Wednesday, August 3, 2016

በኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ላይ ክስ የተመሰረተው ኣዲስ ኣበባ ሲሆን ጎንደር ላይ የቀረበው ክስ ከሳሽ የለውም።

  


በኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ላይ ክስ የተመሰረተው ኣዲስ ኣበባ ሲሆን ጎንደር ላይ የቀረበው ክስ ከሳሽ የለውም።
በኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ላይ ክስ የተመሰረተው ኣዲስ ኣበባ ሲሆን ጎንደር ላይ የቀረበው ክስ ከሳሽ የለውም።
የጎንደር ሕዝብ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ተላልፎ ቢሰጥ ወዮላቹ ሲል የኣማራ ክልል ባለስልጣናትን ኣስጠንቅቋል።
በወልቃይት የኣማራ ማንነት ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ ሲያደርጉ እና ማነታቸውን ለማረጋገጥ ትግል ከሚያደርጉት የኮሚቴ ኣባላት ኣንዱ የሆኑት ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ከትግራይ ክልል ጨለማን ተገን ኣድርገው ለኣፈና የመጡ የሕወሓት የደህንነት ሃይሎችን ተልእኮ ካከሸፈ በኋላ በሕዝብ ፍቃደኝነት በኣደራ በኣማራ ክልል መንግስት ወህኒ ቤት እንዲቀመጥ የተደረገ ሲሆን ክስ ተመስርቶበታል ተብሎ ጎንደር ፍርድ ቤት ቤት ቢቀርብም ከሳሽ ስላሌለው ኣሁንም በኣንገረብ ወህኒ ቤት ይገኛል።
በትላንትናው እለት ከጎንደር እና ከኣዲስ ኣበባ ታፍነው በተወሰዱ ሕጋዊ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ወኪሎች እና የኣማራ ማንነት ለማረጋገጥ ሲሰሩ የነበሩ ኮሚቴዎች እና ተባባሪ ኣባላት ላይ ክስ የተመሰረተ ሲሆን በኣዲስ ኣበባ ከቀረበው ክስ ላይ በኣራተኛ ተከሳሽነት ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እንደሚገኙበት ለማወቅ ተችሏል። በዚህም መሰረት የኣዲስ ኣበባው የሕወሓት ፍርድ ቤት ኮሎኔሉ ተላልፈው እንዲሰጡት ለኣማራ ክልል ደብዳቤ ይጽፋል ተብሎ ሲጠበቅ የጎንደር ፍርድ ቤት ጉዳዩን የማየት ስልጣን የለውም በማለት ጎንደር የተሰየሙ ዳኞች ኣራት ለኣንድ ድምጽ ሰጥተው ውጤቱ እየተጠበቀ ሲሆን የጎንደር ሕዝብ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ተላልፎ ቢሰጥ ወዮላቹ ሲል የኣማራ ክልል ባለስልጣናትን ኣስጠንቅቋል።
ከወልቃይት የአማራ ማንነት ኮሚቴ ስለ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዴ በትክክል እሰከ አሁን ድረስ ያለን መረጃ የሚከተለው ነው።ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ አሁንም ከዚህ በፊት እንደነበረው በህዝብ አደራ በተሰጠበት እንዳለና በየጊዜው የምንጎበኘው መሆኑን እያሳወቅን ለማዕከላዊ ተላልፎ ሊሰጥ ነው የሚሉ መላምንቶች ከእውነት የራቁ መሆናቸውን እየጠቀስን ኮሬኔል ተላልፎ እንዳይሰጥ የጎንደር ህዝብ በቂ ክትትል እያደረገ መሆኑን ታወቆ የአማራ መንግስት ከአቅሙ በላይ ቢሆን እንኳ መልሶ ለህዝብ እንደሚያስረክብ ተስማምቷል። ይህ ተጥሶ ኮሎኔሉ ተላልፎ ቢሰጥ ከፍተኛ መስዋህት ሊያስከፈል እንደሚችል ለክልሉ መስተዳደር ከወዲሁ አሳስበናል። እንኳን ኮሬኔል ሊወሰድ የተወሰዱትን ሳናስለቅቅና ወልቃይትን ሳናስመልስ እንቅልፍ የለንም።

No comments:

Post a Comment