Tuesday, December 6, 2016

በቆላ ወገራ የዐማራ ገበሬዎች ተጋድሎ ያስመዘገቡት ዝርዝር መረጃ Muluken Tesfaw

  


በቆላ ወገራ የዐማራ ገበሬዎች ተጋድሎ ያስመዘገቡት ዝርዝር መረጃ – Muluken Tesfaw
በቆላ ወገራ የዐማራ ገበሬዎች በትግሬ ወያኔ ፋሽስታዊ ድርጅት የተቃጣባቸውን ጀምላ ዕልቂት በሚገባ ለመመከት ችለዋል፡፡ በጎበዝ አለቆች የተደራጁት የቆላ ወገራ ገበሬዎች በተደጋጋሚ ከሦስት ጊዜ በላይ የመጣውን የወያኔ ነፍሰ ገዳይ ቡድን እንዳለ ሲያረግፉት በቤታቸውና ንብረታቸው ላይ በከባድ መሣሪያ ማቃጠልን መርጧል፡፡ ይህንንም በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
በሦስት ጊዜ ውጊያው የሚከተሉት ድሎች ተመዝግበዋል፤
ኅዳር 17 ቀን 2009 ዓ.ም. በነበረው ውጊያ 22 የወያኔ ወታደሮች ሲገደሉ 14ቱ ደግሞ በከባድ ቆስለው የመጣው ወታደር ሙትና አስከሬን ሆኖ ተመልሷል፡፡
ኅዳር 18 ቀን 2009 ዓ.ም. በቀጣዩ ቀን ተጨማሪ ጦር ወደ አካባቢው መጥቶ ጦርነቱ ቀጥሎ ነበር፡፡ በዚህ ቀን ደግሞ 10 ወያኔዎች ተገድለው 7 ቆስለው ተመለሱ፡፡
ኅዳር 24 ቀን 2009 ዓ.ም. በባንዳዎች የሚመራ የወያኔ ጦር ድንገተኛ ጦርነት ከፍቶ ነበር፡፡ በዚህ ዕለት ደግሞ ከፍ ያለ ድል በወገራ ገበሬ ታጋዮች ተመዘገበ፡፡ 24 የነፍሰ በላ አስከሬኖችና 14 የቆሰሉ ወታደሮች ተጭነው አካባቢውን በግዴታ ለቀዋል፡፡
የተማረከ የጦር መሣሪያ፤
አንድ መትረየስ ከ260 ጥይት ጋር እንዲሁም 56 አውቶማቲክ ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች ከነሙሉ ትጥቃቸው በቆላ ወገራ የዐማራ ገበሬ ተጋድሎ እጅ ገብቷል፡፡
ከተገደሉ የወያኔ ወታደሮችና ባለሥልጣናት ጥቂቶቹ
ኮሎኔል ይመር መሰለ አቡሃይ (የጸረ ሽምቅ ወታራዊ ግብረ ኃይል አዛዥ)፣ ምክትል ሳጅን ዋጋዬ ጫቅሉ (የፀረ ሽምቅ ግበረ ኃይል አመራር) እንዲሁም ስሙ ለጊዜው ያልታወቀ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮነን ይገኙበታል፡፡
በዐማራ ገበሬዎች ላይ የደረሰ ጥፋት፤
ሴት ምላስና ሰበንተራ በተባሉ አካባቢዎች በቤታቸው ውስጥ የነበሩ አንድ አቅመ ደካማ ሽማግሌ አዛውንት እንዲሁም አንድ ልጅ ተገድለዋል፡፡ በተጨማሪም ብዙ የዐማራ ገበሬዎች ቤት በጅምላ እንዲነድ ሆኗል፡፡
(ይህ ሪፖርት የተሠራው በተጋድሎው በሰነበቱ የዐማራ ገበሬዎች መረጃና ብሎም በፍላገታቸው መሠረት መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን)

No comments:

Post a Comment