Saturday, March 11, 2017

ብአዴን የህውሃት የትሮይ ፈረስ – (በቬሮኒካ መላኩ )

በቬሮኒካ መላኩ
……………………
ሰሞኑን የትግሬ ብሄርተኞች ” ብአዴን እንደዚህ አለ እንደዚያ አለ ” እየተባለ ሴቱ በየወፍጮ ቤቱ ወንዱም በየቀንዶ ቤቱ እያወራ እየፈነጠዘ ነው ።
ለአማራ ህዝብ ብአዴን የሚባል ድርጅት ባእዱ ነዉ ። የአማራ ህዝብ ብአዴን አማረኛ ተናጋሪ ህወሀት ናቸሁ ተላላኪ ናቸሁ ብሎ ፊቱን ካዞረባቸው ብዙ አመታት ተቆጠረ ።
ብአዴን ሲጠሩት አቤት ሲልኩት ወዴት የሚል የሆዳሞች ስብስብ የህዋት ተላላኪ ድርጅት ነው ተብሎ አቋም የተያዘበት ድርጅት እንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው ። መቸም ትግሬዎች በራሳችሁ አምሳል ጠፍጥፋችሁ የሰራችኋቸውነን ተላላኪዎቻችሁን እያወቃችሁ ብአዴን እንዲህ አለ እያላችሁ ጮቤ ምትረግጡት እና ህዝቡን ለመሸወድ የምትሞክሩት ነገር አስገራሚም አስቂኝም ነው።
እንደት ትግሬ የራሱን ድምፅ እንደገደል ማሚቶ ኤኮ እያደረገ መልሶ በሚዲያው መስማቱ እንደት ሊያስፈነጥዘው ቻለ? ይሄ የሰዎቹን ንቃተ ህሊና የት ደረጃ እንደደረሰ አመላካች ስለሆነ አይገርምም ።

“ብአዴን ማነው ? ” የሚል ጥያቄ በማንሳት አንባቢን ማዛግ የሚያስፈልግ አይመስለኝም ። ነገር ግን አንዳንድ ጥያቄዎችን ማንሳት ጥሩ ይመስለኛል ።
ለመሆኑ ግማሽ ትግሬው እና የአማራን ህዝብ በፀያፍ ስድቡ የዘለፈው አለምነው መኮንን እንዴት ለአማራ ሊያስብ ይችላል?
የትግሬ ተወላጁ ካሳ ተ/ብርሀን እንዴት ለአማራ መሬት ሊጨነቅ ይችላል? ኤርትራዊው በረከት ስሞን እንዴት የሚጠላውን አማራ ሊያስብለት ይችላል?
የእድሜውን ከግማሽ በላይ ሀረር እና ትግራይ ውስጥ ሲርመጠመጥ ያሳለፈው እና ትግሪኛ ተናጋሪው አዲሱ ለገሰ በምንም ተአምር ለአማራ ሊቆረቆር ይችላል?
ትግሬው ህላዊ ዮሴፍ እንደት ለአማራ ሊጨነቅ ይችላል?
የትግሬን የአምባሻ ዱቄት ተሸከም ቢሉት የማያቅማማው ሎሌ ደመቀ መኮንን እንደት አማራን ሊወክል ይችላል?

የአማራ ህዝብ ብአዴን ወልቃይት እና ሌሎች በማን አለብኝነት የተወሰዱ የአማራ መሬቶች ማስመለስ እንደማይችል አሳምሮ ያውቀዋል። ማስመለስ ቢችልማ መጀመሪያውን እንዴት አሳልፎ ይሰጥ ነበር?

አዲሱ ለገሰ የተባለው የህውሃት ሎሌ በወልቃይት ጉዳይ ላይ ባደረገው ኢንተርቪው ሳያስበው አንድ እውነት አምልጦታል ። Smart ብትሆኑ ኖሮ የሰውየው ንግግር ሊያሳዝናችሁ እንጅ ሊያስፈነጥዛችሁ ባልተገባ ነበር ። ሎሌ አዲሱ ለገሰ ምን አለ ? ” የወልቃይት ጉዳይን የብአዴን ጥያቄ አይደለም አለ ።” እውነቱን ነው ። ከመነሻውም የወልቃይት ጥያቄ የ 40 ሚሊዮን የአማራ ወልቃይት ህዝብ ጥያቄ እንጂ ብአዴን የተባለው ድርጅት ጥያቄ አልነበረም ። የአማራ ህዝብ እኮ እየታጋለ ያለው ህውሃትን ብቻ ሳይሆን አማርኛ ተናጋሪ የህውሃት ክንፍ የሆነውን ብአዴንንም ጭምር ነው ።

ባለፉት 25 አመታት የወልቃይት ህዝብ እያለ ያለው ጨዋታው በየብሄርህ ከሆነ እኛን ለምን ከብሄራችን ትነጥሉናላችሁ ነው። ይሄ ደግሞ መብታቸው ነው። ቋንቋቸውን ባህላቸውን ለመጠበቅ ወደ ክልላቸው መመለስ አለባቸው።
የወያኔ አስተዳደር ስምምነት ይሄው ስለሆነ የወልቃይት ህዝብ ማንነቱን ከመሬቱ ጋር ኣያይዞ እየጠየቀ ስለሆነ መመለስ አለበት።
ዘረኛው ወያኔ አልተረዳውም እንጂ የትግራይ ህዝብ ድንበሩ ተከዜም ወልቃይትም አልነበረመም። ድንበሩ ከኢሉባቦር እስከ ኦጋዴን እስከ ሞያሌ እስከ ባድመ ነው። ነገር ግን ወያኔ የዘር ጨዋታውን ፊሽካ በማስነፋት ስለጀመረው በስግብግብነት እንደ አሳማ ከጎንደር እና ከወሎ የዋጠውን መሬት ማንቁርቱን ተይዞ መትፋቱ አይቀርም ። በመጀመሪያ በዚህ ጉዳይ ላይ ወደ ስምምነት መምጣት አለባት። ሁላችን ወሰናችን ይሄ መሆኑን መስማማት አለብን። አለበለዚያ ወያኔ በአንድ በኩል የቋንቋ መንግስት አምሮት በሌላ በኩል ደግሞ ትንሽ ለም መሬት ሲያይ ከቤንሻንጉልም ከአማራም ቦጨቅ ማድረግ እያማረው ኣይሆንም። ትክክልም አይደለም።

በብዙ መልኩ ስንገመግመው የትግሬ ወያኔ ባህሪ የክረምት ጅብ አይነት ነው ።
በአንድ በኩል በትግሬ ውስጥ ያሉ ሃብቶችን የኢፈርትንም ጭምር ፣ተፈጥሮ ሃብቱንም የኛ የትግራይ ህዝብ ብቻ ነው ይልና በአንድ እጁ ይዞ ይታያል። ንብረትነቱ የኛ ብቻ ነው ይላል። በሌላ በኩል ደግሞ የአባይን ወንዝ ፣ የጣናን ተፋሰስ እና ለም መሬት ፣ የጉጂዎችን ወርቅ ፣የጅማውን ቡና የሁላችን በማለት አብሮ ይበላል። የሌላውን በአንድ ገበታ አርገን እንብላ ይልህና የራሱን ብቻውን ይውጣል ። የራሱን በጁ ይዞ እያደለበ የሌላውን ያጫርሳል። ይሄ ጥሩ አይደለም። ለሃቹ ለሃገራችን ኣይበጅም። ብንገነጠልም እንኳን ለጉርብትና አይሆነንም። ታሪካዊ እሴቱም ጥሩ ኣይደለም።

የአማራ ህዝብም ሆነ የሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ወራቶች ጥያቄውን በግልፅ አስቀምጧል፡፡ ይህም ከተከዜ ማዶ ያለን ቦታ ለጎንደር መመለስን ጨምሮ የህወሃትን የበላይነት፣ ጣልቃ ገብነትና ዝርፊያ ጨርሶ መቆምንም ይጨምራል፡፡ ይህን በመናቅ ግን ጥያቄውን ሳይመልሱ መቅረት በጉልበት መሞከር ሁኔታውን የሚያብስ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠር ሀይል እንኳ ቢኖራቸሁ ህዝብን ማሸነፍ እንኳን በእውን በህልማችሁ እንኳን ሊሳካላቸውሁ የማይችል ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ዘመን እንዳለፉት 25 አመታት አይደለም። አማራ አሁን ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ሁሉንም ያውቃል ። ወቅቱ እጅግ የተለየና ለህዝብ ምቹ የሆነ ሲሆን የፈለገውን ያህል አጋዚ ያሰማራ በመጨረሻ ላይ ግን ዘመኑ የወያኔን ፍፃሜ ማብሰሪያ ዘመን የሚሆን ነው፡፡

ወያኔ እና መሰሎቹ አንድ መገንዘብ ያለባቸው ነገር አለ ። ጥያቄዎች በሰላም መንገድ ካልተፈቱ ስንፋጅና ስንጎዳዳ ኖረን ወያኔ በጉልበት እንደወሰደው ሁሉ ከነወለዱ በጉልበት ይመለሳል ።

ማጠቃለያ
የአማራ ህዝብ ምን ማድረግ አለበት?

1~ የአማራ ህዝብ በታሪክ ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ የተጋረጠበትን ችግር ለመፍታት እርስ በእርስ መረጃ እየተለዋወጡ በወንድማማችነት መንፈስ መደራጀት ያስፈልጋል ።አማራ በማንም እንዳይጠቃ እርስ በርስ እየተጠባበቁና እየተከላከሉ ወንድማማችነትን ማዳበር ።

2~ የገበሬውን ነገር አደራ፡፡ ከማንኛውም ጊዜ በበለጠ ሁኔታ በመረጃ እያጠነከሩ በስራው መበርታት ይኖርብታል፡፡
ዛሬ ካልተሰራና ነገ ካልተመረተ ከነገ ወዲያ ችግር ሲፈጠር ህወሃት በእርዳታ መልክ የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ጥገኛ ለማድረግ እንዳትችል ዛሬውኑ ሁሉም በእጃችን ያለና የሚቻል ስለሆነ ሁሉም በያለበት በስራ መበርታት አለበት፡፡ በስራ የሚበረታና ራሱን የሚችል ህዝብ ምን ጊዜም አሸናፊ መሆኑ ታወቆ አርሶ አደሩ በስራው እንድበረታ መርዳት ።

3 ~ሌላው ቁልፍ ነጥብ የአማራ ቲቪ እንደ OMN መቁዋቋም አለበት።
አባቶቻችን ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ያሉት ትልቅ ስትራቴጂ ነው ።”ህዝቤ እውቀት በማጣት ጠፋ” ይላል ነብዩ ሆሴ።ያማራ ህዝብ የጠፋው እውቀት፣መረጃ፣ በማጣቱ ነው።መረጃ የደምስር ነው።መረጃ የሌለው ማህበረሰብና ከባህር እንደ ወጣ አሳ መጨረሻቸው “ሞት” ነው ። አማራ ለህዝቡ መረጃ የሚሰጠው የራሱ የሆነ ሚዲያ እንደሚያስፈልግ ታውቆ ለተግባራዊነቱ ጥረት ማድረግ ።
ልብ ያለው ልብ ይበል!

No comments:

Post a Comment