Friday, March 17, 2017

አምባጊዮርጊስ ላይ ጥቃት ማን ፈፀመ? – አስናቀው አበበ source ሳተናው

 28
ከቦታው በጥንቃቄ ጊዜ ወስደን እንዳጣራነው ጎንደር/ወገራ አውራጃ በአምባጊዮርጊስ ከተማ የፖሊስ ጣቢያ ላይ እሮብ እለት ድንገተኛ ተኩስ ከፍተው የነበሩት የአርበኞች ግንቦት ሰባት ተወርዋሪ ሃይል መሆኑን ለመረዳት ችለናል። ይህ ነው የሚባል ጉዳት መድረሱን ማረጋገጥ ባይቻልም ከሰሞኑ የጎንደር ሆስፒታል በተጎዱ ወታደሮች መጨናነቁን መዘገባችን ይታወቃል።
በሁኔታው የወያኔ ተላላኪ የአካባቢው ባለስልጣናት ክፉኛ መደናገጣቸው ታውቋል። እየተደናበረ ያለው ወያኔ የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ም/ኮሚሸነርን እና የመምሪያዉ ም/ሀላፊን በተመሳሳይ ወቅት ይዞ ማሰራቸውን መረጃወች ይጠቁማሉ።
አምባጊዮርጊስ ከጎንደር ወደ 40 ኪ.ሜ. ገደማ የምትርቅ ከተማ ስትሆን ወያኔ በቅርብ ጊዜ በጅምላ ህዝብ የፈጀባት ቦታ ናት። አካባቢውን መሰረት ያደረገው የከፋኝ ሃይል ተደጋጋሚ ጀብዱና ድል የፈፀመባት የእንቃሽ አካባቢ መገኛ ናት።
ድል የህዝብ ነው©!

No comments:

Post a Comment