Thursday, March 23, 2017

በመኪና አደጋ የ41 ሰዎች ሕይወት አለፈ source zhabesha

አቢሰሎም ፍሰሐ
ከደሴ ወደ ባሕር ዳር ሲጓዝ የነበረ ISUZU የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከ20 ሜትር በላይ ወደ ሆነ ገደል መንገድ ስቶ በመግባቱ ለ41 ሰዎች ሕይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል፡፡
መጋቢት 13 ቀን 2009 ዓ.ም ረፋድ ላይ አደጋው እንደደረሰ የነገሩን ምንጮች አውቶቡሱ ይዟቸው ከነበሩት 65 ሰዎች መካከል በሕይወት የተረፉት 24ቱ ብቻ ናቸው ተብሏል፡፡
ከአደጋው የተረፉት አብዛኛዎቹ ተጎጅዎች በከባድ ሁኔታ የተጎዱ ሲሆን በወልዲያ ሆስፒታል እርዳታ እየተደረገላቸው ቢሆንም ሕይወታቸው አስጊ ነው ተብሏል፡፡
የወልዲያና አካባቢው ሕዝብ ደም በመለገስና ተጎጂዎችን በሚችለው ሁሉ ቢረዳ መልካም እንደሆነም መረጃውን የሰጡን ሰዎች ተናግረዋል፡፡

No comments:

Post a Comment