Wednesday, March 8, 2017

እስከመቼ ሃይለማሪያም በነሳሞራ እየተናቀ ይኖራል ? #ግርማ_ካሳ


የአፍሪካ ኢንተሊጀንስ ጠቅሶ ዘሃበሻ የሚከትለዉን ዘግቧል። አፍሪአ ኢንተሊጄንስ የሚታመን ምንጭ ነው። ኢሕአዴእግ ስልጣን እንደያዘ ገና የአዲስ አበባ ቻርተር ሳይጸድቅ የኢትዮጵያ አወቃቀር ምን እንደምትመስል አፍሪካ ኢንተሊጀንስ ነበር ያወጣው። ብዙም አልቆይም በቻርተሩ ጸደቀ።
 
ይሄ ሜዲያ ብዙዎቻችን ለአንባቢያን ለምሳየት ስንሞክር የነበረውን ነገር ነው በግልጽ ያስቀመጠው። በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለው ሁለት መንግስት ነው። አንደኛው በሃይለማሪያም ደሳለኝ የሚመራው ሲሆን፣ ሁለተኛ በጥቂት ህወሃቶች የሚመራውው፣ ደህንነቱን እና ሰርራዊቱን የሚቆጣጠረውው፣ እነ ኃይለማሪያም የማይታዘዝ ብቻ ሳይሆንን የሚንቅንና መመሪያዎች በጎን እየላከ ዉሳኔያቸውን የሚሰርዝ አካል ነው።
 
እና ሃይለማሪያም የአገር ችግር በድርድር እንዲፈታ ያለው ፖለቲካ እንዲለዝብ የሕዝብ ጥያቄ እንዲፌታ ይፈልግጋሉ። ይህ አሁኡንን ይደረጋል የተባለውንን ድርድር ያመቻቹት እነርሱ ናቸው። ግን የሕወሃቱ ሁለተኛው መንግስት ድርድር የሚባል ነገር አይፈለግም። እያሰረ፣ እየገድደለ፣ እያፈናቀል በጥጋብና በ እርብሪት መግዛት ነው የሚፈለገው። ለዚህ ነው ተቃዋምሚዎች ከድርድሩ እዲወጡ አመራሮችን እያሰረ ያለውና የሚከሰው።
 
ህወሃት ለ547 መቀመጫ 38 ብቻ ነው ድምጽ ያለው። በኢሕአዴግ ዉስጥ ደግሞ አንድ አራተኛ ብቻ ነው መቀመጫ ያለው። ታዲያ እንዴት በዚህ መልክ እየተዋረዱና መሳቂያ እየሆኑ ዝም ብለው ያያሉ ? እስከ መቼ ነው እነዚህ የታሪክ አተላዎችን ይታገሳሉ ? እስከመቼ ነው፣ ግድ የለም ለሌላው አይቁሞ ለራሳቸውና ለክብራቸው እንኳን የማይቆሙት ? እስከ መቼ እነ ሶሞራ እንደ ዉሻ እያዩዋቸው ዝም የሚሉት ?
 
አንድ ጊዜ በብአዴን ጉባዬ አባላቱ “እነርሱ ባልፎቅ ሲሆኑ እኛ ሎተሪ ሻጮች ነው የሆንነው” እያሉ ሲያማረርሩ ነበር። እስከመቼ ነው የሚያማርሩት ?

No comments:

Post a Comment