Monday, October 17, 2016

የወያኔ ኣስቸኳይ ጊዜ ኣዋጁን ተከትሎ በጎንደር ጸረ ወያኔ ቤት የመቀመጥ ኣድማ ተጀመረ። ቆንጅት ስጦታው 



የወያኔ ኣስቸኳይ ጊዜ ኣዋጁን ተከትሎ በጎንደር ጸረ ወያኔ ቤት የመቀመጥ ኣድማ ተጀመረ።
በኢትዮጵያ የሕወሓት ኣገዛዝ የኣስቸኳይ ጊዜ ኣዋጅ ብሎ ግድያውና ኣፈናውን ሕጋዊ ያደረገበት ኣዋጅ ከወጣ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሕጉን በመቃውም ጸረ ወያኔ ቤት የመቀመጥ ኣድማ በጎንደር መጀመሩ ታውቋል። ኣስቸኳይ ጊዜ ኣዋጅ የተባለው ማንኛአንም ተቃውሞ የሚከለክል ቢሆንም የጎንደር ሕዝብ ግን እምቢ ለነጻነቴ እምቢ ለመብቴ ሲል ጸረ ወያኔ ቤት የመቀመጥ ኣድማ በማድረግ የጎንደር ከተማ ጭር ኣድርጓታል።
ሕዝቡ ድርጅቶቹን በመዝጋት ቤቱ በመቀመጥ የጀመረው ኣድማ ኣሁን ለሶስተኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል። የኣሁኑ ኣድማ የንግድ ድርጅቶችን እና ኣጠቃላይ የኣገልግሎት ሜስጫዎችን ጨምሮ ትራንስፖርት በሙሉ በኣድማው ይሳተፋሉ። በዚህ ኣድማም የመንግስት ሰራተኞች ምንም ኣይነት ኣማራጭ ስለማያገኙ ቤታቸው በመቀመጥ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ታውቋል። የቤት ውስጥ የመቀመጥ ኣድማው ለሳምንት የታቀደ ሲሆን በባህር ዳርም ባለፈው ሳምንት ኣድማው ተግባራዊ እንደነበር ይታወሳል።
ዝርዝሩን ፡ http://mereja.com/network/post/200/a-week-after-ethiopia-s-state-of-emergency-gonder-starts-a-gene
Gonder

No comments:

Post a Comment