Wednesday, November 23, 2016

በገዛ ወገኖቻችን አማካኝነት እህቶቻችን ላይ ስውር ግን ዘመናዊ የባሪያና የወሲብ ንግድ እየተፈፀመ ነው

  


አሳዛኙ ጉዞ ቀጥሏል !
እኛም መጮሀችንን አላቋረጥንም!
Nubiya Kush Kedamawi(መሳይ አክሊሉ)
“እህቶቻችን የባንጋሊ፣ የህንድና፣ የፓኪስታኒ መጫወቻ እየሆኑ ነው,,,”
“በገዛ ወገኖቻችን አማካኝነት እህቶቻችን ላይ ስውር ግን ዘመናዊ የባሪያና የወሲብ ንግድ እየተፈፀመ ነው,,,,”
“የመጡበትንም ሆነ አመጣጣቸውን በጭራሽ የማያውቁ አሉ,,,”
“በኦማን ብቻ ከ40 የማያንሱ ኢትዮጵያውያን ያለ አሻራ በባህር ትገባላችሁ በሚል በራሳችን ሀገር ሆዳምና ህሊና ቢስ ደላላዎች ተታልለው እስር ቤት ከገቡ 4 ወር አልፏቸዋል,,”
ሰላማችሁ ይብዛልኝ ውዶቼ እንዴት ናችሁ? በናንተ ፀሎት፣ ምርቃትና፣ መልካም ምኞት ይኸው በፈጣሪ ጥበቃ አለሁ።
ላለፉት ሁለት ቀናት በርከት የሉ ጥቆማዎች የመልዕክት ሳጥኔ ውስጥ ተሰትረው አነበብኩ። ሃሳባቸው ስለ ህገወጥ የዱባይ የሰራተኛ ጉዞ ነው።
ከ 2013 ጀምሮ በተለይም በሳኡዲ አረቢያ ሀገር በሪያድ ከተማ መንፉሃ በተሰኘው አካባቢ ውስጥ ከደረሰው አሳዛኝ የኢትዮጵያውያን ሞትና ሰብዓዊ መብት ረገጣ በጟላ ወደ አረብ ሀገራት የሚደረገው የሰራተኛ ጉዞ በሞላ ማለት ይቻለል መዘጋቱ ይታወሳል።
ሆኖም ግን በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደተለያዩ የአረብ ሀገራት የሚደረገውን ጉዞ እገዳው በፍፁም ሊያስቆመው አልቻለም።
ዛሬም በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል በመቶዎች የሚቆጠሩ እንስቶች ወደ ዱባይ አየር ማረፊያ መጉረፋቸውን አላቆሙም።
“ከነገ ወዲያ ወደ ዱባይ ልበር ነው,,, ”
ብታምኑም ባታምኑም ከሰዓታት በፊት ይህን መልዕክት በስልክ የላከችልኝ በቅርቡ 20ኛ ዓመቷን ያከበረች በቅርብ የመውቃት ሴት ነት።
በአስተሳሰብ ብስለት፣ በአካላዊ ብቃት እና በማህበራዊ ግንኙነት ክህሎት ብቁ ያልሆኑ ትናንሽ እህቶቻችሁን እና ልጆቻችሁን ከጉያችሁ እየፈለቀቃችሁ ገንዘብ እየሰጣችሁ ወደ ባርነት የምትልኩ ቤተሰቦች ምን አይነት ህሊና ነው ያላችሁ በፈጣሪ?
ዱባይ አየር ማረፊያ ላይ የሚገቡትን ሴቶች እየተቀበሉ የሚወስዱት እነማን ናቸው????
ባንጋሊዎች፣ ህንዶች ፣ ፓኪስታኒዎች እናም ሴቶቻችን ወዴት እንደሚሄዱ ሳያውቁ እንደበግ እየተነዱ ወደማያውቁት የጭለማ ዓለም ይወሰዳሉ ከዛስ ቤተሰብ በስድስት ወሩ ልጄ ድምፇ ጠፋ ብሎ የአዞ እንባ ማንባት አጉል እዬዬ።
የዱባይ መንግስት ለቪዚት ቪዛ እንኳ የዕድሜ ገደብ ወስኗል ለሴት 30 ለወንድ 28 ብሎ የ 20 እና የ18 ዓመት ልጆችን እየወሰዱ በየካፍቴሪያው በየሺሻ ቤቱ መማገድ ከቶ ግፍ አይደለምን?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ የሚገኘው የኢሚግሬሽን ንዑስ ክፍልስ ለምን የሚወጣውን ሰው የእድሜ እና የሂደቱን ምክንያት አይቆጣጠርም? ምኑ ከብዶ ነው?
ስለእውነት እህቶቻችን እያለቁ፣ እየተበላሹ፣ ወደ ጭለማ እየተነዱ ነው በየገጠሩ በየእርሻ ቦታው ቤትና ግቢ ተዘግቶባቸው፣ የረሀቡና የደሞዝ ክልከላው ሳያንስ በፆታዊ ጥቃት የእድሜ ልክ የህሊና ቁስል እየላጡ ከዓለም ተገልለው በስቃይ የሚኖሩትን አምላክ ያያቸዋል።
ሰው ከሀገሩ ወጥቶ አይስራ የሚል አቋም የለኝም ግን ሁሉም በህግና በአግበቡ ይሁን ነው በደህንነትና በሰላም ሰርተው ከራሳቸው አልፈው ለብዙዎች የተረፉ አሉ ግን በዚህ መልክ አይደለም።
አስቸኳይ መፍትሄ ያስፈልጋል ቁጥጥር ሊኖር ግድ ነው
ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ፣
የሴቶች ጉዳይ፣
የውጪ ጉዳይ,,, ሌሎቻችሁም የመንግስት አካላት የናንተ እርምጃዎች ወሳኝ ናቸው የነገ ሀገር ተረካቢ ትናንሽ እህቶቻችንን እንታደግ።
No automatic alt text available.

No comments:

Post a Comment