Monday, November 28, 2016

ለሕዝብ እንቆረቆራለን የሚሉ በስድብ ፖለቲካ ሲናቆሩ ሕወሓት በደቡብ ክልል የኮንሶ ሕዝብ ላይ አዲስ ጭፍጨፋ ጀምራለች።Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)



ለሕዝብ እንቆረቆራለን የሚሉ በስድብ ፖለቲካ ሲናቆሩ ሕወሓት በደቡብ ክልል የኮንሶ ሕዝብ ላይ አዲስ ጭፍጨፋ ጀምራለች።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) የለውጥ ሃይል ነኝ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነኝ የብሄር ፖለቲካ ኣራማጅ ነኝ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው አትኩሮቱና ተግባሩ ሁሉ ቢመከር በማይመልስበት የዘለፋና የቅፈላ ፖለቲካ ላይ ባተኮርበት በዚህ ወቅት ላይ ወያኔ በሕዝቦች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃውን ቀጥሏል።ከቃላት ጦርነት ይልቅ ለሕዝብ የሚጮህ የሕዝብን ዋይታ የሚያስማ የሕዝብን ትግል የሚጋራ ወገን ያስፈልጋል። ለአለም ማህበረሰብ ማጋለጥ የለውጥ ሃይሉ ግዴታ ነው።
በኮንሶ ሰዎች አሁንም በጅምላ እንደሚታሰሩ፣የኮንሶን ሕዝብ ወክለው ጥያቄ ያቀርቡ የነበሩ የኮሚቴ አባላት የተወሰኑት መታሰራቸውን አብዛኞቹ ደግሞ መኖሪያ መንደራቸውን ትተው መሰደዳቸውን እኛም በስደት ጫካ ገብተን ነው የምናነጋግራችሁ ሲሉ የኮንሶ ነዋሪዎች ነን ያሉ ሁለት ሰዎች ቤተሰቦቻቸው እንደታሰሩባቸው፣ በኮንሶ የተነሳውን በዞን የመደራቸት ጥያቄ ያነሱ ሰዎች ቀያቸውን ጥለው ጫካ መግባታቸውንና እየተፈጠሩ ባሉት ሁኔታዎች ግራ እንደተጋቡ ለአሜሪካ ድምጽ ተናግረዋል።ወያኔ ሕዝብን እየጨፈጨፈ ባለበት በዚህ ወቅት መነታረክ ለወያኔ ወንጀሎች ሽፋን መስጠት ነው። ለአለም ማህበረሰብ ማጋለጥ የለውጥ ሃይሉ ግዴታ ነው። #ምንሊክሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment