Tuesday, August 30, 2016

በአማራ ክልል የሕዝቡ ተቃውሞ ዛሬም ተቀጣጥሎ ቀጥሏል።ከፍተኛ የተኩስ እሩምታ እየተሰማ ነው።




በአማራ ክልል የሕዝቡ ተቃውሞ ዛሬም ተቀጣጥሎ ቀጥሏል።ከፍተኛ የተኩስ እሩምታ እየተሰማ ነው።
#Ethiopia #Amharaprotests #BahrDar #AmharaResistance #MinilikSalsawi
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) በባህር ዳር ተቃውሞ ዛሬም ተቀጣጥሎ መቀጠሉ ታውቋል።ከባሕር ዳር 45 ኪሎ ሜትሮችን በምትርቀው የጉማራ መንደር እስከ ዛሬ ሌለት ድረስ በቆየ የተኩስ ልውውጥ 8 የወያኔ ፌደራሎች ተገድለዋል። 2 ዐማሮች በተጋድሎው ተሰውተዋል። የ8 ፌደራል ሙሉ ትጥቅ ገበሬው ተከፋፍሏል። መንገዶች ዝግ ሲሆኑ ሕዝቡም ራሱን እያስተደዳረ ነው።በባህር ዳር እና አዋሳኝ በሆኑ ከተሞች በህዝብና በወያኔ ቅልብ ወታደሮች መካከል ውጊያ እየተካሄደ ነው፡፡
Minilik Salsawi's photo.
ከባህር ዳር ወደ ጭስ አባይና አዴት ሞጣ ቢቸና በሚወስደው መንገድ ላይ በምትገኘው ሰባታሚት ላይ የአማራ ህዝብ ወያኔን በአኩሪ ጀግንነት እየተፋለመ ነው፡፡በባህር ዳርም ቀበሌ 7 እና 17 ከፍተኛ የተኩስ እሩምታ እየተሰማ ነው። ወያኔ በማንኩሳ ዐማሮች ላይ ሙለ ጦርነት አውጇል።ከማንኩሳ አካባቢ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው የወያኔ ነፍሰ ገዳይ ወታደሮች ሕጻናትን ጨምሮ በደካሞችና አዛውንቶች ላይ ሁሉ እያነጣጠሩ እየተኮሱ ነው።ማንኩሳ ማንኛውም ዓይነት መረጃ መለዋወጫ መንገድ ተዘግቷል። #ምንሊክሳልሳዊ
Minilik Salsawi's photo.
Minilik Salsawi's photo.


No comments:

Post a Comment