Sunday, August 28, 2016

ከአ.አ. ወደ ባህርዳር የሚወስደው መንገድ ደምበጫ ድልድይ ሰልፈኞች ዘግተውታል



አማራ ተጋድሎ ዛሬም ተቀጣጥሎ ቀጥሏል::
ከአዲስ አበባ ወደ ባህርዳር የሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘውን ደምበጫ ድልድይ ሰልፈኞች ዘግተውታል። የመንገድ መዝጋቱ ዓላማ የወያኔን ኢኮኖሚ ለማዳሸቅ ነው። የመንገድ መዝጋቱ እንቅስቃሴ በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ በነዳጅ እጥረት ምክንያት በቅርብ ጊዜ ውስጥ በአዲስ አበባ የሚንቀሳቀስ ተሽከርካሪ አይኖርም።
እንዲሁም ከባህርዳር ወደ አ.አ የሚያስገባው ሙሉአለም ችግኝ ሀሙሲት ላይ ተዘግቷል::
ብዙ የወያኔ ታፔላወች ተሰባብረዋል።”ወያኔ ሌባ” “ወያኔ ሌባ” ደምቆ የስተጋባል ሰልፈኞች ያስተጋቡት ጩኸት ነበር። የገብያ ቀን ቢሆንም አርሳ አደሮች ወደ ከተማ እንዳይገቡ በሚሊሻዎች ታግደዋል። በርካታ ወጣት እየጨፈረ ነው።ከተለያዬ ሰፈር ሰልፉን ለመቀላቀል አሁንም ህዝቡ እየተመመ ነው



No comments:

Post a Comment