Thursday, November 10, 2016

ሕወሓት በመካከለኛ እና ዝቅተኛ የብአዴን ኣባላት ላይ እርምጃ ሊወስድ ነው።Minilik Salsawi –



ሕወሓት በመካከለኛ እና ዝቅተኛ የብአዴን ኣባላት ላይ እርምጃ ሊወስድ ነው።

ማፊያው የሕወሓት ቡድን ከኣማራው ሕዝብ ጎን የቆሙ የመካከለኛና ዝቅተኛ የብአዴን ኣባላት ላይ እርምጃ ሊወስድ መሆኑን መረጃዎች ጠቆሙ። በመካከለኛና በዝቅተኛ የብአዴን ኣባላት ላይ እርምጃ እንዲወስድ የሕወሓት ኮማንድ ፖስት ሙሉ ሃላፊነት ተሰቶታል። በክልሉ ውስጥ የተነሳውን የሕዝብ ተቃውሞ ከጎን ቆመዋል ድርጅታችንን ከድተዋል የተባሉትን የብ አዴን ኣባላት ጨምሮ በኣጠቃላይ በመካከለኛ እና ዝቅተኛ ኣባላት ልይ እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቱ ሲጠቆም እርምጃው ከግድያ ጀምሮ እስከ ጅምላ እስር መሆኑን የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል።
ምንጮቹ እንዳሉት የብአዴን ኣባላት ቀድመው እርምጃውን ማክሸፍና ሕዝቡ ኣስተባብረው በክልሉ ያለው የሕወሓት ሰራዊትና ኮማንድ ፖስት ብሎ ራሱን የሚጠራው ገዳይ ቡድን ላይ ኣስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ መክረዋል።

No comments:

Post a Comment