Saturday, October 22, 2016

ባህርዳር ላይ የአሰቸኳይ ግዜ አዋጁን በመተላለፍ የስራ ማቆም አድማ አድርጋቹሃል የተባሉ 68 ነጋዴዎች በእስር ላይ ይገኛሉ ቆንጅት ስጦታው 



ባህርዳር ላይ የአሰቸኳይ ግዜ አዋጁን በመተላለፍ የስራ ማቆም አድማ አድርጋቹሃል የተባሉ 68 ነጋዴዎች በእስር ላይ ይገኛሉ በጎንደርም በተመሳሳይ መልኩ ከመቶ በላይ ነጋዴዎች መታሰራቸውም ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ መንግስት ታሳሬዎቹን ከነገ ዛሬ ይፈታል እያልን ብንጠባበቅም ይባስ ብሎ በአሰቸኳይ አዋጁ ደንብ መሰረት የአምስት አመት እስር ይጠበቃቸዋል እሚል ከአንድ ፖሊስ አዛዥ ተነግሮናል ፡፡
ሰለዚህ የባህርዳር ህዝብ እና ነጋዴዎች የወገኖቻችን እስር በዋዛ ፈዛዛ የምናልፈው ጉዳይ አይደለም በሚል በከተማው በቅደመ ሁኔታ የተንጠለጠለ የስራ ማቆም አድማ እና ሰልፍ ለማድረግ ህብረተሰቡ እየተመካከረ ይገኛል፡፡
1ኛ መንግስት 68 ታሳሬዎችን እስከ ጥቅምት 20 ካልፈታ ጥቅምት 30 /2009 ዓም ለ3ቀን እሚቆይ የስራ ማቆም አድማ መደረግ እንዳለበት የታሳሪ ቤተሰቦች ጥሬ አድርገዋል፡፡
2ኛ ከስራ ማቆም አድማው በኅላ መንግስት ታሳሪዎችን ለመልቀቅ ይሁንታውን ካላሳየ ጥቅምት 26 ቅዳሜ ቀን ላይ የአደባባይ ሰልፍ ከቅዳሜ ገበያ ጀምሮ ወደ ጊዎርጊስ ቤተክርስቴያን ከዛም ወደ ርዕሰ መስተዳዳር በመጓዝ ሰልፍ እንደሚደረግ ጥሬ እንዲተላለፍ እና ህብረተሰቡም ዝግጂት እንዲያደርግ መልዕክት እየተላለፈ ይገኛል ፡፡እና እናተም በገፃቹህ ይህን ጥሪ ታስተላልፋልን ዘንድ በማክበር እንጠይቃለን፡፡
የታሳሬ ቤተሰቦች

No comments:

Post a Comment