Thursday, March 16, 2017

ውክልናቸውን በግላቸው ያፀደቁ የብሄር ፖለቲከኞች – ዳንኤል ሃይሌ

ሁሉም ሊባል በሚችል መልኩ በብሄር ተደራጂተናል የሚሉት ድርጅቶች ገና ከስልጣን ደጃፍ ሳይደርሱ ድፍረታቸው እና ንቀታቸው ማንነታቸውን ፍንትው አርጎ እያሳየነው።
ዛሬ ማውራት የምፈልገው እኔ ስለወጣሁበት አማራ ነው የሌሎቹን በይደር እንያዘው። የአማራን ህዝብ መደራጀት ከቶ ማንም የሚቃወም ይኖራል ብዬ አላስብም ምክንያቱም ስለዲሞክራሲ የምናልም ከሆነ ሰዎች በምንም ይሁን በምንም የመደራጀት መብታቸውን ልናከብር ይገባል እንዲሁም እነሱም የሌላውን የማክበር ግዴታ አለባቸው ብለን እናምናለን። ፍትህ እና ዲሞክራሲ በጠፍባት ሀገር ዜጎች በማንኛውም መልኩ የመደራጀትና ሀሳባቸውን በነፃነት ገልፀው መኖር በማይቻልበት ሁኔታ ውስጥ ሆነን እኮ በምን ስሌት ነው እኔ የዚህ ቢሄር ተወካይ ነኝ ወይም በግልፅ ቋንቋ “እኔ የአማራ ብሄር ተወካይ ነኝ እደራደርለታለሁ” የምንለው?
አዎ እውነት ነው የአማራ ህዝብ የሞት አዋጅ የታወጀበት ባልሰራው በደል ባለፋት 25 ዕመታት የዘር ማጥፍት ሲፈፅምበት ቆይቷል። ለዛም ነው ተደራጅቶ እራሱን መታደግ አለበት የምንለው ሆኖም ባሳለፍነው አንድ አመት ውስጥ የተፈለፈሉት ታላቁን የአማራ ህዝብ እንወክላለን የሚሉን ድርጅቶች ህዝባችን ብለው የተነሱለትን ህዝብ ስነልቦና እንኳን ማንበብ የማይችሉ ከራሳቸውም የተጣሉ ሆነው አግኝተናቸዋል። አብዛኛዎቹ የተፈበረኩት በወያኔ የውጭ የፓለቲካ እስትራቴጂክ መዋቅር ውስጥ መሆኑን በግዜ ተጉዘን መረዳት ችለናል ፤ እደውም አንዳንዴም “አግ7 ወደስልጣን ከሚመጣ ከብአዴን ጋር ተስማምተን እንሰራለን” ትዕግስታቸው ሲያልቅ ብለው የሚናገሩም አሉ። ምን እሚሉት ፈሊጥ ነው ከገዳይ ጋር እሰራለሁ ማለት?
የህዝብ ውክልና ምንድነው?
ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት የፓለትካ አጣብቂኝ ውስጥ ሆነን ስለህዝብ ውክልና ማውራት ማለት አላዋቂነት ነው ተብሎ ሊታለፍ አይገባም በማንአለብኝነት የተሞላ የስልጣን ጥማት የነገሰበት አስተሳሰብ ነው።
አምባገነኑን የወያኔ አፓርታይድ ስርአት ሳንጥል እና በነፃነት አገራችን የፖለቲካ ሜዳ ላይ ፖሊሲያችንን አቅርበን ቆሜልሀለው የምንልውን ህዝብ ይሁኝታ ሳናገኝ አይ እኔ የተወለድኩት ጎጃም፣ጎንደር፣ወሎ…ወዘተ ስለሆነ እኔነኝ ተወካይህ በማንነትህ ላይ እደራደራለሁ ማለት የጠገበውን ወያኔን አዉርዶ የራበውን ምትኩን ማንገስ ነው የሚሆነው። ለዛም ነው ምንም እንኳን የአስተሳሰብ ልዩነት ቢኖረንም አምባገነኑን የወያኔን ስርአት በጋራ ጥለን በነፃነት ለተጨቆነው ህዝብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ሀሳባችንን አቅርበን ውክልናን የምንረከበው። በተቃራኒው ግን አሜሪካ አገር ቁጭ ብሎ አገር ቤት ወያኔ ሲወድቅ ስልጣን እንደሚያገኝ እርግጠኛ መሆን የሚፈልጉ ቆሜለታለው የሚሉት ወገን ሞት ምንም የማይመስላቸው ሆነው አግኝተናቸዋል።
አግ7 እንኳን እግር በሌላቸው የወያኔ ድርጅቾች በወያኔም አይፈርስ! አግ7 ውስጥ ምንያህል አማሮች እንዳለን እናንተም ታውቃላችሁ አሁን እናንተም ደረታችሁን ነፍታችሁ እየታገልን ነው የምትሉት ትግል ወልዶ ያሳደገው አሁን ላለንበት ያንገዛም እቢተኝነ ማዕበል ያበቃው አግ7 ነው! እኛም አማራ ነን የህዝባችን ሞት የሚገለን።
አልመሸም ገና ብዙ መንገድ ይቀረናል አብረን ብንጟዝ ቶሎ ያሰብንበት እንድርሳለን የወገኑ ስቃይ የሚያመው ሁሉ ልዩነቱን አቻችሎ ለአንድ ጠላት ወያኔ በጋራ ይነሳ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ዳንኤል ሃይሌ

No comments:

Post a Comment