Monday, August 15, 2016

Camp111 የተባለ ኣዲስ የሜካናይዝድ ጦር ተቋቁሞ በቅማንቶች መሬት ላይ ሊሰፍር ነው።



Camp111 የተባለ ኣዲስ የሜካናይዝድ ጦር ተቋቁሞ በቅማንቶች መሬት ላይ ሊሰፍር ነው።


ከሕወሓት ኣገዛዝ ወታደራዊ ደህንነቶች የሚደርሱ መረጃዎች እንደጠቆሙት ሕወሓት ከመከላከያ ሰራዊቱ ከሚሊሻዎችና ከቀድሞ የሕወሓት ታጋዮች የትግራይ ተወላጆችን በመመልመል ስልጣኑን የሚያስጠብቁለት የኣማራውን ሕዝብ ይመቱልኛል ያላቸውን ታማኝ ወታደሮች በኣንድ የሜካናይዝድ ጦር ስር በማሰባሰብ በቅማንቶች መሬት ላይ ግዙፍ ወታደራዊ ካምፕ111 በመገንባት ሊያሰፍር መሆኑን ተጠቁሟል።
Image may contain: text
ዘረኛው የሕወሓት ኣገዛዝ የቅማንትን ሕዝብ መጠቀሚያ በማድረግ በጀግንነት
የሚኖረውን እና ቀልቡን የገፈፈለትን የኣማራን ሕዝብ ለመምታት ማሰቡ በራሱ ላይ መርዛም እባብ እየጠመጠመ ነው የሚሉት ኣደራጆቹ ወታደራዊ ደህንነቶቹ የቅማንት ሕዝብ በቅርቡ የሚያውቀውና የሚያምነው ኣማራን ነው ሲሉ ሕወሓት በገዛ እጁ ያሰፈራቸው የትግራይ ተወላጆች ሳይቀሩ ከፍተኛ ኣደጋ ውስጥ መሆናቸውን ሲጠቁሙ በኣሁኑ ወቅት ለም ከሆኑ የኣማራ መሬቶች በተለይ ከሰሜን ጎንደር ሕወሓት ያሰፈራቸውን ኣባላቶቹን እንዲያነሳ ከማይታወቅ ኣካል ማስጠንቀቂያ ደርሶታል።በኣጠቃላይ በኣማራ ክልል ውስጥ ወልቃይትን ጨምሮ የሰፈሩ የትግራይ ተወላጆች በከፍተኛ ኣደጋ ውስጥ በስጋት እየኖሩ ነው ሲሉ ምጮቹ ይናገራሉ፥ ሕወሓት ያለው እድል ሕዝቡን ካአደጋና ከስጋት ለማላቀቅ ኣንድም ኣከባቢውን ለነጠቀው የወልቃይት ሕዝብ ማስረከብ እና ለቆ መውጣት ኣሊያም ሕዝቦች እንደድሯቸው ተፈቃቅረና ተከባብረው እንዲኖሩ ነጻነታቸውን ማክበር ያስፈልጋል፤የሰሜን ጎንደር ሕዝብ መሬቱን ተነጥቆ እንዲሁ እንደማይኖር ሁሉ መሳሪያን ለማስፈታት ማሰብ ወደባሰ የእርስ በርስ ጦርነት መግባት ነው ሲሉ ምንጮቹ ተናግረዋል።

No comments:

Post a Comment