Friday, March 10, 2017

ዶክተር መረራ የዋስ መብታቸው እንደተከለከለ ሲገለጽላቸው በፍርድ ቤት ይህን ተናገሩ

ዶክተር መረራ የዋስ መብታቸው እንደተከለከለ ሲገለጽላቸው በፍርድ ቤት ይህን ተናገሩ:-
“ 1) ከእነጄኔራል መንግስቱ ንዋይና ጄኔራል ታደሰ ብሩ ዘመን ጀምሮ ከአንድ ትውልድ በላይ ገዳዮችና ሟቾች አሳሪዎችና ታሳሪዎች በበዛበት የሀገራችን የፖለቲካ ድራማ ውስጥ በመቆየት አንድ አንድ ከሆዱ በላይ ለሀገሩ የሚያስብ ምሁር ማድረግ እንዳለበት ሁሉ ከአርባ አምስት አመታት በላይ ለሀገሬ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ በታማኝነት መታገሌ እየታወቀ ወደ ጎን መገፋቱ፡-
2) ለሁላችንም የምትሆንና በእኩልነት የምታስተናግደን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንድትፈጠርና ነፃ የፍትህ ሥርዓት በሀገራችን እንዲሰፍን ላለፉት ሃያ አምስት አመታት በመታገሌ መከሰሴ አንሶ የአገሪቱ ፓርላማ አባል የነበርኩ ሰው ለተራ ወንጀለኛ የሚፈቀድ የዋስ መብት በመከልከሌ የተሰማኝ ጥልቅ ሀዘን ለራሴ ብቻ ሳይሆን እኛም ሆን ልጆቻችን በሰላም ይኖሩበታል ለምንለው መከረኛ ሀገራችንና አላልፍለት ብሎ ስታመስ ለሚኖር መከረኛ ሕዝባችን ጭምር መሆኑን እንዲታወቅልኝ ነው፡፡







No comments:

Post a Comment