Thursday, October 6, 2016

ኢትዮጵያዊያን በቢሾፍቱ ለተጨፈጨፉ ወገኖች የሻማ ማብራት ዝግጅት አደረጉ




img_5255img_5255
ቁጥራቸው በሽዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በትናንትናው ምሽት ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ውስጥ በመሰባሰብ ዋይት ሃውስ ቤተመንግስት ፊት ለፊት ተገኝተው የእሬቻን በዓል ቢሾፍቱ ከተማ ውስጥ በማክበር ላይ በነበሩ የኦሮሞ ብሔረሰብ አባላትና ሌሎችም ታዳሚዎች ላይ በአጋዚ ጦር ጥይት የረገፉትን ወገኖች በማሰብ የጸሎትና የሻማ ማብራት ዝግጅት አድርገዋል። በዝግጅቱ ላይ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ ከኢትዮጵያ ሙስሊም ሐይማኖት፣ ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን የተወከሉ አባቶች ልብ የሚነካ፣ የሚያበረታታና የሚያጽናና መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
በዚህ ዝግጅት ላይ የኢትዮጵያዊያን አንድነት ጎልቶና ደምቆ የታየበት ከመሆኑም በላይ የህዝቡ ጠላት ወያኔ ብቻ መሆኑ ከተለያዩ የማህበረሰብ ተወካዮች በተላለፈው መልክት ተገልጿል። በተለይም የኦሮሞና የአማራ ህዝብ ድርና ማግ መሆናቸውና እንደማይነጣጠሉ እንዲሁም አንዱ ከሌለ ሌላው እንደማይኖር የተረጋገጠበትና የታየበት መድረክ ነበር። (ስለዝግጅቱ የሚያሳዩ ተጨማሪ ፍቶግራፎች እንለቃለን

No comments:

Post a Comment