Thursday, December 1, 2016

ዶ/ር መራራን ማሰሩ ኢህአዲግ እንደልማዱ ተዳፍኖ በነበረው እሳት ላይ ቤንዚን ጠብ አደረገ !!Dereje Gerefa Tullu



ኢህአዲግ እንደልማዱ ተዳፍኖ በነበረው እሳት ላይ ቤንዚን ጠብ አደረገ !! Dereje Gerefa Tullu
ዶር መራራ ኢህአዲጎችን ብዙ ጊዜ በሁለት ነገር አንጀታቸውን እንደሚያቆስላቸው ይታወቃል።
አንዱ ከሰው ጭንቅላት የማይጠፉ አጫጭር አረፍተነገሮችን በመጠቀም እና ብዙ ረጃጅም የኢህአዲግ አረፍተ ነገሮችን በመደረማመስ ነው።
ለምሳሌ የሚበላውን ያጣ ህዝብ መሪውን ይበላል።
ኢህአዲግ አፍ እንጅ ጆሮ የለውም።
አቅም ያጣውን አቅም ግንባታ ትምህርት ያሌለውን ትምህርት ሚንሥቴር ወዘተ
ሌላም መጥቀሥ ይቻላል።
ሌላው የዶር መራራ ኢህአዲጎችን አቁሳይ ሥልት ስሞቅ እየቀጠቀጣቸው ኢህአዲጎች ሰው ለማሰር በንዴት ሥቅዘፈዘፉ ሃይበርኔት ያደርጋል።በዚህ መልኩ ዶር መረራ ኢህአዲጎችን ብዙ ጊዜ አምልጦአቸው አብሽቆአቸዋል።ይህንን ደግሞ በ1998 የቅንጅት መሪዎች ከታሰሩ በኃላ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናው ሳይቀሩ በፓርላማ ቀርበው ተናግረውታል።ጠቅላይ ሚንስትሩ ዶር መራራ በነገር ስጎነትሉአቸው በንዴት “ከDC እስከ አምቦ መንግሥትን ለመጣል ሰንሰለት እየዘረጉ ስከሽፍ ምንም እንዳልተፈጠረ ፓርላማ መግባት እና ማምለጥ ከዚህ በኃላ አንፈቅድም ነበር ያለወቸው።” ዶር መራራ በወቅቱ በለዘብተኛ ፈገግታ አልፈውታል።
የአሁኑን ግን ዶር መራራ በተለመደው እሥትራቴጅው (እሳቸው push and pull ይሉታል ይባላል) ከእሥር ማመለጥ የፈለገ አይመሥለኝም።ዶር መራራ ለተዳፈነው እሳት እራሱን መስዋአት በማድረግ ለማቀጣጠል የወሰነ ይመሥለኛል።እኔ በለኝ መረጃ ዶር መረራ ኢህአዲጎች ነገሮችን ሰከን ብለው እንዲያስቡ እና ነገሮችን በሚመስል መልኩ እንድፈቱ ከፍተኛ ፍላጎት እና መጠነኛ ተስፋ ነበረው።አሁን ግን ያንን መጠነኛ ተስፋውን ኢህአዲጎች በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደጉም በኖ እንድቀር ያደረጉት ይመስለኛል።ይህንን ደግሞ ከአዋጁ ማግስት በVOA ቀርቦ ተናግሮታል።
ስለዚህ የረጋ የመሰለው ማዕበል እንድናጥ ዶር መረራ አንድ ስልት መቀየስ አለበት ።ለዚህ ደግሞ እራሱን ለመሰዋዓትነት ማዘጋጀት ብቸኛ አማራጩ ነው።መቼም ከዚህ በኃላ እንደ አንዳንድ የፖለቲካ መሪዎች ጫካ ገባለሁ ብሎ አስመራ አይገባም።
ነገሮችን በኢህአዲግ በኩል ካየነው ዶር መራራን በዚህ ጊዜ ማሰሩ ቅንጣት ያክል የፖለቲካ ጥቅም የለውም።ምክንያቱም ሰውዬው አብሮ የሚሰራቸውን ሰው ሰብስበው በማስገባት ምንም ተፅዕኖ እንዳይኖረው ማድረግ ችለውበታል።ስለዚህ እሱን በማሰራቸው በሱ በኩል ልመጣ የሚችል እና ልቀንሱት የሚችሉት ምንም ዓይነት የፖለቲካ ጫና የለባቸውም።
በማሰራቸው ግን የፖለታካ ጫና ውሥጥ እንደሚገቡ ለማወቅ ፖለቲከኛ መሆን አያስፈልግም።
ሰውዬውን ያሰሩት ከአውሮፓ ህብረት ሰዎች ጋር ተማካክሮ ስመለስ ነው።ሀገር ቤት የሚናጠውን እና ለጊዜው የረጋ የመሰለውን ማዕበል እንኳን ብንተው ከነሱ ጋ በመመካከሩ እና በመታሰሩ ለክብራቸውም ጥሩ ስለማይሆን የአውሮፓ ህብረት ሰዎች የሚችሉትን ማድረጋቸው አይቀርም።
ለማጠቃለል ዶር መራራ በወሳኝ ሰዓት ላይ እራሱን መሥዋዓት በማድረግ የረጋ የመሰለውን ማዕበል መናጥ የፈለገ ይመሥለኛል።ይህ እንኳን ባይሆን አጀንዳ አጥቶ እርስ በራሱ የሚባላውን የዲያስፖራ ደጋፍያቸውን አጀንዳ በመሆን ያሰባሰብላቸዋል።።ይህም ባይሆን ከሂሊና ሸክም ይገላግለዋል።
ኢህአዲግ ደግሞ እንደበሬው ሳሩን እንጅ ገደሉን ሳያይ የረገጠው ፈንጅ አለ ቢዬ አስባለሁ።
በኔ ዕይታ የፈንጅው መፈንዳት የረጋ የመሰለውን ማዕበል መናጡ አይቀርም።
በሌላ አነጋገር ኢህአዲግ ዓመቱን ሙሉ ስያደርግ እንደነበረው ረግቶ የነበረውን የህዝብ ማዕበል ዶር መራራን በማሰር ለመቀስቀስ እየሰራ ነው።በተዳፈነው እሳት ላይ ቤንዚን ጠብ አድርጓል።አቅም ላነሳቸው ሃይሎችም ዳገት ላይ ውሃ አቀብሎአቸዋል።የቀረው የጊዜ ጉዳይ ነው

No comments:

Post a Comment