Wednesday, December 28, 2016

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እጅግ ታሟል ( Tariku Desalegn)



ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እጅግ ታሟል
በዝዋይ ባቱ ሆስፒታል የሚገኙ ምንጮቻችን እንደገለፁል ዛሬ ታህሳስ 18/09ዓ.ም ተመስገን ታሞ በአንፖላንስ ወደ ሆስፒታሉ እንደመጣ ነው፡፡ የእስር ቤቱ ወታደሮች ወደ ሆስፒታል ይዘውት ሲገቡ ቀደመው በአቅራቢያው የነበረውን ሰው ከቦታው ዙር እንዲሉ ስላደረጉ የተመስገንን የህምም ደረጅ ቀረብ ብሎ ማየት አልተቻለም፡፡ተመሰገን በእስትሬቸር እየገፉ ወደ ሆስፒታል ውስጥ አንደስገቡት ለማወቅ ችለናል፡፡አሁን ከቀኑ 8፡10 ሆናል እስካሁን ተመስገን በዝዋይ ባቱ ሆስፒታል ይገኛል::
የዛሬን ቀን በተመለከተ የዝዋይ እስር ቤት አስተዳዳሬዎችና የዛሬው የሽፍት መሪ ሻለቃ ንጉሴ እንዲሁም እስከ ዛሬ በተመሰገን ላይ ለደረሰው እና ለሚደርሰው ነገር ሁሉ መንግስት ሀላፊነቱን ይወስዳል፡፡
ታህሳስ 18/09 ዓ.ም (Tariku Desalegn)

No comments:

Post a Comment