Thursday, August 25, 2016

ፍኖተ ሰላም የጦር ቀጠና ሆና ስታመሽ ገዱ ኣንዳርጋቸው ዛሬም የሕዝብን ጥያቄ የጸረ ሰላም ሃይሎች ሴራ ነው ይላል።



ፍኖተ ሰላም የጦር ቀጠና ሆና ስታመሽ ገዱ ኣንዳርጋቸው ዛሬም የሕዝብን ጥያቄ የጸረ ሰላም ሃይሎች ሴራ ነው ይላል። Minilik Salsawi
Minilik Salsawi's photo.
ከትላንትና የተጀመረው በምእራብ ጎጃም ዋና ከተማ ፍኖተ ሰላም ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን ሕዝቡ በከፍተኛ ደረጃ ተቃውሞ ሲያሰማ ውሏል። መከላከያ፣አማራ ልዩ ሀይል፣የገጠር ሚሊሻ በጥዋት ከተማ ገብተዋል ። ተቃውሞው ዛሬም ገንፍሏል።አስለቃሽ ጭስ ወደ ህዝቡ እየበተኑ ነው። ባከል ሰፈር ከፍተኛ ተኩስ አለ።ፖሊስ ከህዝብ ጎን ነው።
ትላንትና በጎንደር የተነሳውን የሕዝብ ኣመጽና ኮሎኔል ድመቀ ዘውዱን ኣፍኖ ለመውሰድ የተደረገ ኦፕሬሽን መክሸፉን ተከትሎ ገዱ ኣንዳርጋቸው የተባለ የሕወሓት ተላላኪ ለሕወሓት ሚዲያ ፋና መግለጫ መስጠቱ የተሰማ ሲሆን ኮሎኔል ደመቀን በወንጀል ተጠርጥሮ የታሰረ ሰው ሲል ከሕዝብ ላይ በኣደራ እንደተረከበ በመዘንጋት ክዷል፤ የጎንደር ሕዝብ ጥያቄን የጸረ ሰላም ሃይሎች ሴራ በማለት የሕዝብን ጥያቄ ወደ ጎን ጥሎ ሲዘባበት ተሰምቷል። ከሕዝብ ጋር እንመካከራለን እንወያያለን የሚሉትን የሕወሓት መሰሪ ማዘናጊያ የሃሰት ዲስኩር ያሰማው ገዱ ኣንዳርጋቸው በክልል ያለውን ችግር ፈቶ ሰላም በማስፈን የሕዝብን ነጻነት ከማረጋገጥ ይልቅ ከሕወሓት ጦረኞች ጋር በመሆን ሕዝብን ለመፍጀት ዝቷል፥ሕዝብ ግን ሁሌ ኣሸናፊ እንደሆነ በተግባር ኣሳይቶ ኣረጋግጧል። #MinilikSalsawi
Minilik Salsawi's photo.

No comments:

Post a Comment