Sunday, November 27, 2016

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይቀጥል ማለት ግድያው አፈናውና እስሩ ይቀጥል ማለት ነው። ኢዴፓ የሕወሓትን የስልጣን ዘመን ለማስረዘም እየተጋ ነው።ምኒሊክ ሳልሳዊ



የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይቀጥል ማለት ግድያው አፈናውና እስሩ ይቀጥል ማለት ነው። ኢዴፓ የሕወሓትን የስልጣን ዘመን ለማስረዘም እየተጋ ነው። 
 
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ከወያኔ ታማኝ ተቃዋሚዎች አንዱ ኢዴፓ የተባለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዳይነሳ እያለ ወያኔን እየተማጸነ ነው። ለምን ሲባል የሕዝብ ጥያቄ መመለስ አለበት ብለዋል።የሕዝብ ጥያቄ ለመመለስ ኣስችኳይ ጊዜ አዋጅ ኣስፈላጊ ኣይደለም ፖለቲካ ለሚያውቅ ሰው ከገባው። የሕዝብ ጥያቄ ደግሞ ወያኔ ስልጣን ይልቀቅ ነው፤ የሕዝብ ጥያቄ ይመለስ ማለት ወያኔ ከስልጣን ይውረድ ከሆነ የ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኣስፍላጊ ስላልሆነ ወያኔ ስልጣኑን መልቅቅ ኣለበት።
 
አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወያኔ ሃይልን ተጠቅሞ በስልጣን ለመቆየት በጭንቀት የወለደው መሆኑ ይታወቃል።የኣስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኣይነሳ ይቀመጥ ማለት በሕዝብ መብትና ነጻነት ላይ መዘባብት ነው። ግድያው አፈናውና እስሩ ይቀጥል ማለት ነው።ይህ አዋጅ ክቀድሞ ኣፈና በበለጠ መልኩ የሕዝብን መብት የሸረሸረ በኣስር ሺዎች የሚቆጠሩትን ወደ እስር ማጎሪያ ካምፖች ያስገባ ገዳይና ጨቋኝ አዋጅ ነው። ይህ አዋጅ ኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆኑ ምእራባውያን ሳይቀር እንዲነሳ እየታገሉ የኢዴፓ የ አ ስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኣይነሳ ምስጢር ግን ምን እንደሆነ ሕዝብ ይፍታው። #ምንሊክሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment