Monday, October 10, 2016

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወደከፋ ጦርነት የሚወስደን ነው – #ግርማ_ካሳ



የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚታወጀው በሶስት ምክንያቶች ብቻ ነው። አንደኛው የዉጭ ወራሪ ሃይል ሲመጣ ነው። አሁን ኢትዮጵያ በማንም አልተወረረችም። ሁለተኛ የተፈጥሮ አደጋ ወይንም ጅምላ ጨራሽ ተላላፊ በሽታ ሲመጣ። እግዚአብሄር የተመሰገ ይሁን ይሄም ብዙ በሌሎች አንዳንድ አገሮች እንደሆነ በኛ አገር ብዙም ታየ ማለት አይቻልም።
አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የአስቸኳይ አዋጅ ትላንት አውጇል። (ሕወሃት አውጆ ሃይለማሪያም እንዲያነብ ተደርጓል) ከላይ በተጠቀሱት ሁለት ምክንያቶች ሊሆን አይችልም። በሶስተኛው ምክንያት እንጅ።
በሕገ መንግስቱ የተጠቀሰው ሶስተኛው ምክንያት ህግና ስርዓት ፈርሶ የሕገ መንግስታዊ ስርዓቱና አደጋ ላይ ከሆነ እና በመደበኛ የሰላም አስጠባቂ ሃይላት ነገሮች መቆጣጠር ካቃጣቸው የሚል ነው። እዚህ ላይ ልብ እንበል፣ የሕግ መንግስቱ ስርዓት አደጋ ላይ መዉደቁ ብቻ በቂ ምክንያት አይደለም። ግን የሕግ አስጠባቂ ሃይላት ሁኔታውን መቆጣጠር ካልቻሉ የሚል አለበት።
ብዙ የአገዛዙ ደጋፊዎች ነገሮች አታካብዱ ፣ ይሄን ያህል ብዙ ችግር የለም ሲሉን ነበር። ሆኖም ይኸው ድርጅታቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አዉጇል። ነገሮች መቆጣጠር እንዳልችሉ፣ አገር አደጋ ላይ እንዳለች አምነዋል።
አዋጁን ተከትሎ ጠቅላይ አቅቤ ህጉ የሚከተሉትን ብለአል፡
መንግስት የተጠረጠረ “ማንኛውንም ሰው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መያዝ ይችላል። ቤቱንም ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መበርበር ይችላል”
“ሁከት እና ብጥብጥ የሚያነሳሱ ድብቅ ቅስቀሳዎች ማድረግ ክልክል ነው”
“በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመራው ኮማንድ ፖስት “ማንኛውንም ዓይነት የመገናኛ ዘዴ የመዝጋት ስልጣን አለው” ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጌታቸው አምባዬ።
ሰዎቹ አንድ የዘነጉት ነገር ቢኖር ግን ይሄ አዋጅ መታወጁ የሚለዉጠው ነገር አለመኖሩ ነው። የኢትዮጵያ ችግር የሚፈታው የሕዝቡን ጥያቄ በማክበርና በመስማት ነው። በዉይይት፣ በብሄራዊ መግባባት ነው። አዋጅ እያወጡ ህዝቡን ማስፈራራትና መለፈፍ፣ በሕዝቡ ላይ መዛት የሚለዉጠው ነገር አይኖርም። የበለጠ ቀዉሱን ያባብሰዋል እንጅ።
ሌላው አላሉትም እንጅ አሁን በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እናደርገዋለን ያሉት ላለፉት በርካታ አመታት ሲያደረጉት ነበር። እስከ አሁን ማረጋጋት ሳይችሉ አሁን ምን ተዓምር ተገኝቶ ማነጋገር የሚችሉት ? ከሰራዊቱ መሃከል ብዙዎች ጥለው እየሄዱ ነው። ሰራዊቱ እየተከፋፈለ ነው። የትኛው ሃይል ነው ድፍን ጎጃማ፣ ድፍን ጎንደርና አብዛኛውን ኦሮሚያስ ሊያረጋጋ የሚችለው ?
ለምን ይህ አዋጅ ነገሮችን በክፉ አቅጣጫ እንደሚያባብሰው አንድ ተጨማሪ ምክንያት አልቅርብ። ከዚህ በኋላ ሰው ሰለፎችና ተቃዉሞዎች በአደባባይ አያደርግም። ሕዝቡ በአደባባይ ብሶት ቢገልጽ ይሻል ነበር። አሁን ግን ነገሮችን በአደባባይ ሳይሆን በሕቡእ ወደ ማድረግ ነው የሚኬደው። አሁን ካየነው በባሰ ሁኔታ ነው ከፍተኛ ጥፋትና ዉድመት የሚደርሰው። ህዝብን በአዋጅ አፍኖ መግዛት በችራሽ አይቻልም።
የሃይማኖት አባቶች፣ አበው፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን….ሁሉም በፊናው አገዛዙ ችግሮችን በዉይይት እንዲፈታ፣ ለብሄራዊ መግባባት እንዲዘጋጅ ሲጠይቁና ሲማጸኑ ነበር። ከነርሱ መካከል አንዱ የሆኑኢት አቶ ገዱ አንዳራግቸው ራሳቸው ህዝብን አክብሮ፣ ከሕዝብ ጋር በመወያየት እንጅ በፖሊስ፣ በደህንነት፣ በመከላከያ ሰላም ማምጣት አይቻልም ነው ያሉት። ሆኖም ግን ህወሃቶች ለመስማት ፍቃደኛ አልሆኑም። በሕዝቡ ላይ በድጋሚ ጦርነት አውጀዋል።
በሕገ መንግስቱ ላይ ያለው ስለ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚደነግገው ሕግ ከዚህ በታች ቀርቧል፡
Article 93 Declaration of State of Emergency
(1) (a) The Council of Ministers of the Federal Government shall have the power to decree a state of emergency, should an external invasion, a break down of law and order which endangers the Constitutional order and which cannot be controlled by the regular law enforcement agencies and personnel, a natural disaster, or an epidemic occur.
(b) Sate executives can decree a State-Wide state of emergency should a natural disaster or an epidemic occur. Particulars shall be determined in State Constitutions to be promulgated in conformity with this Constitution.
(2) A state of emergency declared in accordance with sub-article 1 (a) of this article:
(a) If declared when the House of Peoples’ Representatives is in session, the decree shall be submitted to the House within forty-eight hours of its declaration. The decree, if not approved by a two-thirds majority vote of members of the House of Peoples’ Representatives, shall be repealed forthwith.
(b) Subject to the required vote of approval set out in (a) of this sub-article, the decree declaring a state of emergency when the House of Peoples’ Representatives is not in session shall be submitted to it within fifteen days of its adoption.
(3) A state of emergency decreed by the Council of Ministers, if approved by the House of Peoples’ Representatives, can remain in effect up to six months. The House of Peoples’ Representatives may, by a two-thirds majority vote, allow the state of emergency proclamation to be renewed every four months successively.
(4) (a) When a state of emergency is declared, the Council of Ministers shall, in accordance with regulations it issues, have all necessary power to protect the country’s peace and sovereignty, and to maintain public security, law and order.
(b) The Council of Ministers shall have the power to suspend such political and democratic rights contained in this Constitution to the extent necessary to avert the conditions that required the declaration of a state of emergency.
(c) In the exercise of its emergency powers the Council of Ministers can not, however, suspend or limit the rights provided for in Articles 1, 18, 25, and sub-articles 1 and 2 of Article 39 of this Constitution.
(5) The House of Peoples’ Representatives, while declaring a state of emergency, shall simultaneously establish a State of Emergency Inquiry Board, comprising of seven persons to be chosen and assigned by the House from among its members and from legal experts.
(6) The State of Emergency Inquiry Board shall have the following powers and responsibilities:
(a) To make public within one month the names of all individuals arrested on account of the state of emergency together with the reasons for their arrest.
(b) To inspect and follow up that no measure taken during the state of emergency is inhumane.
(c) To recommend to the Prime Minister or to the Council of Ministers corrective measures if it finds and case of inhumane treatment.
(d) To ensure the prosecution of perpetrators of inhumane acts.
(e) To submit its views to the House of Peoples’ Representatives on a request to extend the duration of the state of emergency

No comments:

Post a Comment