Tuesday, November 1, 2016

በኢትዮጵያ የኣስቸኳይ ጊዜ ኣዋጁን ተከትሎ የውጪ ድርጅቶች የእርዳታ ስራዎች በኣብዛኛው እንቅስቃሴ ቀንሰዋል።። ሰራተኞቹንም ጭጭ ኣሰኝቷል።#MinilikSalsawi



#Ethiopia #StateofEmergency በኢትዮጵያ የኣስቸኳይ ጊዜ ኣዋጁን ተከትሎ የውጪ ድርጅቶች የእርዳታ ስራዎች በኣብዛኛው እንቅስቃሴ ቀንሰዋል።። ሰራተኞቹንም ጭጭ ኣሰኝቷል። #MinilikSalsawi #NGO
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) በኢትዮጵያ ውስጥ ወራቶችን ያስቆጠረው በኣገዛዙና በሕዝብ መካከል የተነሳውን ግጭት ተከትሎ የገዢው ፓርቲ ያወጀው የኣስቸኳይ ጊዜ ኣዋጅ በተለያዩ ተቋማት ላይ ገደብ በመጣሉ ነጻ ፕሬስ በማገዱ የሲቪሎችንና የዲፕሎማቶችን እንቅስቃሴ በመገደቡ የውጪ ድርጅቶች የእርዳታ ስራዎች እንቅስቃሴ ቀንሰዋል። የወያኔ ኣገዛዝ በፈጠረው ሳንካ እርዳታ ፈላጊው ሕዝብ በጣም እየተጎዳ ነው።
በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ ኣለም ኣቀፍ የእርዳታ ድርጅት ማህበረሰብ ኣባላት በኢትዮጵያ የተከሰተው ቀውስ በስራቸው ላይ እያደረሰ ያለውን ተጽእኖ ከመናገር ይልቅ ዝምታን በመምረጥ ኣብዛኛዎቹ ስራቸውን እንቅስቃሴ ቀንሰዋል። መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በፍርሃት ተወጥረዋል። ከደርዘን በላይ የሚሆኑ በሰብዓዊ እርዳታና በልማት ስራዎች ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች እንዲሁም የተባበሩት መንግስታተ የእርዳታ ኣስተባባሪ ቃለመጠይቅ ለመስጠት ፈቃደኛ ኣይደሉም።ኣብዛኛዎቹ ድርጅቶች ኣደጋ ውስጥ የሆኑ ያህል ሆኖ እንደሚሰማቸው ታውቋል።
የጸጥታ ሃይሎች በሕዝብ ላይ የሚወስዱት እርምጃ ለእርዳታ ሰራተኞች እንቅፋት ከመሆኑም በላይ የሰብዓዊ ቀውስ ኣስከትሏል። የትራንስፖርት ችግር የኢንተርኔት መቆራረጥ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን ረሃብ ለማስታገስ በስራ ላይ ለተሰማሩ የውጪ ድርጅቶች የመንግስት ሃይሎች ሊያሰሩ ኣለመቻላቸው ተጠቁሟል። #ምንሊክሳልሳዊ — ዝርዝር ዘገባው እዚህ ሊንክ ላይ ቀጥለው ያንብቡ :- http://mereja.com/…/ethiopia-s-state-of-emergency-silences-…
Image may contain: 6 people , text

...

No comments:

Post a Comment