Thursday, December 15, 2016

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከነበረበት ዝዋይ ማረሚያ ቤት የት እንደተወሰደ አየታወቅም።ቆንጅት ስጦታው



ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከነበረበት ዝዋይ ማረሚያ ቤት የት እንደተወሰደ አየታወቅም።
የተለያዬ ሚድያዎች ባለቤት የነበረውና በተደጋጋሚ የሚድያ ተቋሙ የተዘጋበት እንዲሁም በፃፋቸው ፅሁፎች ህዝብን ለአመፅ አነሳስተሃል ተብሎ በ2007ዓ.ም ጥቅምት ወር የ3 አመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት ታዋቂው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ታስሮበት ከነበረው ዘዋይ ከተማ በሚገኘው የፌደራል ማረሚያ ቤት ሊያገኙት እንዳልቻሉ ቤተሰቦቹ ገልፀዋል።
የጋዜጠኛው ቤተሰቦች በዝዋይ፣ ቃሊቲ፣ ሸዋ ሮቢት፣ በቅሊንጦ በሚገኙ የፌደራል እስር ቤቶች ውስጥ እንዲሁም በማእከላዊ ወንጀል ምርመራ ተዘዋውረው ቢገልጉትም ከእስር ቤቱ ሰዎች “ተመስገን ደሳለኝ የሚባል እስረኛ አናውቅም” የሚል መልስ ተሰትቷቸዋል።

No comments:

Post a Comment