Friday, October 21, 2016

የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ለኮማንድ ፖስት ሳያሳውቁ ከሃገር እንዳይወጡ ዕገዳ ተጣለ Command Post ban govt officials from leaving Ethiopia using the SoE : ESAT ቆንጅት ስጦታው  



በቅርቡ በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሰረት የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ለኮማንድ ፖስት ሳያሳውቁ ከሃገር እንዳይወጡ ዕገዳ መጣሉን የኢሳት ምንጮች ገለጹ። ለህዝብ ይፋ በሆነው የአፈጻጸም መመሪያ ላይ በግልፅ ባይጠቀስም ኮማንድ ፖስቱ ሳያሳውቅ ከሃገር መውጣት አይችሉም።
ዕሁድ መስከረም 29, 2009 ይፋ የሆነውና ከመስከረም 28 ጀምሮ ተግባራዊ መሆኑ የተገለፀው፣ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ በመላዋ ኢትዮጵያ ስራ ላይ መዋሉ ይታወቃል። ይህንን የሚያስጽም መመሪያ ቅዳሜ ጥቅምት 5 ፥ 2009 ይፋ ቢደረግም፣ የመንግስት ባለስልጣናትን የተመለከተው የማስፈጸሚያ ክፍል ተቆርጦ በውስጣዊ መመሪያነት ተገድቧል።
ኢትዮጵያውያን በምልክት ቋንቋ መነጋገርን ወይንም ምልክት ማሳየትን ጨምሮ በሚናገሩት ብቻ ሳይሆን በሚያዩትና በሚሰሙት ነገር ላይ ጭምር ገደብ የጣለው ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአዲስ አበባ የሚገኙ ዲፕሎማቶች ከአዲስ አበባ ከ40 ኪ/ሜትር የበለጠ መንገድ ለመጓዝ ከፈለጉ ለኮማንድ ፖስቱ ማሳወቅ ግዴታቸው መሆኑንም አስቀምጧል። በትምህርት ተቋማት ሌላው ቀርቶ በመንፈሳዊ ስፍራዎች ጭምር በሚደረጉ ሃይማኖታዊ ስብከቶች ላይ ጭምር ገደብ የሚጥለው ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የአፈጻጸም መመሪያ ከህዝቡ ግልጽ ተቃውሞ እንደገጠመው በኦሮሚያ ክልል በሜታ ሮቢ በአንድ አጋዚ ወታደር በተገደለ የ9 አመት ተማሪ ስነስርዓት እንዲሁም በጎንደር ከተማ ቢያንስ ለሁለት ቀናት በቀጠለው አድማ ታውቋል።
High ranking government officials are not allowed to leave the country without the authorization of the command post that was set up to enforce the state of emergency declared in Ethiopia a week ago, sources disclosed to ESAT.
The ban was not included in the details of the emergency law that was released last week but sources say an internal memo sent to higher officials by the command post prohibit government officials from leaving the country without the knowledge of the command post.
The so called command post is run by three veteran members of the TPLF, namely Abay Tsehaye, Debretsion Gebremichael and Samora Yunis, the sources said adding Siraj Fergessa of the OPDO was just the media face of the Tigrayan clique running the command post.
The Ethiopian regime declared a state of emergency on October 9, 2016 after a year long protest by the Oromos and the Amharas against Tigrayan domination of the economy and political power.
The people of Bahir Dar and Gondar in the Amhara region held a strike this week defying the state of emergency, although the martial law prohibits strikes and protest demonstrations, among others.
Source: Ethsat.com

No comments:

Post a Comment