባበቅ ጀመር። ከምሽቱ አስራ አንድ ሰዓት ተኩል ሲሆን አንድ ፖሊስ የበር መክፈቻ ቁልፎችን ሌላው ደግሞ ሶስት ሜትር እርዝመት ያላቸው ጠንካራ ገመዶች ይዘው በመከታተል ወደ እስረኛ ክፍሎች አመሩ። የብረት ፍርግርግ ባለው መስኮት ፖሊሱ ተጠግቶ የእስረኛውን ስም ይጠራና ለካቦው(በክፍሉ ወስጣ ላለ የእስረኞች አለቃ) ገመድ አቀብሎ የኋሊት እንዲያስረው ያዝዛል። ስማቸው የሚጠራ ለጋ ወጣቶች ሲወጡ ስርዓቱን የሚያወግዝ፣ ቀሪ ጓዶቻቸውን የሚያጽናና መፈክርና መዝሙር ሲያሰሙ አንዳች ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር። እንዲህ እያደረጉ ከየክፍሉ በጠቅላላው 75 ወጣቶችን ጉድጓዱ ጥግ ወስደው በገመድ በማነቅ ማጅራታቸውን እየመቱ ጣሏቸው። እሸቱ ዓለሙ ረጂም ጥቁር ካፖርት ለብሶ እያንዳንዱ ላይ እርምጃ መወሰዱን ቆሞ ያረጋግጥ ነበር። ብዙዎቹ ወደገደል ሲጨመሩ ሳይሞቱ ከነህይወታቸው ነበር።በተለይ ሲያምረኝ ደረሰ የተባለው እስረኛ ግዙፍም ስለነበር አልሞት ብሎ እየተናገረ ወደ ጉድጓዱ መወርወሩን ቀባሪዎቹ በምሬ ይገልፁ ነበር። በሁኔታው ዘግናኝነት የተረበሹት ቀባሪዎች ለበርካታ ቀናት እህል መብላት ሆነ ከሰው መነጋገር ከብዷቸው ሰነበቱ። ታደለ ያዴታና ትኩዬ ልጅዓለም የተባሉ እስረኞች በነጋታው “ፍርድ አልተሰጠንም እኮ” ብለው ሲያመለክቱ “ ኑ ፍርድ እንስጣችሁ” ብለው ወስደው ገደሉዋቸው። ከተፈታሁ በኋላ የእነዚያን ጓደኞቼንና ዘመዶቼን ደጋፊ የሌላቸው ወላጆች የማፅናናበት ቃል አልነበረኝም። ዐይን ውሃቸው የሃዘናቸውን ጥልቀት አድምቆ ያሳየኝ ነበርና።
በጊዜው አገሪቷ ውስጥ ከተካሄደው ጭፍጨፋ አንፃር የመቶ አለቃ  እሸቱን ድርሻ አቃልሎ የሚያይ ካለ ተሳስቷል። በጀርመን ለብዙ ሚሊዮን ሰዎች እልቂት ምክንያት የሆነው መሪው ሂትለር ቢሆንም እሱ ሞቶ ተባባሪዎቹ ዛሬ በየአሉበት እየተፈለጉ ዘጠና ዓመት ሞልቷቸው አንኳ ከፍርድ አላመለጡም። ለዛሬ የዘረኝነት ጭፍጨፋ ተዋናይ መሪው መለስ ዜናዊ ቢሞትም የንፁሃን ደም እጃቸው ላይ ያለው የመለስ ተከታዮችና የራዕዩ አስፈፃሚዎች እስከ እለተ ሞታቸው እየተሳደዱ ከፍርድ አያመልጡም።
እሸቱና ጓደኞቻቸው የገደሏቸው ወጣቶች ቢተርፉ ኖሮ ለወላጆቻቸው ሆነ ለአገራቸው ምን ያህል ይጠቅሙ እንደነበር ለመገመት ያንን የመከራ ጊዜ በተለያየ አጋጣሚ ተርፈው የተገኙ በርካታ አገር የጠቀሙ ኢትዮጵያውያንን በምሳሌነት ማቅረብ ቀላል ነው። መቶ አለቃ እሸቱና ጓደኞቹ ሊገድሏቸው ካወጧቸው ውስጥ የሶስት ጓደኖቼን ሁኔታ ባብራራ ጥሩ ምሳሌ ይሆናል። ሁለቱ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ናቸው። ባህርዳር ሆስፒታል አካባቢ በድሮ አጠራር ሽምብጥ ከሚባል ሰፈር ተከራይተው የሚማሩበት ቤት ሲፈተሽ የኢህአፓ ወረቀት ስለተገኘ በጥርጣሬ ተያዙ። ስለኢህአፓ የሚያውቁትነገር  አልነበራቸውም። ሌላው ባህርዳር ጥጥ ፋብሪካ ወዝ አደር ሲሆን ለሠራተኛው መብት ተቆርቋሪና ንቁ ተሳታፊ ስለሆነ ብቻ የታሰረ ነው። ደብረማርቆስና በየአውራጃው ዋና ከተሞች ግድያው የሚፈፀም ወቅትበንዱ ቀን ከባህርዳር ወህኒ ቤት በለሊቱ የሚገደሉት ወጣቶች ስም እየተጠራ የኋሊት እየታሰሩ መኪና ውስጥ ሲገቡ ሶስቱ ጓደኞቼም በአንድ መኪና ተጨመሩ። ሌሎችን እየጠሩ እያሰሩ ወደ ሌላ መኪና በሚያስገቡበት ጌዜ “እርስ በርሳችን እንፈታታና ለማምለጥ እንሞክር” የሚል ሃሳብ አንዱ ሲያቀርብ ሁሉም በጥሞና ሰምተው መተባበር አልተባበሩም። አብዛኞቹ በድንጋጤ ምክንያት ለመወሰን አልቻሉም። ጎን ለጎን የነበሩት ወዝ አደሩና ሌላው ጓደኛዬ ተፈታቱ። ፊት ለፊት ወንበር የነበረው ጓደኛዬ የሚተባበረው አጥቶ የኋሊት እንደታሰረ ተቀምጧል። አንድ ካድሬ ሽጉጡን አቀባብሎ መሃላቸው ሲቀመጥ ጋቤና ውስጥ ሾፌሩና ሌላው ገዳይ ክላሽ ይዘው ገቡ። እስረኞችን የያዙ መኪኖች ከወህኒ ቤቱ ወጥተው ወደ አባይ ማዶ አቀኑ። ድልድዩን ከተሻገሩ በኋላ መግደያው ቦታ ደርሰው የፊተኛው መኪና ሲቆም ሁሉም ቆሙ። እጁ የተፈታው ጓደኛዬ የታሰረ መስሎ ከቆየ በኋላ በቅፅበት ካድሬውን በቦክስ መትቶ ሽጉጡን ለመያዝ ተናነቀው። ካድሬው በደመነፍስ መተኮስ ሲጀምር ጓደኛዬ ተመትቶ ወደቀ። በዚህ መካከል ወዛደሩና ሌላው ጓደኛዬ ከመኪናው ወጥተው በየፊናቸው በጨለማ ወደ አባይ አፋፍ ሲሮጡ ጥይት በላያቸው ቢዘንብም በተዓምር ተረፉ። ተመትቶ የነበረው ጓደኛዬ ሲነቃ ከሌሎች መኪኖች ያሉ እስረኛ ጓደኞቹ እየተረሸኑ ነበር። ቀስ ብሎ ሳይታይ ከመኪናው በመውጣት አመለጠ።
ከዚያ ጭፍጨፋ የተረፉት ሁለቱ አገራቸው ውስጥ ትልቅ ሥራ እየሠሩ ናቸው። ሶስተኛው አሜሪካ ይኖራል። ሶስቱም ተርፈው የወላጆቻቸውን እንባ አብሰዋል፣ ጡረዋል፤ ወንድምና እህቶቻቸውን አስተምረዋል፣ ዘመዶቻቸውን ረድተዋል። ለብዙዎች አርአያ በመሆን አገራቸውን ጠቅመዋል። ይታያችሁ! ያ ሁሉ ወጣት ባይጨፈጨፍ፤ ህዝባችንና አገራችን አሁን ባሉበት አይገኙም ነበር። መቶ አለቃ እሸቱ ሆነ መላኩ ተፈራን የመሰሉ ጨካኝ ግለሰቦች አገሪቷን በብዙ ጎድተዋታል። ኢትዮጵያ በእኛ እድሜ ያጣቻቸውን ወጣቶቿን አንድ ጊዜ በዐይነ ህሊናችን እናስብ!
  • በደርግና በድርጅቶች የእርስ በርስ መጫረስ መቶ ሺዎች ሞተዋል፤
  • በኤርትራ ጦርነት ብዙ መቶ ሺዎች በረሃ ላይ ቀርተዋል፤
  • በትግራይ ተራራና ሸንተረር ሮጠው ያልጠገቡ ወጣቶችና ጎልማሶች ለብኩን ዓላማ ተጨፋጭፈዋል፤
  • በባድሜ ጦርነት ከሁለቱም ወገን መቶ ሺዎች አልቀዋል፤
  • ወያኔ ስልጣን ከያዘ ወዲህ ዘረኛ ፍላጎቱን ለማሟላትና ለመዝረፍ ሺዎችን በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች በጠራራ ፀሃይ ሲገድል፣ ሲያጋድል እናቶቻችን ከል ከመልበስ አልወጡም። ከዚያም አልፎ በልጆቻቸው ሬሳ ላይ እንዲቀመጡ የሚያደርግ ከናዚዎች ያልተናነሰ ዘረኛ ቡድን ነግሶባቸዋል።
  • በኢትዮጵያ ታሪክ ሆኖ የማያውቀው ዜጎች ከኖሩበት ቀዬ በመቶ ሺዎች ተፈናቅለዋል። ይህንንም ወያኔ በዋናነት የሚያከናውነው ተግባር ሆኗል።
  • ወታደሩ የአገሩን ድንበር ለሱዳን አስረክቦ መሃል አገር ወንድሞቹን ለመግደል በጥዋቱ በየዜጎቹ በር ዘብ የቆመበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
ባለፉት አምሳ ዓመታት አገር የሚገነቡ ሚሊዮን ልጆቿን በጨካኞች ግድያ ያጣች፤ ሺህ ሆስፒታል፣ ሺህ ዩኒቨርስቲ፣ ሺህ ግድብ፣ መቶ ሺህ ኪሎሜትሮች የመኪና መንገድና የባቡር ሃዲድ መገንባት የሚያስችል ሃብቷን ልጆቿ ለሚገደሉበት ጦር መሳርያ መግዣ አውላለች። ዘራፊ አምባገነን ገዥዎቿ የምዕራቡን ባንክ በገንዘቧ እስኪያጨናንቁ ተዘርፋለች። ቀሪ ዜጎቿም የሚላስ የሚቀመስ አጥተው ሞትን እንኳ በሰላም መጠባበቅ ተነፍገው ሲፈናቀሉ፣ ሲሰደዱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲገረፉ፤ ሞትን እየተመኙና የምፅዐትን ቀን እየጠበቁ ይኖራሉ።
መቶ አለቃ እሸቱ ወንጀሉን በፈጸመ በአርባ ዓመቱ ፍርዱን አግኝቷል። በሱ ጊዜ ትውልድ ላይ የፈረዱ ሁሉ ይዘገያል እንጂ ፍርዳቸውን ያገኛሉ። ጨካኝነትን በከፋ መልኩ እየተገበሩ ያሉ የአሁኖቹ ወያኔዎችና ተባባሪዎቻቸው በምንም ዓይነት ከፍርድ አያመልጡም። የዘመኑ ቴክኖሎጅ ምስጋና ይግባውና እያንዳንዷ ድርጊታቸው ተመዝግባ ተይዛለች። መሰላቸው እንጂ ዘርፈውና ገድለው የሚደበቁበት የዓለም ክፍል አይኖርም። እነሱ ያሰደዱት ኢትዮጵያዊ በሄዱበት ሁሉ አሳድዶ ለፍርድ ያቀርባቸዋል።
የትግራይ ህዝብና ልሂቃን ደጋግማችሁ ማሰብ ያለባችሁ ጉዳይ ቢኖር ህወሃት በትግራይ ህዝብ ስም ወንጀል የሚፈፅም መሆኑን ነው። እንዲሁም ተጠያቂዎቹ በድርጊቱ ቀጥተኛ ተሳታፊ የሆኑት ዘራፊና ጨፍጫፊዎች ከፍርድ የማያመልጡ ቢሆንም የትግራይን ህዝብ እንደከለላ በመጠቀማቸው ከቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ እየነጠሉት መሆኑንም ነው። ስለዚህ ይህን ዕውነት አሁን በግልፅ ማየት ከተሳናችሁና ሆነ ብላችሁም የህወሃትን ወንጀል መቃወም ካልቻላችሁ አደጋው ሰፊ ነው። የትግራይ ህዝብ ህወሃት ከመኖሩ በፊት ኢትይጵያዊ ነው። ወያኔ ከወደቀ በኋላም ኢትዮጵያዊ ሆኖ ይቀጥላል። ከሚወድቅ ስርዓት ጋር ማበር ግን ዋጋ የሚያስከፍል ይሆናል። በወያኔ የምትጠፋው ኢትዮጵያ የናንተም መሆኗን አትዘንጉ። ጉዳቷም እንደሚጎዳችሁ እወቁ።
ኢትዮጵያዊ ሆነህ ሃቅም ያለህ ዜጋ መገደል፣ መታሰር፣ መገረፍ፣ መዘረፍ፣ መዋረድ እንዲበቃ ከፈለግህ እርስ በርስ መጎነታተሉን፣ ወያኔ በሰፋልህ የዘር ቀረጢት ለመግባት መሽቀዳደሙንና የጥላቻ ፕሮፓጋንዳሕን ተውና የሃገርም የአንተም ጠላት የሆነ አምባገነን ስርዓትን ለመጣል ከወንድሞችህ ጋር ሆነህ ታገል። ለዚች አገር ውድቀትና በዚህ ደረጃ መገኘት አምባገነን ገዥዎቿ ብቻ ሳይሆኑ ለእነሱ አሳልፈን የሰጠናትና እስካሁን እንዲፈነጩ የፈቀድን እኛም በመሆናችን ተጠያቂነት አለብን። ከሃጤያቱ ነፃ መሆን የምንችለው አምባገነን ስርዓትን ለመጣል የተግባር አስተዋፆ ስናደርግ ብቻ ነው። ጊዜህን በወሬና በምሬት ከምታሳልፍ በተግባር ተሳተፍ። ለልጅህ የምታስረክበው ሃገር ሆነ በጎ ታሪክ የለህም። ሃገርህንም ታሪክህንም በጥሩ መጠበቅ የምትችለው ራስህ ብቻ ነህ።
ከተፈጥሮ ሞት ውጭ የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሞት በፍጥነት መቆም አለበት። በዝምታችን፣ በስንፍናችን፣ በክፍፍላችን፣ በትምክህታችን፣ በዘረኝነታችን ምክንያት የኢትዮጵያውያን ህይወት በየቀኑ እየተቀጠፈ ነው። ኢትዮጵያዊ ላይ ሲደርስ የሰው ህይወት ዋጋ ረክሷል። እኛ ስላረከስነው ዓለምም እንስሳ የሞተ ያህል አላየውም። “ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ ባለእዳ አይቀበለውም” እንደተባለው እኛ ባለቤቶቹ ለህይወታችን ክብር አልሰጠነውም። እኛ ስናከብረው ሌላውም ያከብረዋል። ሶማሌው ሲገደል ሶማሌ በመጮህ፣ አማራው ሲገደል አማራው በመሰለፍ፣ ኦሮሞው ሲገደል ኦሮሞው በማመፅ፣ ትግሬው ሲገደል ትግሬው ደም በመመለስ የሰውን ክቡር ህይወት ለፖለቲካ ፍጆታ አርክሰን ከማውረዳችን በላይ ወያኔን ዘረኛ ብለን ለመኮነን የሞራል ብቃት አሳጥቶናል። ለሰው ልጅ ክቡር ህይወት በተለይም ለኢትዮጵያዊ  ህይወት ክብር ሳንሰጥ፤ ራሳችንን የለውጥ አካል ማድረግ ጨርሶ ቀልድ ነው። ወንጀልም ነው። ከጨፍጫፊው ወያኔና ከነመቶ አለቃ እሸቱ የተሻለ ልዕልና ለመጎናፀፍ የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ህይወት ሊቆጨንና ሊያነሳሳን ይገባል። በዚህን ጊዜ ነው የኢትዮጵያውያን ህይወት ክቡር የሚሆነውና ግድያ የሚቆመው።

Monday, December 18, 2017

የሶማሌ ክልል ር/መስተዳድር ለተፈናቃዮች ያደረጉት ጥሪ Deutsche Welle (DW) amharic news

በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ከወራት በፊት አንስቶ ግጭት ተከስቶ እንደነበር ይታወሳል። በሁለቱ ክልሎች መካከል ያለው ወሰን በትክክል ባለመለታየቱ በተነሳው ግጭት በሁለቱም ክልሎች በመቶዎች የሚገመቱ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ እና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩም መፈናቀላችው ይታወቃል።

«ይህ ሁሉ ሰው ሲፈናቀል የፌዴራል መንግሥት የት ነበር?»

በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች በተከሰተው ግጭት የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች ወደነበሩበት እንዲመለሱ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር ከጥቂት ቀናት በፊት ጥሪ አቅርበዋል። ተፈናቃዮች ወደ ሶማሌ ክልል እንዲመለሱ የቀረበው ጥሪ በርግጥ ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ነው አይደለም፣ እንዲመለሱ የሚያስችሉ ሁኔታዎች አሉ የሉም ፣ እነዚህ ጥያቄዎች ብዙ እያነጋገሩ ነው። በዚሁ ጉዳይ ላይ እኛም ውይይት አካሂደንበታል።
አርያም ተክሌ
ማንተጋፍቶት ስለሺ 

አበራ የማነአብ – ከመኢሶን እስከ 17 የወያኔ እስር ቤት ስቃይ | አሁንስ? | ያልተነገሩ ታሪኮችን የያዘ ልዩ ቃለምልልስ – አያምልጥዎ source zhabesha


 
 e

  
l
hare

አበራ የማነአብ – ከመኢሶን እስከ 17 የወያኔ እስር ቤት ስቃይ | አሁንስ? | ያልተነገሩ ታሪኮችን የያዘ ልዩ ቃለምልልስ – አያምልጥዎ

Monday, November 20, 2017

የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር አቶ ነአምን ዘለቀ ከአዲሱ የወያኔ የጸጥታ ዕቅድ ጀርባ ያለውን ሴራ አጋለጡ (ሊታይ የሚገባው) source zehabesha

(ዘ-ሐበሻ) የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር የሆኑት አቶ ነአምን ዘለቀ ሰሞኑን በተለያዩ ሚዲያዎች ሾልኮ በመውጣት ለሕዝብ ስለደረሰው ከአዲሱ የወያኔ የጸጥታ ዕቅድ ሰነድ ጀርባ ያለውን ሴራ አጋለጡ:: የድርጅታቸው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ የሆኑት አቶ ነአምን ከአርበኞች ግንቦት 7 ራድዮ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ሰነዱን አስታከው ሕዝብ ማወቅ አለባቸው ያሏቸውን ነጥቦች በስፋት አስቀምጠውታል:: ተመልክተው ለወዳጆችዎ ያካፍሉት ዘንድ ዘ-ሐበሻ ጥሪዋን ታቀርባለች::


ጎንደር በሚገኙት የወያኔ ባለስልጣናት ላይ ጥቃት ተሰነዘረ | አዘዞ ወታደራዊ ካምፕ እና ኤርፖርት መስመር ታምሷል! source zehabesha

ለጥቃቱ በህቡእ የቆየ ድርጅት ሃላፊነት ወስዷል!
ሙሉነህ ዮሐንስ
ቅዳሜ ህዳር 9 2010 እኩለ ሌሊት ሲሆን ጎንደር አዘዞ ውስጥ በተመሳሳይ ሰአት በሁለት ቦታ በወያኔ ላይ እርምጃ መውሰዱን በህቡ ስንቀሳቀስ ቆይቻለሁ ያለ ድርጅት በላከልን መልእክት አሳወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፓርቲ(ኢብፓ)/Ethiopian National Party የላከውን መግለጫ ዝርዝሩን እንደሚከተለው አቅርበነዋል።
የኢብፓ ወታደራዊ ክንፍ ሁለት ፍንዳታ ነው የፈፀምኩት ያለው። አንደኛው ጥቃት አዘዞ 24ተኛ ክፍለ ጦር ካምፕ ላይ ነው። በጥቃቱ በውስጡ ምን እንደያዘ ያልታወቀ መጋዘን ጋይቷል። በወታደሩ ላይ ከፍተኛ ትርምስ ፈጥሯል። ዋናው የጥቃቱ ኢላማ የሆነው ግን ሁለተኛው ጥቃት ነው። ድርጅቱ ቀድሞ ባገኘው ጥብቅ መረጃ መሰረት ጨለማን ተገን አድርገው በእኩለ ሌሊት አዘዞ ወደ ሚገኘው ኤርፖርት በሁለት ዘመናዊ ኮብራ መኪኖች ሲጓዙ አዘዞ በሚገኝ ድልድይ አካባቢ ሲደርሱ የእጅ ቦንብ ተወርውሮባቸዋል። ተከታትሎ ተኩስ ስለተከፈተባቸው በፍጥነት ወደ ኋላ ዞረው ወደ ጎንደር ከተማ እንዲመለሱ ተገደዋል። በመኪኖቹ ውስጥ የነበሩትን የህወሃት ባለስልጣናት ማንነትና የደረሰባቸውን ጉዳት ለጊዜው መለየት አልተቻለም።
24ተኛውና 42ተኛው ክፍለ ጦሮች የሰፈሩበት ካምፕ ላይ የተጣለው የመጀመሪያው ጥቃት አቅጣጫ ማሳቻ ነበር። የደፈጣ ጥቃት የተፈፀመበት ድልድይ ወደ መተማ መስመር መገንጠያ ላይ ነው። ሃላፊነት የወሰደው ኢብፓ ጠላትን ከፍ ባለ ደረጃ ለመፋለም ያለንን ወኔና ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብሏል።
በቂ ቅድመ ዝግጅት በመደረጉ ታጋዮቹ በቀላሉ ወደ ቦታቸው ተመልሰዋል። ለደሞዝ ሲል ለወያኔ አገልጋዩ ወታደር ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ አድሮባቸዋል። ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ አሰሳ እየተደረገ ነው። የወያኔ አመራሮች ተሸብረዋል። በአጠቃላይ ጎንደር ላይ ከፍተኛ የሆነ ውጥረት ተፈጥሯል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፓርቲ የወያኔን እብሪት አንታገሰውም ቀጣይና ተከታታይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ ማስጠንቀቂያ ልኳል።
ድርጅቱ በተለያየ አደረጃጀት በስፋት በገጠርም በከተማም ሲታገሉ የቆዩ ሃይሎችን ወደ አንድ ወጥ አደረጃጀትና አመራር ማሰባሰቡን እንዲሁም መሰል ቀጣይ ተግባራት በመላ ሃገራችን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ድርጅቱም አመራሩም ሙሉ ለሙሉ በህቡእ ሃገር ውስጥ እንደሚንቀሳቀስ ስለ ገለፀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፓርቲ አላማና ማንነት የድርጅቱ ማኒፌስቶ ስለደረሰን በቀጣይ እንዘግባለን።

749 Shares
Share
Tweet
Pin
Email
Share

Wednesday, November 15, 2017

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በኦሮሚያ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ source zehabsha

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ትላንት በኦሮሚያ ውስጥ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ጉጂ ዞን ሊበን ወረዳ ውስጥ መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ በጥቃቱም ሰባት ሰዎች የተገደሉ ሲሆን፣ ዛሬም በስፍራው ከፍተኛ ውጥረት መንገሱን ለመረዳት ተችሏል፡፡ ጥቃት ፈጻሚዎቹ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል የፖሊስ አባላት መሆናቸውን በዓይናቸው እንደተመለከቱ የገለጹት ነዋሪዎች፣ በቀጣይም ለደህንነታቸው እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል፡፡
File Photo
በጥቃቱ ከተገደሉ ሰዎች በተጨማሪ የቆሰሉ ሰዎች ስለሞኖራቸውም እየተነገረ ይገኛል፡፡ የክልሉ ልዩ ጦር ጥቃቱን ከፈጸመ በኋላ ከአካባቢው ብዙም ርቆ እንዳልሄደ የሚናገሩት የዓይን እማኞች፣ ሁለተኛ ዙር ጥቃት ሊፈጸም ይችላል የሚል ስጋት በማኅበረሰቡ ዘንድ መፈጠሩንም ነዋሪዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡ የልዩ ኃይሉ አባላት፣ ሰባት ሰዎችን ከገደሉ በኋላ አንድ ትምህርት ቤት በጥይት እንዳጋዩ የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ በተጨማሪም ሁለት የመኖሪያ ቤቶች በልዩ ኃይሉ አባላት እንዲቃጠሉ መደረጉንም ነዋሪዎቹ ያክላሉ፡፡
እንደ ነዋሪዎቹ ገለጻ ከሆነ፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል አባለቱ ጥቃቱን የፈጸሙት በስፍራው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ባሉበት ሁኔታ ነው፡፡ ጥቃቱ ሲፈጸም የመከላከያ ሰራዊት አባላቱ ምንም ዓይነት እርምጃ አለመውሰዳቸውን የዓይን እማኞቹ ይገልጻሉ፡፡ ከሟቾች መካከል አራቱ ዕደሜያቸው ገፋ ያለ ሲሆን፣ ከ60 እስከ ሰባ ዓመት ይገመታሉም ተብሏል፡፡ ከዚህ ቀደም በኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል መካከል በተፈጠረው ግጭት፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በአሮሚያ ክልል ውስጥ በርካታ ሰዎችን መግደሉ ሲነገር ቆይቷል፡፡ በሁለቱ ክልሎች መካከል ተፈጥሮ የነበረው ግጭት ቆሟል ተብሎ በመንግስት እየተገለጸ ባለበት በዚህ ሰዓት፣ ልዩ ኃይሉ ወደ ኦሮሚያ ክልል ዘልቆ ጥቃት የፈጸመበት ምክንያት አልታወቀም፡፡

Friday, November 10, 2017

ንግስት ይርጋ በክሷ ምክንያት በደል እየደረሰባት እንደሆነ ተገለፀ source zehabesha

(በጌታቸው ሺፈራው)
የ”ሽብር” ክስ የተመሰረተባት ንግስት ይርጋ በክሷ ምክንያት ማረሚያ ቤት ውስጥ በደል እየደረሰባት መሆኑን ጠበቃዋ ለፍርድ ቤቱ ገልፀዋል። ንግስት ይርጋ በቤተሰብ ጥየቃ ገደብ እየተደረገባት መሆኑን ለፍርድ ቤት አቤቱታ ባቀረበችው መሰረት ፍርድ ቤቱ ምንም ገደብ ሳይደረግባት እንድትጠየቅ ቢወስንም የቃሊቲ ማረሚያ ቤት የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ሳያከብር ቀርቷል።
ፍርድ ቤቱ ትዕዛዙን ለምን እንዳላከበረ በችሎት እንዲያስረዳ ትዕዛዝ ቢልክም ማረሚያ ቤቱ በሁለት ቀጠሮች ቀርቦ አላስረዳም። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ለ3ኛ ጊዜ በሰጠው ትዕዛዝ ዛሬ ህዳር 1/2010 ሁለት ኃላፊዎች ቀርበዋል።

የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የፍትህ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዋና ሱፐር ኢንተንደንት አስቻለው መኮንን የማረሚያ ቤቱን እና የታራሚውን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል ንግስት ተለይታ እንደምትጠየቅ፣ እንዲሁም ሁሉን እስረኛ በተመሳሳይ ሰዓት ማስተናገድ ስለማይቻል የንግስት ጥየቃ ሰዓት ከሌሎች እስረኞች የተለየ መሆኑን እና ባስመዘገበችው የቤተሰብ አባላት እየተጠየቀች መሆኑን አስረድተዋል።
ንግስት ይርጋ በበኩሏ ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ስትገባ የሚጠይቋትን አስመዝግቢ መባሏንና ከተመዘገቡት ውጭ ያሉና 720 ኪሎ ሜትር ርቀት ድረስ ሊጠይቋት የሚመጡ ዘመድና ወዳጆቿ አልተመዘገባችሁም እየተባሉ እንደሚመለሱ ለፍርድ ቤቱ ገልፃለች። ጉዳዩን ለፍርድ ቤት በአቤቱታ አቅርባ ገደብ እንዳይደረግባት ብይን ቢሰጥም ማረሚያ ቤቱ ትዕዛዝን አለማክበሩን አስታውሳለች። ማረሚያ ቤቱ ለምን የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ እንደማያከብር በጠየቀችበት ወቅትም የሴቶች ጥበቃ እና ማረፊያ አስተዳደር ኃላፊ ዋና ሱፐር ኢንተንደንት አለም ጥላሁን “ይህን ትዕዛዝ የሰጠው ዳኛ ማን ነው? ማወቅ እፈልጋለሁ።” እንዳሏትና እኚህ ኃላፊ ችሎት ውስጥ እንደሚገኙ ለፍርድ ቤቱ አስረድታለች።
ሆኖም ፍርድ ቤቱ ችሎት ውስጥ የነበሩትን ኃለፊ ለምን ይህን እንዳሉ መልስ እንዲሰጡ ሳይጠይቃቸው ቀርቷል። ማረሚያ ቤቱ ለፍርድ ቤቱ በፅሁፍ በሰጠው መልስ ላይ የፈረሙት የሴቶች ጥበቃና ማረፊያ አስተዳደር ጥበቃና ደኅንነት ስራ ዘርፍ ኃላፊ ለተ እግዜር ገ/ መድኅን ናቸው። ሆኖም ትዕዛዙን ለፍርድ ቤት ያደረሱትና በቃል መልስ የሰጡት የለተ እግዜር ኃላፊ ናቸው የተባሉት ዋና ሱፐር አለም ናቸው።
ማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ከሰጡት መልስ በተቃራኒ ገደብ እየተደረገባት መሆኑን ንግስት ለፍርድ ቤቱ ገልፃለች። በሀገራችን ባህል የታመመ እና የታሰረ ሰው ማንም እንደሚጠይቀው ያስታወሰችው ንግስት ይርጋ ጠያቂዎቿ መታወቂያ እስከያዙ እና ጠያቂና እሷን የሚቆጣጠሩ ፖሊሶች እስካሉ ድረስ በማንኛውም ሰው መጠየቅ መብቷ እንደሆነ ገልፃለች።
“ማንኛውም የተከሰሰ ሰው ነፃ ሆኖ የመገመት መብት አለው” ያሉት ጠበቃ ሄኖክ አክሉሉ በበኩላቸው፣ ማረሚያ ቤቱ ንግስት ይርጋን በክሷ ምክንያት በደል እየፈፀመባት እንደሚገኝ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። የፌደራል ማረሚያ ቤቱ ተወካይ ከገለፁት በተቃራኒ ሌሎች እስረኞች ከ3 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት ሲጠየቁ ንግስት ይርጋ ከ6 እስከ 7 ሰዓት ባለው አንድ ሰዓት ብቻ እንደምትጠየቅ ገልፀውም ማረሚያ ቤቱ የሚያደርሰውን አድሎ አስረድተዋል። ካስመዘገብሽው ውጭ አትጠየቂም የሚለው የማረሚያ ቤቱ አሰራርም ህገ መንግስታዊ እንዳልሆነ ገልፀዋል።
የንግስት ይርጋ ሌላኛው ጠበቃ አቶ አለልኝ ምህረቱ ፍርድ ቤቱ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት መልስ እንዲሰጥ ትዕዛዝ ቢሰጥም፣ መልስ ለመስጠት የመጡት የእስረኞችን የዕለት ተዕለት ጉዳይ የማይከታተሉ የፌደራል ማረሚያ ቤት ኃላፊ መሆናቸው ጉዳዩን በደንብ እንደማያውቁት ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ባስመዘገበቻቸው ዘመድና ጓደኛ እየተጠየቀች ነው ያለ ሲሆን አቶ አለልኝ በበኩላቸው ህገ መንግስቱ የቅርብ ዘመድ እና ጓደኛ ሲል ወሰን እንደሌለው፣ ከዚህ መለስ ተብሎ ሊገደብ እንደማይገባ አብራርተዋል።
በንግስት አቤቱታ ጉዳይ ቀጠሮ የተሰጠው ማረሚያ ቤቱ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ለምን እንዳላከበረ ቀርቦ እንዲያስረዳ ለማዳመጥ የነበር ቢሆንም ዛሬም የሁለቱን ክርክር አዳምጦ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በዚህም መሰረት ንግስት ይርጋ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 21 መሰረት ገደብ ሳይደረግባት እንድትጠየቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል። የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ንግስት ይርጋ የማይገባ ጭቅጭቅ ማድረጓን ባይገልፁም ፍርድ ቤቱ ” ተከሳሽም የማይገባ ጭቅጭቅ ውስጥ ላለመግባት ጥንቃቄ ያድርጉ፣ ህጉን ለይተው አውቀው ይጠቀሙ” ብሏዋል። ከችሎት ውጭ ያነጋገርኳቸው የንግስት ጠበቆች ንግስት መሰል ባህሪ አሳይታለች ባልተባለበት ፍርድ ቤቱ ያልተነሳ ነገር ላይ ለተከሳሽ ትዕዛዝ መስጠቱ ተገቢ አይደለም ብለዋል። በሌላ በኩል ንግስት ይርጋ ጥርሷን ታማ መድሃኒት ቢታዘዝላትም መድሃኒቱ በታዘዘላት ሰዓት እየተሰጣት እንዳልሆነ አቤቱታ አቅርባለች።
የማረሚያ ቤቱን መልስ ከመስማት በተጨማሪ እነ ንግስት ይከላከሉ ወይስ አይከላከሉ በሚለው ላይ ብይን ለመስጠት ተቀጥረው የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ “መዝገቡ ተመርምሯል።ጊዜ አግኝተን ማጠቃለል አልቻልንም” ብሎ ለህዳር 5/2010ዓ•ም ለብይን ሌላ ቀጠሮ ሰጥቷል።

Saturday, November 4, 2017

በኢትዮጵያ የጥቅምት ወር የዋጋ ግሽበት አስደንጋጭ ጭማሪ አሳየ source zehabsha

ቢቢኤን) በኢትዮጵያ በጥቅምት ወር ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ተመዘገበ፡፡ የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ እየተገባደደ በሚገኘው የጥቅምት ወር የግብይት ስርዓት ላይ ጥናት ያደረገ ሲሆን፣ ጥናቱም በወሩ ከፍተኛ ግሽበት መመዝገቡን አመላክቷል፡፡ ባለፈው መስከረም ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ 10 ነጥብ 8 ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፣ እየተጠናቀቀ በሚገኘው በዚህኛው የጥቅምት ወር ደግሞ የ12 ነጥብ 2 በመቶ የዋጋ ግሽበት ተከስቷል፡፡ ሁኔታው አስደንጋጭ መሆኑን የሚናገሩት የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች፣ የዋጋ ግሽበቱ በየወሩ እየተከሰተ መሆኑ ደግሞ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ እንደሚያደርገው ይገልጻሉ፡፡

የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ እንደገለጸው በዚህኛው ወር ከፍተኛ የዋጋ ንረት ከታየባቸው ምርቶች መካከል፣ ፍራፍሬዎች ይጠቀሳሉ፡፡ ሙዝና አቮካዶ የመሳሰሉ ፍራፍሬዎች ከፍተኛ የዋጋ ንረት ታይቶባቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ስኳር እና ቡና በዚህ ወር አስደንጋጭ የዋጋ ንረት አስመዝግበዋል፡፡ በተለይ ስኳር እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ የተደረገበት ሲሆን፣ አንድ ኪሎ ስኳርም እስከ መቶ ብር ድረስ መሸጡን ለማወቅ ተችሏል፡፡ እንዲሁም ቡናም በተመሳሳይ ሁኔታ በጥቅምት ወር አሳሳቢ የዋጋ ንረት አስመዝግቧል፡፡
ከአትክልት ደግሞ ቲማቲም፣ ካሮት እና ድንች የሚፋጅ የዋጋ ጭማሪ ተደርጎባቸዋል፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በአትክልት ተራ፣ በመርካቶ እና በሌሎች የአዲስ አበባ ትላልቅ የገበያ ስፍራዎች በአትክልት ዋጋ ላይ አስደንጋጭ ጭማሪ ተደርጓል፡፡ ከጥራጥሬ እህሎች ደግሞ በጤፍ፣ ስንዴ እና በቆሎ ላይ መጠነኛ ጭማሪ መደረጉን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በኢትዮጵያ የተከሰተው የኑሮ ውድነት ለደሃው ብቻ ሳይሆን፣ አለው ለሚባለው የህብረተሰብ ክፍልም እጅግ ፈታኝ ደረጃ ላይ መድረሱ በተደጋጋሚ ተነግሯል፡፡ በፍጆታ ምርቶች ላይ በየወሩ እየጨመረ የመጣው የዋጋ ንረት መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ሀሳብ ላይ ጥሎታል- እንደ መረጃዎች ገለጻ!

Tuesday, October 31, 2017

በህወሓት/ኢህአዴግ ውስጥ የተፈጠረው አለመግባባት ብሶበታል ተባለ source zehabesha



በህወሓት/ኢህአዴግ ውስጥ የተፈጠረው አለመግባባት እየባሰበት እንደመጣ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ፓርቲው አጣብቂኝ ላይ በወደቀበት በዚህ ሰዓት፣ ባለስልጣናቱ የተለያየ አስተሳሰብ ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ በተለይ በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረው ህዝባዊ ንቅናቄ በፓርቲው አመራሮች ዘንድ የሚወሰነውን ውሳኔ ጉራማይሌ እንዲሆን እንዳደረገው የጠቆሙት ምንጮች፣ ፓርቲው ትልቅ ችግር ውስጥ እንደሚገኝ አክለው ገልጸዋል፡፡ ፓርቲው ከፍተኛ መናጋት እና ክፍፍል እየገጠመው እንደመጣ ከዚህ ቀደም ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ የህወሓት/ኢህአዴግ አመራሮችን ለሁለት ከከፈሉ ጉዳዮች መካከል አንደኛው የፖለቲካ እስረኞችን የተመለከተው እንደሆነ ታውቋል፡፡
በተለይ በፖለቲካ ጉዳይ የታሰሩ የኦሮሞ ፖለቲከኞችን መፍታት በኦሮሚያ ክልል ለተከሰተው ህዝባዊ ተቃውሞ እንደ ማብረጃ ይጠቅማል ብለው ያሰቡ የፓርቲው አመራሮች፣ እስረኞቹ እንዲፈቱ ሀሳብ ማቅረባቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ በሌላ ወገን ያለው አመራር ግን አንደኛው አመራር ያቀረበውን ሀሳብ እንደማይቀበለው መግለጹን ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ በአንደኛው ወገን ‹‹ከመሬት ተነስቶ የፖለቲካ እስረኞቹን መፍታት ከባድ ሽንፈት ነው የሚያስከትልብን›› የሚል አመለካከት የያዘ ሲሆን፣ በሌላኛው የፓርቲው ወገን ደግሞ፣ ‹‹እስረኞቹን መፍታት ከመጣብን መዓት አይበልጥም፡፡›› የሚል አመለካከት መኖሩንም ከምንጮች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡
በተለይ ዶ/ር መረራ ጉዲናን ጨምሮ አቶ በቀለ ገርባ እና ሌሎች በፖለቲካ ጉዳይ የታሰሩ የኦሮሞ ፖለቲከኞችን መፍታት፣ በኦሮሚያ የተፈጠረውን ቀውስ በመጠኑም ቢሆን ሊያበርደው ይችላል የሚል አቋም የያዙ የህወሓት/ኢህአዴግ አመራሮች፣ ሃሳባቸው የበላይነት እየያዘ እንደመጣ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሆኖም እስረኞቹን በነጻ ከመልቀቅ ይልቅ፣ ጉዳዩ የፍርድ ሂደቱን የተከተለ እንዲመስል በዋስ መልቀቁ እንደሚሻል በአንደኛው የፓርቲው ወገን ስምምነት ላይ መደረሱን የቢቢኤን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዛሬው ችሎቱ፣ አቶ በቀለ ገርባን በዋስ የፈታበት ምስጢርም አንደኛው የህወሓት/ኢህአዴግ አመራር ቡድን በደረሰበት ስምምነት መሆኑን የሚገልጹት መረጃዎች፣ በቀጣይም ከኦሮሞ ፖለቲከኞች ውስጥ ከእስር ሊፈታ የሚችል ሰው እንደሚኖር ከወዲሁ ጠቁመዋል፡፡ ሆኖም በቀጣይ ማን ከእስር እንደሚፈታ ለማረጋገጥ አልተቻለም፡፡

Sunday, October 29, 2017

አንዳርጋቸው ጽጌ ዛሬ በዚህ ሰአት  – መስቀሉ አየለ  source zehabesha


ገና ለጋ ሳለ በማርክሲዝም አስተሳሰብ ርቆ የሄደው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ኢንጂነሪንግ ተማሪ የነበረው አንዳርጋቸው ጽጌ ከኢህአፓ ትግል መክሸፍ በኋላ እንደማንኛውም የዘመኑ ወጣት በሱዳን በኩል ወደ አውሮፓ በማቅናት ዱር ቤቴ ብሎ ወደ ኤርትራ በራሃ እስከወረደበት ግዜ ድረስ በዚያው ቆይቷል።

ሆኖም ግን አንዳርጋቸው በአውሮፓ የዩኒቨርሲቲ ቆይታው በወጣትነቱ ከተማረው የኢንጂነሪንግ ትምህርት በማፈንገጥ ነፍሱን ሲበላው ለከረመውና የርሱን ትውልድ በዚያ ደረጃ እንደዛ አድርጎ ያሰከረው ነገር ምን እንደሆነ ሚስጥሩን ፍለጋ ቢረዳኝ በሚል ፍልስፍና ተማረ። ሆኖም ግን ትምህርቱን ከጨረሰም ቦሃላም እንደ ማንኛውም ስደተኛ ቤትና ትዳር ወደሚል የግል ሩጫ ሳያዘነብል ከሰው ገለል ብሎ ብሎ ብዙ በማንበብና ብዙ በማሰብ በተመስጦ ውስጥ ቆይቷል።

ግለ ታሪኩ እንድሚያስረዳው አንዳርጋቸው በብዙ መልኩ አውሮፓ ውስጥ የተባህትዎ ኑሮው የእርሱ መገለጫው እንደነበርና ለዚህም አስረጅው ነገር ከባእቱ ሳይወጣ እረጅም ግዜ የሚያሳልፍ ፣ ብዙ ባለመብላት ይልቁንም ከእፍኝ ቆሎ ጋር ትንሽ ቡና በመጠጣት ሰውነቱን ድካም ሳይሰማው ብዙ የሚያነብና ብዙ ከመናገር አርምሞን የሚመርጥ ሰው ነበር።
በዚህም የተነሳ በአንድ ነገር ላይ ብቻ ሳይወሰን ዘ ስካይ ኢዝ ዘሊሚት በሚል ስሌት ፈርጀ ብዙ እውቀቶችን ለማዳበር የቻለ ሰው ነው አንዳርጋቸው። አንዳርጋቸው ጽጌ ሁሌም ተማሪ፣ በየትኛውም የእውቀት ዘርፍ ላይ መናገር ሲጀምር የሚያስደምም አንደበተ ርትኡ፣ ከምንም በላይ ከሰዎች በታች ዝቅ ብሎ ማንንም ለመስማት ትእግስት ያለው ነገር ግን አንድ ግዜ ላሰመረበት መስመር የማይደራደር እንደ ፌሮ የማይታጠፍ የመርኽ ሰው በሉት እልከኛ ነው።
አንድ ምሳሌ ላንሳ፤
አንዳርጋቸውን በአንድ ወቅት አንድ የሆነ አፍሪካ አገር ውስጥ አግኝቸው በራሱ አንደበት እንዳጫወተኝ ሲጋራ ያጨስ እንደነበር፤ ያም ሆኖ ግን ይህንን ስሜቱን እንደማይወደው ለዚህም እንዲረዳው ወደ ህክምና ማእከል ሄዶ ሲጋራ ለማቆም የሚያስችል ልዩ ልዩ ቴራፒ ለመውሰድ ሞክሮ አንዱም አይነት መንገድ ሊሰራለት እንዳልቻለ ፤ ነገር ግን ባንድ ምሽት ላይ አንዲት ኩነት እንደተፈጠረች እንዲህ ሲል አጫወተኝ። ግዜው አለ አልጎርደን ብራውን የተባለ የቀድሞው የብሌየር ዘመን ቻልስለር የበጀት ሪፖርት የሚሰጥበት ቀን ነበር። በበጀት ሪፖርቱ ዙሪያ ለቻንስለሩ ከቀረቡለት ጥያቄዎች አንዱ የሲጋራን ታክስ የሚመለከት ሲሆን ጋዜኛው እንዲህ ሲል ጠየቀ፣
“ሚር ቻንስለር እርስዎ ወደ ዳውኒንግ ስትሪት ከመጡ ግዜ ጀምሮ የሲጋራ ዋጋ በመቶዎች ፐርሰንት እጥፍ እያደገ ነው፣ ለዚህ ምላሽዎ ምን ይሆን?” የሚል ነበር።
ቻንስለር ብራውን፤ “አየህ እኛ በሁለት መቶ ያህል አገሮች ለምናካሂደው የውጭ ፖሊሲ (በየሃገሩ ያሉትን ኤምባሲዎቻችንን እና የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶቻችንን ) እንዲሁም ሌሎች የሁለት አንስተኛ የሚኒስቴር መስሪያ ቤት በጀት ሙሉ ለሙሉ የሚሸፈነው ከሲጋራ በሚገኝ ታክስ ነው በመሆኑ አማራጭ የለንም” ብሎ ቁጭ አለ።
ጋዜጠኛውም በማስከተል ገና ለገና “ሰው ሲጋራ ያጨሳል ብላችሁ ይህን ያህል በመቶ ቢሊዮን ፓውንድ የሚቆጠር በጀት ስትይዙ ሰው ሁሉ ተነጋግሮ ሲጋራውን ማጨስ ቢያቆም ምን ሊውጣችሁ ነው?” ሲል ይጠይቃል፤ ነገር ግን ቻንስለሩ መልሳቸው አጭር ነበር። “አያቆምም!!!” የሚል፤ “ለዚህም” አሉ ቻንስለሩ፣ “ለዚህም በደንብ ወጥነት ያለው (ፓተርንድ) የሆነ መረጃ አለን። ማጨስ የጀመረ ሰው ማለት በራሱ ላይ ስልጣን የሌለው እስቱፒድ ነው ..” የሚል ነበር። ይኽን በቀጥታ ለእግሊዝ ህዝብ ሲተላለፍ የነበረ ቃለ ምልልስ ቤቱ ውስጥ ሆኖ ሲከታተል የነበረው አንዳርጋቸው የመጨረሻውን መልስ ሲሰማ ፈገግ ነበር ያለው። እጁንም ወደ ደረት ኪሱ ሰደድ ሲያደርግ አስር ያህል ሲጋራ የያዘ አንድ የሲጋራ ፓኮ ነበረው፤ አውጥቶም ቅርጥፍጥፍ አደረገና ከፊት ለፊቱ ባለው የብርጭቆ ውሃ ውስጥ ነከረው። “በእርግጥም..!!!” አለ አንዳርጋቸው “ከእንግዲህ የኽን ቃለምልልስ ሰምቸ የሲጋራን ዘር ዳግም ወደ አፌ ብመልሰው አንተ እንዳልከው በእርግጥም እስቱፒድ መሆኔን በእራሴው ግዜ አረጋገጫለሁ ማለት ነው” አለ። ነገሩ ወዲህ ነው፤ የሚገርመው ነገር ከዚያች ቀን ጀምሮ የአንዳርጋቸው ጽጌ ሲጋራ ማቆም መቻሉ ብቻ አልነበረም። እርሱ ሲጋራውን ሲያቆም ማዛጋት፣ ማፋሸግ እራስ ምታትም ሆነ እንቅልፍ እንቅልፍ ማለት ሳያስፈልገው እንደማንኛውም ሱስ እንደሌለበት ሰው እንዲሁ ጽድት ባለ መንፈስ ከብሩህ ፈገግታ ጋር ነበር ከእቅልፉ የነቃው። በዚህም አንድ ሰው ከውስጡ ሲወስን ምን ያህል አቅም መፍጠር እንዲሚቻለው ቀላሉ ማሳያ ሆኖ አልፏል።
እንዲህ ያሉት በመርህ የመጽናት ባህሪዎቹ ለአንዳርጋቸው በጸጥታ ውስጥ በኖረባቸው የጽሞና ግዜያት ያዳበራቸው የሞራል መሰረቶቹ ናቸው። በዚህ የተነሳ ማንም ሰው አንዳርጋቸውን ቀርቦ ለማወቅ እድል ቢገጥመው እርሱ ማለት ከራሱ ጋር የታረቀ፣ ፍጹም ሰላማዊ፣ እንደ ሱናሜ በሚገነፍል ማእበል ላይ ተረጋግቶ መራመድ የማይሳነው፣ የማይሞቀው የማይበርደው፤ በአለም ሳለ እራሱን የካደ ትሁት ሰው ነው።
ዛሬ አንዳርጋቸው ጽጌ በፍልስፍና ውስጥ ያዳበረውን ወደ ውስጥ የማየት ክህሎት በሌላ ገጽታው በመመርመር ያሳልፋል። ወያኔዎች ባዘጋጁለት ከመሬት በታች በተሰራች በጣም ጠባብና አየር አለባ መስኮት አልባ ክፍል ውስጥ የብሉያትን እና የሃዲስ ኪዳንን እንዲሁም የነገረ መለኮትን ትርጉዋሜዎች አዳርሷል። ሰባቱን አጽዋማት ሲጾም በቀን አንድ ግዜ ምግብ ይቀምሳል።የያኔው የማርክሲስት ባህታዊ ፍልስፍና እና ነገረ መለኮት ሳይጣረሱ የት ላይ እንደሚገናኙ ዛሬ በስልሳዎቹ መጀመሪያ እድሜው ላይ ነጥቡን አግኝቶታል።ይዅውም በፍልስፍና ፒውር ሰብጀክቲቪቲ የሚባለው በመጸሃፍ ከንጻሃ ስጋ ወደ ንጻሃ ነፍስ፤ ከንጻሃ ነፍስ ወደ ንጻሃ ልቡናና፤ ነጽሮ ስላሴና አይምሮ መንፈሳዊ እያሉ ባለቤቱ ክርስቶስን እስኪያክሉት በመንፈስ ማደግ ነው። ዛሬ አንዳርጋቸው በዚያ ጎዳና ላይ ነው። ማን ያውቃል፤ እንደ ጳውሎስ ቀናኢ ነገር ግን በራሱ መንገድ ይጏዝ የነበረ፤ በዚያው ልክ ከሰማይ በታች ለሰው ልጆች ሰላም የማይገደው ነገር የሌለና ለዚህም እርሱ በወቅቱ በገባው መስመር ፤ለራሴ ሳይል ከልጅነት እስከእውቀት እራሱን አሳልፎ የሰጠለት ይኽ የእንጨት ለቃሚ ልጆች ጎስቋላ ህይወትን የመታደግ ትግል፤ እንዲሁም የደም ንኪኪው ካለባቸው የሰቃሊያነ ክርስቶስ ተረፈ አይሁድ እጅ ከወደቀበት ቀን ጀምሮ በእያንዳንዷ ደቂቃ የከፈለውን ስቃይ ከጾም ከጸሎት ከንሳሃ ቆጥሮለት እርሱ ብቻ ባወቀው የገለጠለት ወይንም የተገለጠለት ነገር አለመኖሩን ማን ያውቃል?፣ ቅዱስ አውግስጢኖስ “ቤተከርስቲያናችን በቅዱስ እስጢፋኖስ ጸሎት ቅዱስ ጳውሎስን ያህል ሃዋርያ አገኘች” ሲል ቅዱስ ጳውሎስን ኋላ ለደረሰበት የብቃት ደረጃ የጠራችው ቀዳሜ ሰማእት ቅዱስ እስጢፋኖስ በዲንጋይ ሲወገር በጸአት ነፍሱ ግዜ “ጌታ ሆይ ይቅር በላቸው ብሎ የጸለያት ጸሎት ነበረች” ማለቱ ነበር። የመድሃኒዓለም ስራው ሰዎች ለክፋት የሚያደርጉትን ክፉ ስራ ሁሉ ወደ በጎ መለወጥ ነው፣ ውሃውን ወደ ወይነጠጅ እንደለወጠው፤ አንዳርጋቸው ጽጌ ወስመ ጥምቀቱ ዘእየሱስ ዛሬ በመንፈስ ከፍታ ላይ ሆኖ ፓትሪያርኩን ጨምሮ ጥቃቅኖቹን ጭንጋፎች በማይክሮስኮፕ ያያቸዋል።

Friday, October 27, 2017

አቶ ኃይለማርያም መንግስት የአባ ዱላ ገመዳን የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ እየመረመረው ነው አለ source zehabesha


ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ አባዳላ ገመዳ ያቀረቡትን የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ እየመረመረው ይገኛል አሉ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ አቶ በረከት ስምዖን ያቀረቡትን የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ መንግስት እንደተቀበላቸው ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ዕለት በኢህአዴግ ፓርላማ ተገኝተው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እሳቸው በተገኙበት የአዲስ አፈ ጉባኤ ምርጫ ይካሔዳል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ ሆኖም ባልታወቀ ምክንያት ምርጫው እንዲራዘም ተደርጓል፡፡
አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ያስገቡት ከአቶ በረከት ስምዖን ቀደም ብለው ቢሆንም፣ የእሳቸው ጉዳይ ተቀምጦ የአቶ በረከት ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል ተብሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዚህ እንደ ምክንያት የሰጡት ደግሞ፣ አቶ በረከት ከዚህ ቀደምም ተደጋጋሚ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ማቅረባቸውን ነው፡፡ የአባ ዱላ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ግን የመጀመሪያው በመሆኑ፣ መንግስት እየመረመረው ወይም እየመከረበት ይገኛል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
አቶ አባዱላ ገመዳ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ያቀረብኩት ‹‹የህዝቤ እና የድርጅቴ ጥቅም ስለተነካ ነው፡፡›› ማለታቸው አይዘነጋም፡፡ አቶ አባዱላ ገመዳ አሁንም በስራቸው ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ ከመቼ ጀምሮ ከስራቸው እንደሚሰናበቱ የታወቀ ነገር የለም፡፡ መንግስት ያቀረቡትን ጥያቄ መርምሮ መቼ ምላሽ እንደሚሰጣቸውም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም የገለጹት ነገር የለም፡፡ በአሁን ሰዓት በገዥው ፓርቲ ውስጥ ከፍተኛ መከፋፈል የተፈጠረ ሲሆን፣ አለመደማመጥ መስፈኑም እየተገለጸ

“በጥልቅ ሀዘን ውስጥ ላለ ሰው ትንቢት አትናገር !” – ዳንኤል ሽበሽ source zhabesha

ዛሬ ጥቅምት 16 ቀን፡ 2010 ዓም ጠቅላይ ሚኒስትራቸው የፕ/ት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ለሕ/ተ/ም ያደረጉትን መክፈቻ ንግግር ተከትለው የሰጡትን ማብራሪያ (brief) አዳመጥኩኝ ፡፡ አንድ ሪፖርት የሚቀዳው ከዕቅድ እስከ ድርጊት ካለው ክፍል ውስጥ መሆኑ ግልጽ ነው ፡፡ ካልዋሸን ወይም ካልተሳሳትን በስተቀር ሪፖርት እውነት መሆን አለበት ፡፡ ከዚህ ሀሳብ ስንነሳ አንገት ስላስደፋን የመንግሥታቸው ሪፖርት ለፓርቲያቸው አባላት (ለፓርላማው) አቅርበውታል ፡፡ የማብራሪያቸው ይዘት ለኔ በብዙ ውሸቶችና በጥቂት አጃቢ እውነታዎች የታጨቀ ነበር ፡፡
እጅግ የመሰጠኝ ግን በፖሊስ አባላት ላይ የሰነዘሩት አስተያየት ነው፡፡ በተለይ በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል ስለተፈጠረው ቀውስ በተመለከተ በቀውሱ ውስጥ የተሳተፉ የፖሊስ ሠራዊት የአመለካከት ችግር እና ኪራይ ሰብሳቢ ጥገኞች ናቸው በማለት ነበር የገለጹት ፡፡ እኛ ባለን መረጃ ግን የፖሊስ አባላት አፈሙዙን ወደ መንግሥትና መንግሥት ፖለቲካል አቅጣጫ ላይ ማዞራቸውን እንጂ አንዱ ሌላውን ሕዝብ ለማጥቃት አይመስለኝም ፡፡ ክቡርነታቸው (አጎቴ lol) እንዳሉትም ከሆነም ማለቴ ነው፡፡
“ልጅን ለማረም አስቸጋሪ የሚሆነው ችግሩ ከወላጆቻኀው ጋር ሲኖር ነው” እንደሚባለው ሁሉ የፖሊሶቹ ችግር ነው የተባለው ችግርም የሚቀዳው ከተቀረጹበት ከአብዮታዊ ዴሞክራሲ አለመለካከታቸው መሆኑ ግልጽ ነው ፡፡ በሊብራል አስተሳሰብ ቢቀረጹ ኖሮ ሊብራልና ዴሞክራቲክ ይሆኑ ነበር እንደ ማለት ፡፡ እንደሚታወቀው ፖሊሶቹ (ልዩ ኃይል) ዕድሜ ክልላቸውን ብናይ እንኳ የሩብ ምዕተ ዓመታት ውጤቶች ናቸው፡፡ በኢሠፓ ወይም በኢህአፓ ማላከክ የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ፖሊሶቹ ኪራይ ሰብሳቢ፤ ፀረ ዴሞክራቲክ ወዘተ ከሆኑ ተጠያቂው አሳዳጊዉም ጭምር እንጂ ታዳጊዉ ብቻ አለመሆኑ ሊሰመር ይገባል ፡፡ አሳዳጊው የትግራይ ነፃ አውጪ እና የእጁ ሥራው #አዴ ናቸው ፡፡ የአንድ ወንዝ ምንጩ በየጊዜው ድፍርስ ከሆነ ወራጁ ውሃው እንደት ሊጤራ ይችላል ? ውሃው እንዲጠራ ከተፈለገ የግልና የጋራ ጥረት ያስፈልገዋል ፡፡ በሁሉም በኩል ጥረቱም ትግሉም አሁን የተጀመረ ይመስለኛል ፡፡
ፖሊሶቻችን የኛ ናቸው ፡፡ እንደ ማንኛው ሰው ሁሉ ዕኩልነትንና ፍትሐዊነትን ይፈልጋሉ ፡፡ እንደ ዜጋ ፍትህንና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ይናፍቃቸዋል ፡፡ ጥሩ ኑሮ መኖር ይፈልጋሉ ብቻም ሳይሆን ያስፈልጋቸዋልም፡፤ በሰው’ ታቸውም በማዕረጋቸውም መከበርን ይፈልጋሉ ፡፡ ያሠማራቸው ሥርዓቱ ከሕዝብ ጋር ባጣላቸው ቁጥር እንደተጣሉ መኖር አይፈልጉም ፡፡ ማንም ተራ ዜጋ እንደሚረዳው በሀገራችን ለተራ እግረኛ ወታደር ይቅርና ለትላልቆቹ ለባለ መሥመር መኮንኖችም ካለው ክብር ይልቅ ለአንድ ቻይናዊ ጉልበት ሠራተኛ ያለው ክብር ይልቃል ፡፡ ለአንድ ኢንስፔክተር፣ ሱፐርኢንተዳንት፣ ኮሎኔልና ወዘተ ከሚሰጠው ሥፍራ ይልቅ ለተራ ጆሮ-ጠቢ ያለው ታአማኝነት ጎልቶ ይታያል … ፡፡ በኀወሓት ዕዝ ሰንሰለት ሥር ተጠርንፈው የሚተነፍሱበትን አጥተው መኖራቸውን ለማንም ግልጽ ነው ፡፡ ነጋ ጠባ ግምገማ ተብየ አውጫጭን ያረሩ ፖሊስ አባላት’ኮ ሁሌም አንገት ደፍተው ይኖራሉ ማለት ለኔ ይከብደኛል ፡፡ ሰዎች ናቸውና አንድ ቀን <… ግን ለምን?…> ብለው መጠየቃቸው አይቀረ ነው ፡፡

በላይ ላያቸው የተቆለሉትና በድሃው ገበሬ ልጅ ደምና በመሬታቸው ቱጃር የሆኑ ዛሬ ላይ የጨዋታ ህጋቸውን ወደ #ቢሊዮኖች ቤት ከፍ ሲያደርጉ (የሠራዊቱን አዛዦችንም ይጨምራል) እነዚህ ሚስክኖቹ ደሞ የታክሲ ሣንትም ጭምር አጥተውና ተርበው በየመንደሩ ሲያዛጉ እንደት ስለሰላም ሊያወሩ ይቻላል? ግዙፉ ሕገመንግሥት ይቅርና የቅርቡን የአለቃ ትዕዛዝ እንደት ብለው ያከብራሉ?፤ ጠ/ሚሩ እንዳሉት ከሆነም ማለቴ ነው ፡፡ በከባድ ሀዘን ውስጥ ላሌ ሰው ትንቢት አትናገር ይባል የለ!? በከባድ አስተዳደራዊ ጭቆና ውስጥ ያለ ሰራዊት፤ የቤት መክፈያ አጥቶ በየካምፑ የሚከራተት ነው ፡፡ የልፋታቸውን ዋጋ በአንፃራዊነት እንኳ መቅመስ ያልቻለ ሠራዊት ፤ ስለ ሰብዓዊነት እየተሰበከላቸው ግን ሰብዓዊ ክብራቸውን ለተነፈጉ ሠራዊት፤ በቅድሚያ ሕገ መንግሥቱን ለመጠበቅም በሕገ መንግሥቱ የተደነገጉ መብቶቻቸው መጠበቅ ይገባል ባይ ነኝ ፡፡ እንዲያውም የሀገራችን ፖሊሶች በባሕልና በሃይማኖት ተፅዕኖ ውስጥ ያደጉና የኖሩ መሆኑ በጀን እንጂ፤ በሥርዓቱ ከሚደርሰባቸው በደል ልክ ቢሆን ኖሮ ምን ሊመፈጠር እንደምችል መገመት አያቅትም ፡፡
በደርግ ጊዜ ከነበረው ከኢት/ያ ሠራዊትም እንዳየነው ከሆነ፤ ቢቸገር ቢቸገር እንኳ መሣሪያ ቢሸጥ ወይም ቢለምን እንጂ መሣሪያውንና ሙያውን ተጠቅመው በእኩይ ተግባር ላይ የማይሳተፍ ነው ፡፡ ይህ ከኢት/ዊ ጨዋነት፣ ከአስተዳደጋቸውና ከግላዊ ባሕርያቸው የሚመነጭ እንጂ ከሙሰኛው፤ ከጨቋኙ፤ ከዘረኛው እና እንዲተኩሱት ከሚያዘው ኃይል አስተሳሰብ የሚመነጭ አይደለም ፡፡ በርግጥ ከሠራዊቱ በኩል ወደ ሕዝቡ ይተኮስ የነበረው ጥይት ለምንና እንደት እንደሆነም አይጠፋብንም ፡፡ ከዚህ በኀላ ግን ሕዝቡም የሠራዊቱ፤ ሠራዊቱም የሕዝቡ ነው !!
በ2005 ዓም በአንዱ ጹሁፌ ላይ ርዕስም ትኩረትም ያደረኩት <ለፖሊስና ለመከላከያ ሠራዊቱ ማን አለላቸው?> የሚል ነበር ፡፡
የጠ/ሚ ኃ/ማርም ንግግር የሀገራችንን ነባራዊና ወቅታውዊ ሐቁን ያላገናዘቤ፤ እውነታውን በደንብ ያልዳሰሰ ነበር ፡፡ ሰላም !!

Thursday, October 26, 2017

የሰው ሕይወት የተቀጠፈበት የአምቦ የተቃውሞ ውሎ በቢቢሲ ዘገባ source zehabesa

በግጭቱ ቢያንስ 10 ሰዎች እንደተገደሉ የአይን እማኞች ይናገራሉ
(Photo credit – BBC)
ስለአምቦው ውሎ የቢቢሲ ዘገባ እንደወረደ:-
በስልክ ያነጋገርናቸው የአምቦ ከተማ ነዋሪዎች እንደነገሩን ስኳር ጭነው በከተማው የሚያልፉ መኪኖች እንዳሉ መረጃ ለአካባቢው በመድረሱ ፤ መኪኖቹን ለማስቆም በመጠባበቅ ከትናንት ጀምሮ መንገድ መዝጋት ጀምረው ነበር።
ምክንያታቸው ደግሞ በሀገሪቱ የሚታየው የስኳር እጥረት በአምቦም የሚስተዋል መሆኑ ነው።
በከተማዋ አንድ ኪሎ እሰከ 70 ብር ድረስ ይሸጣል ይላሉ።
እናም በዚህ ሁኔታ ስኳር ተጭኖ ወደሌላ ቦታ መሄዱን በመቃወም ነው መንገድ መዝጋት የጀመሩት።
” ከተማዋን አቆርጠው የሚሄዱ ዋናና መጋቢ መንገዶች በመዘጋታቸው የክልሉ ፖሊስና እኛ ሆነን በህገወጥ መንገድ ሊያልፍ የነበረውን ስኳር ስንጠብቅ አድረናል”ይላሉ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለገ አንድ የአካባቢው ነዋሪ።
ዛሬ ግን ከማለዳው አንድ ሰዓት አካባቢ የፌደራል ፖሊስና የመከላከያ ሰራዊት መለያ የለበሱ በተቃዋሚዎች ላይ በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን ተናግሯል።
“እኔ በአይኔ ያየሁት አምስት ሰዎች ሲገደሉ ነው።ግን የሞቱት በጣም በርካታ ሰዎች ናቸው” ያለን ደግሞ ሌላው የከተማዋ ነዋሪ ነው።
” ሁለት የፌደራል ፖሊስ ልብስ የለበሱ በድንጋይ ተደብድበው እንደሞቱ አይቻለሁ” ብሎናል።
ቢቢሲ ግን የሟቾቹን ትክክለኛ ቁጥር ለማረጋገጥ አልቻለም።
ከግጭቱ ጋር ተያይዞ በንብረት ላይም ጉዳት የደረሰ ሲሆን የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ ንብረት የሆኑ ሁለት የጭነት መኪናዎች ተቃጥለዋል።
በከተማዋ ስኳር እንዳይዘዋወር መንገዶች እንዲህ ተዘግተዋል
የአሮሚያ ክልል የመንግስት ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋ በፌስ ቡክ ገጻቸው የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉንና በሌሎች ሰዎች ላይም የአካል ጉዳት መደረሱን የሚገልጽ መረጃ አስፍረዋል።
” ከሰላማዊ ሰልፍና ከስኳር ፍተሻ ጋር በተያያዘ ወጣቶችን በማነሳሳትና ስርዓት አልበኝነት እንዲስፋፋ በማድረግ ለግጭቱ መንስዔ የሆኑትን አካላት እናወግዛለን” ብለዋል።
በአሁኑ ሰዓት ከተማዋ በአንጻራዊነት የተረጋጋች ትመስላለች፤ ነገር ግን መንገዶች እንደተዘጉ ሲሆን ሰልፈኞቹም ወደየቤታቸው አልተመለሱም።
ከዚህም የተነሳ ብዙዎች አሁንም ተጨማሪ ጉዳት ሊደርስ የሚችል ስጋት እንዳላቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል።

የሀገሪቱ ጦር እና ደህንነት የህወሓትን ስልጣን በማዳን ስራ ላይ አተኩሯል source zehabesha

(ቢቢኤን) በኢትዮጵያ የሚገኙው ማንኛውም ዓይነት ጦር እና የደህንነት አካል የህወሓትን ስልጣን ለመታደግ አተኩሮ እየሰረ እንደሚገኝ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ የሀገሪቱ የደህንነት እና የመከላከያ ሰራዊት ቁልፍ ቦታዎች በህወሓት እጅ ውስጥ እንደመገኘቱ፣ የፓርቲውን ዕድሜ ለማራዘም ከመቼውም ጊዜ በላይ እየተሰራ እንደሚገኝ ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ ለዚህም ሲባል መደበኛ ስራቸው ሀገር መጠበቅ የሆነ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ህዝባዊ ተቃውሞ በተነሳባቸው ቦታዎች ጭምር እየሔዱ በህዝብ ላይ ጥቃት እየፈጸሙ እንደሚገኙ መረጃዎች በመጠቆም ላይ ናቸው፡፡

ከሁለቱ አካላት በተጨማሪ ደግሞ በህወሓት ርዕዮተ-ዓለም ቅርጽ የተመሰረተው የአጋዚ ጦርም እንደተለመደው፣ የስርዓቱን ዕድሜ ለማስቀጠል ግድያን ጨምሮ ማንኛውንም ዓይነት አረመኔያዊ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል፡፡ የኦሮሚያ ፖሊስ ከዚህ ቀደም ከነበረው አኳኃኑ የተወሰነ መሻሻል ማሳየቱ እና ለተቃውሞ አደባባይ ከሚወጡ ሰዎች ጋር መግባባት መፍጠሩ ህወሓትን አላስደሰተውም ይላሉ- ታዛቢዎች፡፡ ለዚህም ሲባል የአጋዚ ጦር ተቃውሞ በሚነሳባቸው የኦሮሚያ ከተሞች እየገባ ግድያ እንዲፈጽም እየተደረገ ይገኛል ብለዋል-ታዛቢዎቹ፡፡
የህወሓት መንግስት ጀምበር እየጠለቀችበት እንደሚገኝ የሚናገሩ አስተያየት ሰጪዎች፣ ስርዓቱ የባከነ ሰዓት ላይ የሚገኝ እንደመሆኑ ማንኛውንም ዓይነት እርምጃ ከመውሰድ እንደማይመለስ ያክላሉ፡፡ ቀስ በቀስም ሀገሪቱን ወደ ወታደራዊ ስርዓት ሊወስዳት እንደሚችልም አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል፡፡ በተለይ በህወሓት እጅ የሚገኙት ዋና ዋና የደህንነት እና የመከላከያ ቦታዎች፣ አሁን ላይ ስርዓቱ እንዴት ብሎ ከመጣበት ህዝባዊ መዓት ማምለጥ እንዳለበት በሰፊው እየመከሩ እንደሆነ ከምንጮች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ በየቀኑ እየተካሔዱ ባሉ ተቃውሞዎች የተነሳ ፋታ ያጣው የህወሓት መንግስት፣ አሁን ላይ ሌሎችን ገድሎ ራሱን ለማዳን እየተፍጨረጨረ ይገኛል፡፡

Tuesday, October 24, 2017

የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ከህዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ዶክመንተሪ ፊልም ሊሰራ ነው

የገዥው ፓርቲ ልሳን የሆነው የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ዶክመንተሪ ፊልም ሊሰራ መሆኑን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ዶክመንተሪው የሚያተኩረው ሰሞኑን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተካሔዱ የተቃውሞ ሰልፎች ላይ ሲሆን፣ ፊልሙ ህዝቡ ያነሳውን የነጻነት ጥያቄ ሌላ መልክ ሰጥቶ ጥላሸት የመቀባት ዓላማ እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ የገባው የህወሓት መንግስት፣ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተስተዋለ የሚገኘው የብሔረሰቦች አብሮ የመታገል ሁኔታ በእጅጉ እያስፈራው እንደመጣ ይነገራል፡፡ ቡድኑ ይህን ሁኔታ ለመሰባበር ወይም የአንድነቱን ጉዞ ለማሰናከልም ደፋ ቀና እያለ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል፡፡

ህዘቡ የመብት ጥያቄውን እያቀረበ የሚገኘው በግልጽ እና በማያሻማ መንገድ ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በኩል ሊሰራ የታቀደው ዶክመንተሪ ፊልም ግን፣ አንዱ ብሔር በሌላው ላይ በጠላትነት እንደተነሳ ተደርጎ ለማቅረብ ታቅዷል፡፡ ለዚህ ዓላማ ሲባልም አስቀድሞ በሰልፎች ውስጥ ጣልቃ እንዲገቡ ተደርገው፣ ሰልፉ ሌላ ዓላማ ያነገበ እንዲመስል ጥረት እያደረጉ ያሉ ካድሬዎች መኖራቸው ታውቋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ፣ በተደጋጋሚ በሰጠው መግለጫ፣ ሰልፎቹን ወደ ሁከት ለመቀየር ሲሞክሩ የነበሩ ሰዎች ተያዙ የሚል ቃል ሲደጋግም ቆይቷል፡፡ ይህም የፊልሙ አንድ ግብዓት መሆኑንም የመረጃ ምንጮች ይጠቁማሉ፡፡
የተቃውሞ ሰልፍ በተካሔደባቸው የኦሮሚያ ከተሞች፣ ቪዲዮ ካሜራ የያዙ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ሰራተኞችን መመልከታቸውንም የዓይን እማኞች ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡ በየከተሞቹ የተደረጉ ሰላማዊ ሰልፎችን ቀርጾ ያስቀመጠው የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን፣ በቀጣይም ሁከት ተነስቶባቸዋል በተባሉ የተቃውሞ ሰልፎች ላይ በመመስረት አዲስ ፊልም ሊሰራ ማቀዱን ከመረጃዎች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ቴሌቭዥን ጣብያው ከዚህ ቀደም የተለያዩ አካላትን እና ሰዎችን ስም ለማጥፋት ዶክመንተሪ ፊልም ሲሰራ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ጣብያው ምንም እንኳን ፊልም የመስራት አባዜ ቢኖርበትም፣ የሰራቸው ፊልሞች ግን አንድም ቀን በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት አግኝተው እንደማውቁ ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡

Monday, October 16, 2017

አባዱላ ገመዳ የለቀቁበትን ምክንያት በዝርዝር አስረዱ source zehabesha

ምክንያት በዝርዝር አስረዱ
 



ከላይ በቀረበው የአባዱላ ንግግር ላይ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሸፈራው የሚከተለውን ምላሽ ሰጥቷል::
ስለ ኦህዴድ ብዙ ብዙ እየተባለ ነው። አባዱላ የህዝብና ድርጅት ክብር ስለተነካ ለቅቄያለሁ ብሏል። በመሰረቱ የህዝብ ክብር አሁን አይደለም የተነካው። ብዙ ሳንርቅ በ2008 እነ አባይ ፀሃዬ፣ እነ ጌታቸው ረዳ በህዝብ ላይ ምራቅ ሲረጩ እነ አባዱላ ጭጭ ብለው ነበር። ዛሬ ነቃን፣ መረረን፣ በዛ ካሉም መልካም ነው።
በ2008 የተነሳው ህዝባዊ ንቅናቄ ትንፋሽ ሲያሳጣቸው ሚዲያውን መግለጫ በመግለጫ አድርገውት ነበር። በዋነኛነት ችግሩ የህዝብ ሳይሆን የኢህአዴግ ነው ብለዋል። ይህን ብለው ግን በዚሁ ንቅናቄ ሰበብ የታሰሩትን አልፈቱም። እንዲያውም የሀሰት ክስ ቀርቦባቸዋል። የኢህአዴግ ችግር ነው በተባለው ጉዳይ የሀሰት ክስ ከቀረበባቸው መካከል እነ አቶ በቀለ ይገኙበታል!
እነ አቶ በቀለ የቀረበባቸውን የሀሰት ክስ ተከላከሉ ተብለው ለጥቅምት 27፣ 28 እና 29 ቀጠሮ ተይዟል። ለዚህ የሀሰት ክስ በምስክርነት የጠሩት ደግሞ ችግሩ የህዝብ ሳይሆን የእኛ ነው ብለው ህዝብን ይቅርታ የጠየቁትን እነ አባዱላ ገመዳ እና እነ ለማ መገርሳን ነው!
እነ አቶ በቀለ የተከሰሱት እነ አባዱላ ገመዳ ክብሩ ተነክቷል ያሉትን ህዝብ አነሳስታችሁዋል፣ አሳምፃችሁዋል ተብለው ነው። ጥቅምት27፣ 28ና 29 እነ በቀለ የሚያስመሰክሩት ለራሳቸው ብቻ ሳይሆን በገዥዎቹ ስለተፈረጀው፣ ሽብር፣ አመፅ ፈጥሯል ተብሎ ለሚከሰሰው፣ አሁንም በየ ፍርድ ቤቱ ስሙ ሲነሳና ክብሩ ሲነካ ለሚውለው ህዝብ ነው!
እውነት እነ አባዱላ ፣ እነ ለማ ስለ ህዝብ ክብር ካሰቡ ጥቅምት 27፣ 28ና 29 ፍርድ ቤት ቀርበው እውነታውን፣ ቢያንስ ያኔ መግለጫው ላይ የሰጡትን ቃል ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል! ባለስልጣናት በምስክርነት ተጠርተው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተልኮላቸዋል ተብሎ ያልቀረቡበት ጊዜ አለ።
ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያው ብዙ ለተባለላቸው የኦህዴድ ፖለቲከኞች ጥቅምት 27፣ 28ና 29 ከባድ ፈተና ይገጥማቸዋል! የመጀመርያው ለምስክርነት መቅረብ አለመቅረባቸው ነው! አይቀርቡም እንጅ ከቀረቡ ለመስቀለኛ ጥያቄው ከአሁኑ ፀሎት፣ ምህላ ማስደረግ ይጠበቅባቸዋል! ምክንያቱም ምስክርነቱ ከህዝብ ወይንም ከትህነግ ጋር እንደሚያቀያይማቸው እሙን ነው!

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከ እስር ከተፈታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ቃለምልልስ ሰጠ – “እናቴን በደህና በማግኘቴ ከፍ ያለ ደስታ ተሰምቶኛል


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከእስር ከተፈታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ቃለምልልስ ሰጠ – “እናቴን በደህና በማግኘቴ ከፍ ያለ ደስታ ተሰምቶኛል”

Thursday, October 5, 2017

ተመድ የቀድሞ አንድነት ፓርቲ አመራር አቶ አንዷለም አራጌ እንዲፈታ ጠየቀ


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቀድሞ አንድነት ፓርቲ አመራር የነበረው አቶ አንዷለም አራጌ እንዲፈታ ጠየቀ፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት አቶ አንዷለምን ያሰረው ዓለም ዓቀፍ ድንጋጌዎችን በመጣስ እንደሆነ የገለጸው ተመድ፣ በመሆኑም መንግስት ፖለቲከኛውን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ አሳስቧል፡፡ ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ላይ እንደገለጸው ከሆነ፣ አቶ አንዷለም አራጌ ለእስር የተዳረገው ያለ ምንም ጥፋት እና በደል ነው፡፡
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ የእስረኞችን ጉዳይ የሚከታተለው ቡድን ባወጣው መግለጫ ላይ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የጸረ ሽብር አዋጁን በመጠቀም ህጋዊ የፖለቲካ ሰዎችን እያጠቃ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ መግለጫው ይቀጥልና፣ አቶ አንዷለም አራጌ ለእስር የተዳረገውም የጸረ ሽብር ህጉን በመቃወሙ እንደሆነም ያትታል፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ አቶ አንዷለም አራጌ ብቻ ሳይሆን ባልንጀሮቹ ጭምር ከእስር እንዲፈቱ የኢትዮጵያ መንግስትን አሳስቧል፡፡
በኢትዮጵያ የሚገኘው ስርዓት እጅግ አስከፊ መሆኑ በተለያየ ወቅት ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ ይህን ጉዳይ የሀገሬው ህዝብ ብቻ ሳይሆን ዓለም ዓቀፍ ተቋማት እና መንግስታት ጭምር እየመሰከሩት ያለው ሐቅ ከሆነም ሰነባብቷል፡፡ በሕወሓት የሚመራው ይኸው ስርዓት፣ ለስልጣኑ የሚያሰጉትን ፖለቲከኞች ሁሉ እስር ቤት አስገብቷል፡፡ ከአንጋፋ ፖለቲከኞች ጀምሮ ገና ወጣት የሆኑ ፖለቲከኞችን እስር ቤት በማስገባት እየተበቀላቸው የሚገኘው አገዛዙ፣ ሰብስቦ ባሰራቸው ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች እና የሰብዓዊ መብት ታጋዮች የተነሳ ከዓለም ዓቀፍ የመብት ተከራካሪዎች ከፍተኛ ውግዘት እየገጠመው ይገኛል፡፡

Friday, September 15, 2017

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ጥቃት አሁንም እንደቀጠለ ነው source zhebsha

የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እየፈጸመ ያለው ጥቃት አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉ ታወቀ፡፡ ከተለያዩ የኦሮሚያ ክፍሎች እየወጡ ያሉ መረጃዎች እንዳመለከቱት፣ በሶማሌ ክልል እና በኦሮሚያ አዋሳኝ ድንበሮች ላይ ከባድ ውጥረት አለ፡፡ ውጥረቱ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መሔዱን የገለጹት የአካባቢው የዓይን እማኞች፣ በተለይ በሶማሌ ክልል የሚኖሩ የኦሮሞ ተወላጆችን የማፈናቀል ድርጊት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን እማኞቹ አክለው ተናግረዋል፡፡

ልዩ ኃይል የተባለው የሶማሌ ክልል ፖሊስ ህወሓት ለክልሉ ፕሬዚዳንት ለአቶ አብዲ በሚሰጠው ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሚመራ ሲሆን፣ ልዩ ፖሊሱ በንጹኃን ሰዎች ላይ ግድያ እንዲፈጽም እየተደረገ ያለውም በህወሓት ሴራ ሆን ተብሎ እንደሆነ ምንጮች ይናገራሉ፡፡ ህወሓት በኦሮሞ እና በኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝብ መካከል ግጭት እንዳለ በማስመሰል የፖለቲካ ጨዋታ ለመጫወት እየሞከረ መሆኑንም ታዛበዎች ይናገራሉ፡፡ ‹‹ድርጊቱ የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካ ውጤት ነው፡፡›› ያሉት ታዛቢዎቹ፣ ህወሓት በመጨረሻው ሰዓት በሀገሪቱ ላይ የእርስ በእርስ ግጭት እንዲፈጠር እንደሚፈልግም ያክላሉ-ታዛቢዎቹ፡፡

በምስራቅ ኢትዮጵያ ሐረርጌ ልዩ ስሙ ሜኢሶ በተባለው አካባቢ ያለው ውጥረት አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይልም ደረስ መጣ እያለ ጥቃት እንደሚፈጽም ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ግጭት ተከስቶባቸዋል በተባሉ የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልል አዋሳኝ ድንበሮች ላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ሰፍረዋል ቢባልም፤ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ግን አሳቻ ሰዓት እየጠበቀ ጥቃት እንደሚፈጽም ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

የህወሓት አጋዚ ወታደሮች ሐረር ውስጥ ግድያ ፈጸሙ source zhebesha

በሐረር የተሰማራው የህወሓት አጋዚ ሰራዊት ግድያ ፈጸመ፡፡ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እየፈጸመ ያለውን አሰቃቂ ጥቃት ለመቃወም በሐረር ከትላንት ጀምሮ ህዝባዊ ተቃውሞ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ዛሬም ቀጥሎ የዋለውን የህዝብ ተቃውሞ ተከትሎ የአጋዚ ወታደሮች ወደ ተቃውሞ አቅራቢዎች በቀጥታ በመተኮስ የሰው ህይወት መቅጠፋቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ የሟቾች ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ አልታወቀም፡፡

ከሟቾች በተጨማሪም በጥይት ተመትተው የቆሰሉ ንጹኃን ሰዎች መኖራቸውን የገለጹት መረጃዎች፣ ሐረር በከባድ ውጥረት ውስጥ እንደምትገኝም ተናግረዋል፡፡ በተለይ ሸዋ በር ተብሎ የሚጠራው የሐረር አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ሲሰማ እንደነበር ከዓይን እማኞች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ እስከ ምሽት ድረስ የቀጠለው የተኩስ ድምጽ ሐረርን የጦርነት ቀጠና እንዳስመሰላት የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል በጅጅጋ ይኖሩ በነበሩ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ በፈጸመው ጥቃት ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ህይወት ተቀጥፏል፡፡ በዛሬው ዕለትም የሟቾች አስከሬን ወደ ሐረር ሲጓጓዝ እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ ትዕዛዝ ከጅጅጋ የተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች ወደ ሐረር እየተወሰዱ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችም ሐረር ያለመጠለያ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡ የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት የሆነው ህወሓት፣ የሀገሪቱን ህዝብ እርስ በእርስ ለማባላት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ የገለጹት አስተያየት ሰጪዎች፣ ፈታኝ ጊዜ ላይ በመሆናችን በአንድነት ልንቆም ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡
BBN news September 14, 2017

Tuesday, September 5, 2017

ጀዋር መሐመድ መንግስት በቴዲ አፍሮ ላይ እየወሰደ ያለውን ተደጋጋሚ ክልከላ አወገዘ source zhabesha

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ዳይሬክተር ጀዋር መሐመድ አምባገነኑ የሕወሓት መራሹ መንግስት በቴዲ አፍሮ ላይ በተደጋጋኢ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አወገዘ::
“ገዥው አካል ለቴዲ አፍሮ የሚያቀርበውን ትርዒት በተደጋጋሚ በመሰረዙ ተገቢ ያልሆነ እና ኢፍትሃዊ ውሳኔ ነው” ያለው ጀዋር በቴዲ ላይ መንግስት የሚወስደው ክልከላ “ይህ ሁሉ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነትን እና ዒላማው የኪነጥበብ ጥቃትን ስለሚያካትት ሁሉም ሊያወግዘው ይገባል” ሲል በፌስቡክ ገጹ ላይ ጽፏል::
ይህ የመንግስት ኪነጠብን የማፈን ተግባር አዲስ ነገር አይደለም አይደለም ያለው ጀዋር “መንግስት ከማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል የበለጠ ስነ-ጥበብ እና አርቲስቶችን ይፈራል::” ካለ በኋላ ሥርዓቱ በኦሮሞ አርቲስቶች ላይም ከስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የወሰደውን ጥቃት ጠቅሷል::

እንደጀዋር ገለጻ ሕወሓት መራሹ መንግስት ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ብዙ የኦሮሞ አርቲስቶችን ገድሏል፣ አስሯል እና ከሃገር እንዲሰደዱ አድርጓል::

ኦነግ በኦሮሚያ የሚደረገውን አድማና ትግል እየመራ መሆኑን አስታወቀ source zhabesha

ዋዜማ ራዲዮ- የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በቅርቡ የተደረገውን ቤት የመቀመጥ አድማ ጨምሮ በኦሮሚያ ወጣቶች በአፋኙ ስርዓት ላይ የሚያደርጉትን ትግል ከፊት ሆኜ እየመራሁት ነው ሲል አስታወቀ።
ድርጅቱ በኤርትራ አስመራ ለአስር ቀናት ያደረገውን ጉባዔ ሲያጠቃልል ባወጣው መግለጫ የኦነግ ክንፍ የሆነው የኦሮሞ ወጣቶች ክንፍ (ቄሮ) እያካሄደ ያለው ትግል ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቡን አስምሮበታል።
ኦነግ ለቄሮ የሚያደርገውን ድጋፍ በሶስት እጥፍ በማሳደግ በቀጣዮቹ ወራት በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት ለማስወገድ እንደሚንቀሳቀስ ተናግሯል።
ለኦሮሞ ነፃነት የሚታገሉ ድርጅቶች ሁሉ ከጎኑ እንዲሰለፉ የጠየቀው ኦነግ የኦሮሞ ነፃ አውጪ ጦርን ወደተግባር ለማስገባት የገንዘብ የቁሳቁስና የሰው ሀይል አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ ለማሰደግ እየሰራሁ ነው ብሏል። ደጋፊዎቹም ለዚህ እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል።
የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ የጠየውቀው መግለጫው ከሌሎች ከተጨቆኑ የኢትዮጵያ ብሄሮች ጋር ለመተባበር ዝግጁ ነኝ ብሏል።
አስመራ የሚገኘው ኦነግ ከሶስቱ ዋና ዋና የኦነግ አንጃዎች አንዱ ሲሆን በአቶ ዳውድ ኢብሳ ይመራል።
በቅርቡ በኦሮሚያ የተደረገውንም ሆነ ሌሎች አድማና አመፃችን በማስተባበር በውጪ ሀገር ያሉ አክቲቪስቶች በተለይም የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አስኪያጅ ጃዋር መሀመድ ሀላፊነቱን ወስዶ ሲሰራ መቆየቱ ይታወቃል።

Friday, August 18, 2017

በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተሰማn source mereja

በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተሰማ
በወልድያ ተቃውሞ መቀስቀሱን ምንጮች ጠቆሙ፡፡ በዛሬው ዕለት የወልድያ ህዝብ ‹‹አላግባብ የተጫነብኝን ግብር አልከፍልም፡፡›› ብሎ አሻፈረኝ ማለቱን ከስፍራው የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡ በዚህም የተነሳ ከተማው ውጥረት ማርገዙን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ባለፈው ሳምንት ለአምስት ቀናት የስራ ማቆም አድማ ላይ የሰነበተው የወልድያ ህዝብ፣ በዛሬው ዕለትም ተቃውሞ አስነስቷል፡፡ የህወሓት መንግስት በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ የግብር ጫና መጣሉ አይዘነጋም፡
በሀገሪቱ ነጋዴዎች ላይ የተጫነውን የግብር ጫና ተከትሎ በመላው ሀገሪቱ ተቃውሞ መቀስቀሱ የሚታወስ ሲሆን፣ ወልድያም ተቃውሞ ከተቀሰቀሰባቸው ከተሞች አንዷ ሆና ሰንብታለች፡፡ በዛሬው ዕለት ተቃውሞው በድጋሚ ማገርሸቱን የተናገሩት የከተማዋ የቢቢኤን ምንጮች፣ ህዝቡ ግብሩ ካልተቀነሰለት በቀር ለመክፈል ዝግጁ አይደለም ብለዋል፡፡ ምንጮቹ አክለውም ‹‹በግብር ስም ዘረፋ መፈጸም ተገቢ አይደለም፡፡›› ሲሉም የህወሓትን መንግስት የዘረፋ አዝማሚያ ተችተዋል፡፡
የከተማዋ ህዝብ ግብር አልከፍልም ማለቱን ተከትሎ፣ የፖሊስ ኃይሎች በከተማዋ መሰማራታቸውን የገለጹት ምንጮች፣ እስከ ምሽቱ አንድ ሰዓት ድረስም ከተማዋ ውጥረት ላይ እንደነበረች ይገልጻሉ፡፡ ከምሽቱ አንድ ሰዓት በኋላ ከተማዋ ጭር ብላ መታየቷን የገለጹት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ መሸት ካለ በኋላ የፖሊሶች ቁጥር ጨምሮ መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡
ጥያቄአቸው እስካልተመለሰ ድረስ፣ የዛሬው ተቃውሞ በነገው ዕለትም ሊቀጥል እንደሚችል ነዋሪዎቹ አረጋግጠዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል ከግብር ጫና ጋር በተያያዘ ተቃውሞ ከተነሳ በኋላ፣ መንግስት የግብር ቅነሳ ይደረጋል የሚል ማስተባበያ ቢሰጥም፣ በመጨረሻም ግን ውሸት መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
BBN

Monday, August 14, 2017

ኢትዮጲያ የማን ናት? መብቱ የዜጎች፣ ስልጣኑ የብሔሮች ነው – ክፍል 2 – ስዩም ተሾመ source zehabesha

“ኢትዮጲያ የማን ናት፡ የብሔሮች ወይስ የዜጎች?” በሚል ርዕስ ባወጣነው የመጀመሪያ ክፍል የኢህአዴግ መንግስት ባለፉት አስር አመታት ፍፁም አምባገነን እየሆነ መምጣቱን ተመልክተናል። ለዚህ ደግሞ ዋና ምክንያቱ ከሕገ-መንግስቱ መሰረታዊ መርሆች ውስጥ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” በሚለው መርህ ላይ መንጠልጠሉና በዚህም ራሱ የዘረጋውን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት ቀልብሶታል።
በመሰረቱ፣ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” የሚለው ሕገ-መንግስታዊ መርህ ከሀገርና መንግስት አመሰራረት ፅንሰ-ሃሳብ ጋር ይጋጫል። ሌላው ቀርቶ ከሕገ-መንግስቱ ጋር ራሱ ይጋጫል። በአጠቃላይ “የሕዝብ ሉዓላዊነት” የሚለው መርህ “ፀረ-ዴሞክራሲያዊ” ነው። “በእንቅርት ላይ ጆሮ-ደግፍ” እንዲሉ መንግስታዊ ስርዓቱ ደግሞ በዚህ መርህ ላይ እንደመሆኑ ሕገ-መንግስቱ፥ ብሎም ፖለቲካዊ ስርዓት ካልተቀየረ በስተቀር ዴሞክራሲ “ላም አለኝ በሰማይ…” እንደሚሉት ሆኖ ይቀራል። በዚህ ፅሁፍ፣ “ከሕዝብ ሉዓላዊነት” መርህ አንፃር የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት እርስ-በእርሱ እንደሚጋጭ እንመለከታለን። በቀጣይ ክፍል ደግሞ ከሀገርና መንግስት አመሰራረት አንፃር የተሳሳተ መሆኑን እንመለከታለን።
ስዩም ተሾመ
በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 8 መሰረት “የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤቶች ናቸው”።ነገር ግን፣ ይህ መርህ ከሉዓላዊነት ፅንሰ-ሃሳብ ጋር ይጋጫል። በዚህ ረገድ ያለውን የተሳሳተ እሳቤ በግልፅ ለመረዳት እንዲያስችለን የሕገ-መንግስቱን የቃላት አጠቃቀም እና የኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በ1993 ዓ.ም ያዘጋጀውን የኣማርኛ መዝገበ ቃላት መሰረት በማድረግ ፅንሰ-ሃሳቡን በዝርዝር እንመለከታለን።
በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 39(5) መሰረት “ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ” ማለት ሰፋ ያለ የጋራ ባህሪይ የሚያንፀባርቅ ባህል ወይም ተመሳሳይ ልማዶች ያሉት፣ ሊግባባበት የሚችልበት የጋራ ቋንቋ ያለው፣ የጋራ ወይም የተዛመደ ሕልውና አለን ብለው የሚያምን፣ የሥነ ልቦና አንድነት ያለውና በአብዛኛው በተያያዘ መልክዓ ምድር የሚኖር “ማህብረሰብ” ነው። (የቃላት ድግግሞሽን ለማስቀረት ሲባል እንደየሁኔታው “ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ” የሚለው “ብሔር” ተብሎ ሊፃፍ ይችላል።) በዚህ መሰረት፣ ብሔር በቋንቋ፥ ባህል፥ ልማድና ስነልቦናዊ አመካከት፣ እንዲሁም በታሪክ፣ ኢኮኖሚና በመልክዓ ምድር የተሳሰረ ማህብረሰብ ነው። በመሆኑም፣ የብሔር መብቶች ከእነዚህ ተፈጥሯዊ ባህሪያት ጋር በቀጥታ የተያያዙ ናቸው። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 39 ላይ “የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብት” በሚል የተጠቀሱት ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይህን ያመለክታሉ።
መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተደነገጉበት የሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍል ሁለት መሰረት፣ በንዑስ አንቀፅ 39(1) “ማንኛውም ብሔር የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከመገንጠል መብት”፣ በንዑስ አንቀፅ 39(2) “ማንኛውም ብሔር በቋንቋው የመናገር፥ የመፃፍ፥ ቋንቋውን የማሳደግ እና ባህሉን የመግለፅ፥ የማዳበርና የማስፋፋት፣ እንዲሁም ታሪኩን የመንከባከብ መብት”፣ በንዑስ አንቀፅ 39(3) ደግሞ “ማንኛውም ብሔር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ መብት” እንዳለው ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ፣ በሕገ-መንግስቱ ንዑስ አንቀፅ 40(3) መሰረት “የመሬት ባለቤትነት መብት”፣ እንዲሁም በንዑስ አንቀፅ 43(1) መሰረት ደግሞ “የልማት መብት” እንዳላቸው ይጠቅሳል።
በዋናነት በሕገ-መንግስቱ እውቅና የተሰጣቸው የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብቶች ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ናቸው። ከዚህ በተረፈ፣ በሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍል አንድ ስር የተዘረዘሩት በሙሉ የግለሰብ ሰብዓዊ መብቶች ናቸው። በክፍል ሁለት ከተዘረዘሩት ውስጥ ከአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) በስተቀር ያሉት በሙሉ የግለሰብ ዴሞክራሲያዊ መብቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ፣ እያንዳንዱ ግለሰብ ግን እንደ አንድ ብሔር ተወላጅ ከላይ የተጠቀሱት የብሔር መብቶች ይኖሩታል።
የአማርኛ መዝገበ ቃላት “ሉኣላዊ” (Sovereign) የሚለውን ቃል “ነፃ የሆነ መሬት፣ ነፃ የሆነ፥ ምሉዕ ስልጣን ያለው ሀገር፥ መንግስት” የሚል ፍቺ ይሰጠዋል። “ሉዓላዊነት” (Sovereignity) ማለት ደግሞ “ምሉዕ የሆነ መብት፥ የነፃነትና ሥልጣን የበላይነት” እንደሆነ ይገልፃል። በዚህ መሰረት፣ “የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት” የሆነ አካል በቅድሚያ ምሉዕ መብትና ነፃነት ሊኖረው ይገባል።
በአጠቃላይ፣ በሕገ-መንግስቱ የተደነገጉት ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሙሉ መሰረታዊ የግለሰብ መብትና ነፃነት ሊሆኑ ይችላሉ። የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብቶች ግን በአንቀፅ 39፣ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት መብቶች ብቻ ናቸው። በዚህ መሰረት፣ አንድ ግለሰብ ምሉዕ መብትና ነፃነት አለው። በተቃራኒው አንድ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ ግን ምሉዕ መብትና ነፃነት የለውም።
ቀደም ሲል ለመግለፅ እንተሞከረው፣ “ሉኣላዊነት” (Sovereignity) ማለት “ምሉዕ የሆነ መብት፥ የነፃነትና ሥልጣን የበላይነት” ነው። በዚህ መሰረት፣ አንድ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ ሉዓላዊ ስልጣን እንዲኖረው በቅድሚያ ምሉዕ መብትና ነፃነት ሊኖረው ይገባል። ነገር ግን፣ በሕገ-መንግስቱ ምዕራፍ ሦስት ክፍለ አንድና ሁለት ስር ከተዘረዘሩት 31 መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች ውስጥ የብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች መብት የሆኑት በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት ብቻ ናቸው። ከእነዚህ ውጪ ያሉት በሙሉ የግለሰብ መብቶች ናቸው።
እያንዳንዱ ግለሰብ በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) የተጠቀሱት የብሔር መብቶች እንደ አንድ ብሔር ተወላጅ ይኖሩታል። እያንዳንዱ ብሔር ግን በአንቀፅ 39፣ ንዑስ አንቀፅ 40(3) እና 43(3) ከተጠቀሱት ውጪ ሌላ ዴሞክራሲያዊ መብት ሊኖረው አይችልም። ምክንያቱም፣ ብሔር፥ ብሔረሰብ፥ ሕዝብ እንደ ግለሰብ በራሱ ሃሳብና አመለካከት የሚንቀሳቀስ ምክንያታዊ ፍጡር ስላልሆነ ሌሎች ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሉትም። በተመሳሳይ፣ እንደ ሰው ሰብዓዊ ፍጡር ስላልሆነ “ሰብዓዊ” መብት ሊኖረው አይችልም። ስለዚህ፣ በሕገ-መንግስቱ ራሱ ምሉዕ መብት ያለው ግለሰብ እንጂ ብሔር፥ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ አይደለም።
በአጠቃላይ፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን የሚችለው እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ ዜጋ እንጂ የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች አይደሉም። ምክንያቱም፣ የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት በምዕራፍ ሦስት ስር ከዘረዘራቸው 31 መሰረታዊ መብቶች ውስጥ ሦስት መብቶች ብቻ ያሏቸው ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች “የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት” እንደሆኑ ይገልፃል። ነገር ግን፣ “ሉኣላዊነት” የምሉዕ መብትና ነፃነት ባለቤትነት እንደመሆኑ መጠን ውስን መብት ያላቸው ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤትነት ሊኖራቸው አይችልም። በዚህ መሰረት፣ የኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት እርስ-በእርሱ እንደሚጋጭ በግልፅ መረዳት ይቻላል።
በመጨረሻም፣ በሕገ-መንግስቱ መሰረት እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ ዜጋ ምሉዕ የሆነ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት አለው። በዚህ መሰረት፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት መሆን የሚችሉት ሁሉም ኢትዮጲያዊያን ወይም ሁሉም የሀገሪቱ ዜጎች ናቸው። ይሁን እንጂ፣ በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 8 መሰረት “የኢትዮጲያ ብሔሮች፥ ብሔረሰቦች፥ ሕዝቦች የኢትዮጲያ ሉዓላዊ ስልጣን ባለቤቶች እንደሆኑ ተደንግጓል። ስለዚህ፣ ሕገ-መንግስቱ እርስ-በእርስ እንዲጋጭ የተደረገበት ምክንያት ምንድነው?
በመሰረቱ፣ የሉዓላዊ ስልጣን ባለቤት የሆነ አካል ባለመብት ብቻ ሳይሆን ባለስልጣን ጭምር ነው። ምክንያቱም፣ ሉዓላዊ ስልጣን ያለው አካል በሀገሪቱ መንግስት ላይ የስልጣን የበላይነት ይኖረዋል። ስለዚህ፣ የሀገሪቱ መንግስት ተጠሪነቱ ለዚህ አካል ይሆናል። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት መሰረት፤ የሀገሪቱ ዜጎች መብትና ነፃነት አላቸው፣ ብሔሮች ደግሞ የሉዓላዊ ስልጣን አላቸው። ዜጎች ምሉዕ መብት አላቸው፣ ነገር ግን መብታቸውን የመጠየቅ ምሉዕ (ሉዓላዊ) ስልጣን የላቸውም። ብሔሮች ደግሞ ምሉዕ (ሉዓላዊ) ስልጣን አላቸው፣ የሚጠይቁት ምሉዕ መብት ግን የላቸውም። በኢፊዲሪ ሕገ-መንግስት መሰረት መብቱ የዜጎች ሲሆን ስልጣኑ ግን የብሔሮች ነው!
በአጠቃላይ፣ የሀገሪቱ ዜጎች የማይጠይቁት መብት ሲኖራቸው፣ የሀገሪቱ ብሔሮች ደግሞ የማይጠቀሙት ስልጣን አላቸው። የኢህአዴግ መንግስት ዘወትር ስለ ብሔር መብትና እኩልነት ይደሰኩራል። ዜጎች የመብትና እኩልነት ጥያቄ ሲያነሱ ግን እንደ ጠላት እያደነ ያስራል፥ ይገድላል፥…ወዘተ።

Friday, August 11, 2017

የሜቴክ ውንብድና….በአዲስ አበባ ትራንሰፖር አውቶቢስ ግዢ ላይ (ጥብቅ መረጃ) source zehabesha

በበዛብህ ሲሳይ (2009) ሀይድራባድ ህንድ
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ ሰሞኑ በቀድሞ የስርዓቱ ልሳን በነበረው በአቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሜቴክ ከንግድ መርከብ ስለገዛቸው ሁለት መርከቦችና ሊያቋቁመው ስላሰበው የውሃ ትራንስፖርት ንግድ ስራ እንዲሁም በአገሪቷ ላይ ያደረሰውን ኪሳራ ካይሁ በኃላ ነው፡፡ እውነት ነው ተቋሙ ሲቋቋም ጀምሮ ለገዢው ጉጅሌ ኢኮኖሚያዊ ትርፍ እንዲያመጣ ተብሎ ብቻ አይደለም የትግራይ ተወላጆችን ከሰሜን ኤርትራዋኖች ላይ እንዲሁም ከደቡብ ደግሞ ሰፊው የኢትዮጰያ ህዝብ ላይ የፖለቲካዊ ልእልና እንዲያመጣ ጭምር እንጂ፡፡ ስለዚህ አቶ ኤርምያስ እንደ አስቀመጠው የሜቴክ መሪዎቹ ሲጋራን በቄንጥ ሚያጨሱ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ እኩይ አላማቸው ላይ የሚሳተፉትን ሆድ አደር “ሙሁራን” ወይም ባለሰርተፊኬቶችን ወይም እንዴት ማስተዳደርና መጠቀም እንዳለባቸው ስለሚያውቁ ይሄው ይሄ ሁሉ ጉዳት በአገሪቱ ላይ ሊያደርሱ ቻሉ፡፡ አንዳንዴ የፈረንጅንም ጫማ ላሾችንም (Bootlikers) ይጠቀማሉ፡፡ በዚህ ጽሁፍ ዋና አላማ ሜቴክ ተልዕኮውን እንዴት እንደሚያሳካ ለማሳይት የታሰበ ሲሆን ፅህፉ ያለውን ነባራዊ ሁኔታን ብቻ የሚያሳይ ነው..ፍርዱን ደግሞ እናነተ ስጡ… መልካም ንባብ !!

በመጀመሪያ ግን አንባቢያን ሊገነዘቡት የምፈልገው ሜቴክ መቆጣጠር ሚፈልገው የኢኮኖሚ አውታር በዋነኝነት ከአገር ውስጥ ወይም ከዉጭ ሃገር ልዪ የፋይናንስ ድጋፍ ያላቸውን ፕሮጀክቶች ሲሆን ትራንስፖርት ደግሞ ዋነኛ ነው ምክንያቱም ከአለም ባንክ ወይም ከቻይና ኤግዚም ባንክ አብዛኛው ብድር የሚሰጠው ለመሰረተ ልማት ግንባታ በመሆኑ ነው፡፡ ሜቴክ ገና ጥርሱን ሳይነቅል ዘሎ ዝርፊያውን የጀመረው የቀድሞ ኢትዮ- ጂቡቲ ባቡር ሃዲድ ላይ ጉብ በማለት ነው፡፡ ለተበተነው የባቡር ሰራተኞች ደሞዝ እከፍላለሁ በሚል ተልካሻ ሰበብ በ1907 የተመረተውን ንፁህ የባቡር ሃዲድ ብረት ወረሰው፡፡ ካለምንም ማስረጃ፡፡ ለዚያውም በ ፈረንጆች 2006 ከአውሮጳ ህብረት በተገኘ የ50 ሚሊዮን ዩሮ ብድር የመልሶ ማቋቋም እድሳት ስራ ጀምሮ የነበረውን እንዲቋረጥ በማድረግ ነው (ግርጌ ፎቶውን ይመልከቱ)፡፡ በመስኩ የተሰማሩት ባለሞያዎች እንሚሉት የቀድሞ የባቡር መስመር በትክክል ቢሰራ ኢትዮጵያ የምታስገባውንም ሆነ የምታስወጣውን ጭነት በአስተማማኝ ከማስተናገዱ አልፎ ሃገሪቱ በሚቀጥሉት ሃያ አመታት ልታመጣው የምትችለውን የኢኮኖሚ እድገትም መሸከም የሚችል ነበር፡፡ ይሄ ለነክንፈ እና አርከበ አይገባቸውም፡፡ የአዲስ አበባ ባቡርም በሰዓት ሃያ ሺህ ህዝብ ያመላልሳል በለው ጉፋያአቸወን ነፍተው አመት እንኳን ሳያገለግሉ ግማሽ ያህሉ ወላለቀው መሃል ሜዳ ላይ ቆሙ!! ሌላው ቢቀር ኢትዮ- ጂቡቲ ባቡር ታሪካዊነቱ ታይቶ ልክ በሰለጠኑት አገራት እንደሚገኙት የድሮ የባቡር መስመሮች ለቱሪዚም አገልግሎት መዋል ይችል ነበር፡፡ በተለይ ከአዲሱ መስመር በበለጠ በብዙ ከተሞች ላይ ማረፊያ ተሪሚናሉች ስላሉት ከተሞችን በንግድ በማስተሳሰር ከፍተኛ አስተዎጽኦ ማምጣት ይችል ነበር፡፡ይሄም ባቡር ወደ 32 ሚሆን ቦታ ላይ ሲያርፍ የቀድሞ ግን ከ100 በላይ ቦታዎች ላይ በማረፍ የከተሞች የኢኮኖሚ እና የማህበረሰብ ትስስርን ያጠናክር ነበር፡፡ ሆኖም ለታሪክ ደንታ የማየሰጣቸው የትግራይ ጉድሌዎችን ያቀፈው ሜቴክ ታሪካዊዉን የበቡር ሃዲድ ብረት ሃላፊነት በጎደለው መንገድ ስልቅጥ አድርጎ በላው፡፡

ከዚህ የረቀቀ አገርን የማውደም ሴራ በሰተጀርባ ያለውን ለመረዳት ግን ከጀነራሎቹ ጋር በመሆን ለሜቴክ ጭንቅላት የሆኑትን ሆድ አደር ምሁራን ተብየዎችንም አብረን ማየት ያለብን፡፡ ምክንያቱም ጠቋሚዎቹና አስተባባሪዎቹ እነሱ ስለሆኑ!!!
ሙሁር ተብየዎችን በማፍራት ግንባር ቀደም የሆነው ገና ከተቋቋመ 20 አመት በሞላው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የሜቴክን አላማ የሚተገብሩለትን በላተኞችን የሚኮተኩትበት ዋነኛ ወታደራው ተቋም ነው፡፡ አካዳሚያዊነቱን ግን ብላሽ ብቻ አይገልፀውም፡፡ አንዴ እዚያ የሚያስተምር ጓደኛየን C ሰጠኅን ብለው ደብድበውታል፡፡ ከዚህ ተቋም የሚመረቁ “ባለሞያዎች” የወታደር ስነ-አምሮ የተላበሱ በመሆናቸው በሲቨል ተቋም ዉስጥ ሲገቡ ይሄንን የመታዘዝና-የማዘዝ ህግጋትን ስለሚተገብሩ ወይም በውይይትና የአመክንዮ ልእልና ስለማያምኑ በሜቴክ አለቆች ዘንድ እጅጉን ጀርባ የሚጣልባቸውና የሚወደዱ ናቸው፡፡ በዩንቨርሲቲው ትምህርት ላይ እያሉም እርስ-በራስ የመገማገምን ትምህርትና የሰዎችን ጉልበት ማሟጠጥ የሚችሉበትን ክህሎት ይቀስማሉ፡፡ ስለዚህ ወደ ስራ ሲገቡ የራሳቸውን ኔትዎርክ በቶሎ ይዘረጉና ምዝበራውን ያሯሩጡታል፡፡ በለራዕዩ መለስ አገሪቱ የተማረ ወታደር አያሰፈልግጋትም ካለ ከዚህ ተቋም የሚወጡት ለሌላ አላማ ነው ማለት ነው፡፡
ከዚህ ቀጥሎማ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ተቋማቶችን በአይን በመማተር ለአለቆቻቸው ሹክ ይላሉ፡፡ ገሚሱን ቻይና በመላክ የውንብድና ሊቅ ሲያረጉዋቸው የተቀሩትን ደግሞ አይናቸውን ጨፍነው አገራዊ (local) ሮል ሞዴል እንዲያበጁ ያረጓቸዋል፡፡ እኔም ከአምስት ከማያንሱ የቀድሞ የስራ ባለደረቦቼ የተረዳሁት አብዛኛዎቹ መለስን እንዲሁም ጥቂቶቹ ስየን እንደ ትልቅ ሮልሞዴል እንደሚዩዋቸው ነው፡፡ ሁለት ዘራፊዎችን!!! ከዚህ ዝግጅት በኃላ ወደ ሲቭል ተቋማት በማስገባት ነባር ተቋማትን በማፍረስ በምትካቸው አዳዲስ ለሚቋቋሙጽ ስም በመስጠት በሮዎችን መክፈት !…ለምሳሌ ኤጀንሲ ፣ባለስልጣን፣ ፅ/ቤት ፣ ተቆጣጣሪ፣ …የረሳሁት ካለ አግዙኝ! ከዚህም አዳዲስ የሚቋቋሙበት ዋና አላማ ተቋሙን ለማደራጀት ተብሎ ከሚመደበው የማቋቋሚያ ገንዘብ ለቤት ክራይ፣ ለጠረቤዛ፣ ለመኪና፣ ..ወዘተ ብለው እንዲጨርሱትና አዳዲስ ተቋማት ውስጥ የራሳቸውን ሰዎች በመሰግሰግ ወደፊት ለሚዘርፉት መንገድ በማበጀት ተጠያቂነት ፈፅሞ እንዳይኖር ለማድረግ ነው፡፡
የሜቴክ መሰሪ አላማ ለመመልከት እስቲ የአዲስ አበባ የመንገዶችና ትራንስፖርት ቢሮን እንይ፡፡ በ2005 ከንቲባ ደሪባ ኩማ ሲሾሙ የከተማይቱን የትራንሰፖርት ችግር ይቀርፋሉ ተብሎ በሰፊው ተዘግቦ ነበር፡፡ በተለይ ፎርቹንና ሪፖርተር ከተቋሙ ጋር ልዩ ጥቅም ስላላቸው የማይመስል ወሬ በማራገብ አንደኛ ናቸው-ለምሳሌ አዲስ አበባ የብስኪሌት ታክሲ ልታገኝ ነው (1 ቀን ሳየሰራ 16 ሚሊዮን ብር አፈር ድሜ ያበላና የከተማዋ ነዋሪዎችም ሽንታቸው እስኪለቁ የሳቁበት)…..15 ፎቅ ያለው ዘመናዊ በኤሌክትሪክ የሚሰራ ፓሪኪንግ ተመረቀ (አጠገቡ ያሉ ኢንተርኔት ቤቶች በኤሌክትሪክ መጥፋት ስራቸውን እንደተዉ ከንቲባው ሳይሰማ ለአድቬንቸር ብሉ የ85ሚሊዮን የብረት ሼልፍ ይመርቃል)… ሌላም ብዙ ብዙ፡፡
ወደ ትራንስፖርት ቢሮው ልመለስና የከተማው ነዋሪ ያለበትን የትራንሰፖርት ችግር ለመቅረፍ አዲስ ተቋም ያስፈልጋል በሚል የትራንስፖርት ፕሮግራሞች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት በሚል እንዲቋቋም ይደረጋል፡፡ ይታያቹህ ለዝርፊያው ያመች ዘንድ መጀመሪያ የፕሮጀክት ማስተባበሪያ ተብሎ የነበረው ፅ/ ቤት ባንዴ እንጣጥ ብሎ የፕሮግራም ማሰተባበሪያ ሆነ! እውነቱ ግን በየትኛውም አለም የተለያዩ ፕሮግራሞችን ማሰተባበር አይቻልም … የእውር መንገድ ለመሆኑና ለመዝረፍ ተብሎ በሜቴክና በከንቲባው የተቀናበረ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ እንደ ፀጉራም ዉሻ አግዝፈው ትልቅ በጀት ለመመደብ እንደሆነ ለሁሉም ባለሞያ ግልፅ ነበር፡፡ የሆነውም ይህንን ተቋም እንዲመራ በብ/ጀ ክንፈ ዳኜው የተመደበው የመከላከያ ዩንቨርሲቲ ምሩቁና የቀድሞ የመረጃ ደህንነት ሰራተኛ የነበረው ዶ/ር ሰለሞን ኪዳኔ ሲሆን ከመጀመሪያውኑ የሜቴክን አላማ ለማሳካት የተተከለ ወታደር ነው፡፡

በመጀመሪያ አዲስ የሚቋቋሙትን ተቋማት ከመደበኛ የሲቪል ሰርቪስና የፋይናንስ ቢሮክራሲ በማስወጣት በቦርድ እንዲተዳደር ማድረግ ሲሆን የቦርድ አባላቱም ባብዛኛወቹ አብሮ በላተኞችና በዶ/ሩ የተመረጡና የቀድሞ የመከላከያ ምሩቃንን የሚያጠቃልል ነበር፡፡ ከንቲባውም ቦርዱን አንድ ቀን ሳይሰበስበው ዶ/ሩ ሁሉን የሚያዝ ሆነ፡፡ ከዚህ በኃላማ ማን ይመልሰው……ልጁ ቀማኛ …አባቱ ዳኛ ሆነው እርፍ! የከተማይቱ ነዋሪ የሚፈልገው ግማሽ ኪሎሜትር ከሚደርሰውን የታክሲ ወረፋ የሚገላግለው ሆኞ ሳለ ባለ 15 ፎቅ ፓርኪንግ፣ ደብል ዴክ የአቶቢስ ማቆሚያ፣ ተርሚናሎች፣ የማይሰሩ የትራፊክ መብራቶች በየአደባባይ መትከል….ብቻ በአጠቃላይ ሜቴክ እንደሚያረገው ጉፋያውን መንፋት ብቻ ሆነ፡፡ ለዚህም ከከንቲባውና ምክትሉ አቶ አባተ ስጦታው ጋር ልዩ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ነባሩን አንበሳ አውቶቢስን (ከአፄው ጊዜ ጀምሮ የነበረ) እንደማጠናከር ፋንታ ሌላ በዚሁ ትራንስፖርት ቢሮ ስር የሚተዳደር አዲስ ሸገር አውቶቢስ የሚባል በመፍጠርና ሜቴክን በአውቶቢስ ግዢ ማክበር ሆነ ዋነኛው አላማ፡፡ በአምባሳደር ሱለማን ደደፎ ደብዳቤ ላይ እንደተገለፀው አዲስ የመርከብ ንግድ ሊጀምሩ እንዳሰቡት ማለት ነው!
ለዚህም ከመስተዳድሩ የሚበጀትና ከአለም ባንክ ሊገኝ ከታሰበው ከ300 ሚሊዮን ዶላር አብዛኛው ለሜቴክ አውቶቢስ መግዢያና ለትራፊክ መብራት መትከያ የሚውል ሲሆን ሜቴክ እስከ አሁን ወደ 1000 አውቶቢስ አገር ዉስጥ ገጣጥሞ ለመስተዳድሩ ያስረከበ ሲሆን አሁን ደግሞ የ750 አውቶቢስ አዲስ ውል አስሯል፡፡ እንደ ሪፖርተር ጋዜጣ ሃተታ ሜቴክ አንዱን አውቶቢስ በ3.6 ሚሊየን ብር ሲሸጥ ሌላው በግል የሚተዳደረው አልያንስ ባስ ደግሞ ተመሳሳይ አውቶቢስ በ 1.6 ሚሊየን ከቻይና ያለቀለት ያስመጣል፡፡ ልዩነቱ የአልያንስ አውቶቢስ ካሜራ ስላልተገጠመለት ብቻ ነው!! በጣም አስቂኝና የሜቴክ- ከንቲባው ድብቅ አላማ ፍንትው አድርጎ ያሳያል፡፡ ይሄም ሜቴክ አደናጋሪ ቃላት በሲቨል መስሪያቤቶች በወተፋቸው ወታደሮቹ እያስነገረ ህዝቡን ማደኸየትና መሰረታዊ ለውጥ በማሓከለኛው ሃገር እንዳይመጣ በማድረግ የፖለቲካዊ አላማውን ያስፈፅማል፡፡ ሌላው የሜቴክ ዘመዶች ደግሞ የተሳተፉበት የሰብ-ኮንትራት ቢዝነስ በትራፊክ መብራት በመትከል ሰበብ ዘመዶቻቸውን ዊስኪ ጨብጠው ለሊቱን እንዲያነጉ ያደረጓቸዋል፡፡ ለዚህም ወደ 170 ሚሊየን ዶላር አዲስ የተመደበ የወንበዴው ወርልድ ባንክ ብድር መንገድ ላይ ነው፡፡ ለዚሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወንድም አቶ ገነቱ ደሳለኝን ስራ አስኪያጅ አድርጎ ዝርፊያውን መሸፋፈንና አጋላጭ እንዳይኖር ማድረግ ነው፡፡
ይህን ሁሉ ስናይ እነዚህ ሰዎች ሁዋላ ከማን ጋር ሊኖሩ ነው የሚለው የሚያስጨንቅ ጥያቄ በአምሮየ ይመላለሳል …..ውይይይ… ሰው ልቦና ከሌለው ለምንም አይሆንም…ለልጆቻቸው ግን ወየዎላቸው……..ግፉ ሲበዛ በሃይለኛው መልሶ ይገፋችኃል፡፡ በ 1960ዎቹ የተማሪ ንቅናቄ ጊዜ የምንለው ነበር……ነቅናቂው ተነቃናቂውን ሲነቀንቀው ተነቃናቂው ነቅናቂውን መልሶ ነቀነቀው!! …..ሰው እያወቀ ነው ዝም ያለው……. ልብ ግዙ ነው ምክሬ!!!! በሚቀጥለው ደግሞ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ኤጀንሲን ላይ አስነብባቹሃለሁ፡፡
ሠላም ሁኑ!

Wednesday, August 9, 2017

“የባህር ዳሩ ዕልቂት አይረሳም.. ሕዝቡ ሰማዕታቱን ሲያስብ አደራቸውን መርሳት የለበትም” – አክቲቭስት ሙሉነህ ዮሐንስ (ጠቃሚ መረጃዎችን የያዘ ቃለምልልስ) sorce zehabesha

“…በባህር ዳር በአንድ ቀን የፈሰሰው የንጹሃን ደም የሚረሳ አይደለም:: ሕዝቡ ሰማዕታቱን ሲያስብ አደራቸውን መርሳት የለበትም…የለውጥ ፈላጊው ተቃዋሚ እርምጃን በተለይ የእውነተኛ ትብብር አለመኖር አንዱ ከአንዱ ጋር ተባብሮ ያለመስራቱን በተመለከተ በተለይ ሚዲያው ግልጽ ውይይት የሚደረግበትን የህዝቡ ትግል በእውነት የሚደገፍበትን ለለውጡ የሚደረገው እንቅስቃሴ ትርጉም ያለው እንዲሆን ሀላፊነት ያለባችሁ ይመስለኛል…”  አክቲቪስት ሙሉነህ ዮሐንስ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከሰጠን ማብራሪያ (ቀሪውን ያድምጡት)