Friday, October 14, 2016

በዘረኝነት መጠቃቀሙ ቀጥሏል፤ለምርምርና ድህረ ምረቃ በኢትዮጵያ ዩንቨርስቲዎች የተመደቡት የትግራይ ተወላጆች ብቻ መሆናቸው ተረጋግጧል። ቆንጅት ስጦታው



በዘረኝነት መጠቃቀሙ ቀጥሏል፤ለምርምርና ድህረ ምረቃ በኢትዮጵያ ዩንቨርስቲዎች የተመደቡት የትግራይ ተወላጆች ብቻ መሆናቸው ተረጋግጧል።
በተለያዩ ዩንቨርስቲዎች የምርምርና ድህረ ምረቃ ትምህርት ቤት ማመልከቻ ያስገቡ ተማሪዎች ውድቅ ሆኖባቸው ትምህርት ቤቱ ከትግራይ ክልል ለመጡ ብቻ በመፍቀድ የሕወሓት የበላይነትን ማረጋገጡ በተለያዩ ዩንቨርስቲዎች የሚገኙ የኣስተዳደርና የትምህርት ክፍል የሚመለከታቸው ምሁራንና ሰራተኞች በምሬት ይናገራሉ።
በተለይ ከባህራ ዳር ዩንቨርስቲ የተገኘ መረጃ እንደሚጠቁመው ዩንቨርስቲው ለዚህ ኣመት ሊያስተናግዳቸው የፈለገውን የኦሮሚያና የኣማራ የምርምርና ድህረ ምረቃ ተማሪዎችን በመመለስ የትግራይ ተማሪዎችን እንዲቀበል ትእዛዝ መተላለፉ ታውቋል። በዘረኝነት መጠቃቀሙ የቀጠለ ሲሆን ከዚህ ቀደም እንደሚታወቀውና ኣሁንም እንደሚሰራበት በገሃድ እንደሚታየው ኣለማቀፍ ስኮላርሺፕ ከሚሰጣቸው ተማሪዎች ውስጥ ዘጠና ስምንት ከመቶው የትግራይ ተወላጆች መሆናቸው በግልጽ ይታወቃል።
ጋዜጠኛና ኣክቲቪስት ሙሉቀን ተስፋው በሰጠው ኣስተያየት ፤ እነዚህ ሰዎች እኮ ምንም እፍረት የሚባል ነገር አልፈጠረባቸውም። በውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚንስትር ለሁለተኛ ዲግሪ ወደ ባሕር ዳር ዩንቨርሲቲ የተላኩ ተማሪዎችን ዝርዝር ተመልከቱት፦የትግራይ የበላይነት የሌለባት ኢትዮጵያ ይህች ናት። ለማንኛውም የባሕር ዳር ወጣቶች ሰዎቹ ለመማር ይሁን ለሌላ ሥራ አመጣጣቸው ስለማይታወቅ በዝርዝር ማወቃችሁ አይከፋም። ብሏል።

No comments:

Post a Comment