Thursday, March 16, 2017

ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ከተከዜ በታች ያለ ኢትዮጵያዊ ያላለቀሰበት ጊዜ የለም፤ በአንጻሩ ከተከዜ በላይ ያሉ ዜጎች ዘመናቸው ሁሉ የፍስሃ ሆነ source zhebesha


ከሙሉቀን ተስፋው
ለቀስተኛው፤ ከተከዜ በታች ያለ ሕዝብ:
ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ከተከዜ በታች ያለ ኢትዮጵያዊ ያላለቀሰበት ጊዜ የለም፤ በአንጻሩ ከተከዜ በላይ ያሉ ዜጎች ዘመናቸው ሁሉ የፍስሃ ሆነ፡፡
እስኪ ትንሾቹን እንይ፤
 ከ1983-86 ዓ.ም በሐረርጌ እስከ 20 ሺህ የሚደርስ ዐማራ በአንድ ዓመት ሲታረድ፣ አጥንታቸው ወደ ወንዝ ሲወረወር፣ አብያተ ክርስቲያናት ሲወድሙ ከተከዜ በላይ ዳንኪራ ይረገጥ ነበር፡፡ በምስራቅ አርሲ የአምስት ወረዳ ዐማራ ቤትና ንብረት ተቃጥሎ ከነነፍሳቸው ወደ ገደል ሲጣሉ፤ በዘንጋዳ ጉድጓድ በጅምላ ሲቀበሩ እየየ ብለን አልቀሰናል፡፡ ወላድ እናቶች ልጃቸው በሳንጃ ከሆዳቸው ላይ የወጣበት ጊዜ በዚሁ በወያኔ ዘመን ነው፡፡ የማይሞላ ገደል ውስጥ የተጨመሩት ዐማሮች፣ ዐይናቸው ተጨፍኖ ወደ ገደል የተወረወሩት መነኮሳትን ማናችንም አልረሳንም፡፡ የመተከልና የወለጋ ጫካዎች በዐማራ አስከሬኖች ሲሞሉ የገዥው ቡድን ዘመዶች አስረሽ ምቺው እያሉ ነበር፡፡
 ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ የወልቃይት ዐማራ እናቶች ስለልጆቻቸውና ባሎቻቸው ያላዘኑበት ጊዜ የለም፤ በዚህ ጊዜ ከወንዝ ወዲያ ማዶ ያሉ ሰዎች ምን ይሉ እንደነበር ማንም መገመት አያቅተውም፡፡
 በ1998 ዓ.ም የኮፈሌና የቆሬ ወረዳ ዐማሮች ቤት ንብረታቸው በጨለማ ነዶ ከቀያቸው ሲፈናቀሉ ማንም ምንም ያለ የለም፡፡

 በ1992/3 ዓም በወለጋ የተለያዩ አካባቢዎች ከአንድ ሺህ በላይ ዐማሮች ቤት እየተዘጋባቸው ሲቃጠሉ ሕጻናት ከታዘሉበት እናታቸው ጀርባ እየተቀሙ ወደ ሚነደው እቶን ሲጣሉ መከላከያ ሠራዊት የሚያመልጡትን ዐማሮች በጀርባ ሆኖ ይጨርስ ነበር፡፡ 14000 (ዐሥራ አራት ሺህ) ዐማሮች ተፈናቅለው ቡሬ ላይ ሲቀመጡ የእለት ጉርስ እንኳ የሰጣቸው የመንግሥት አካል አልነበረም፡፡ ጃዊ ላይ ከ800 በላይ በወባ ሲያልቁ የወባ መድኃኒት ያቀረበ የጤና ባለሙያ እንኳ አልነበረም፡፡

 በ1990ዎቹ መጀመሪያ በወያኔና በሻቢያ ጦርነት ከ70 ሺህ በላይ ወንድሞቻችን በጦር በጦርነት ተማግደው አልቀዋል፡፡
 በ1999 ዓ.ም በጂማ ከነቤተክርሲያናቸው ዐማሮች ቤት ተዘግቶባቸው ሲነዱ ማንም ምንም አላለም፡፡
 በ2004-7 በቤንች ማጂ፣ በከማሽ፣ በመተከል፣ ከ32000 በላይ ዐማሮች ቤት ንብረታቸው ወድሞ ሲባረሩ ከተከዜ ማዶ ያሉ ሰዎች ደን ጨፍጫፊ ትምከተኞች ናቸው በማለት ነበር የተሳለቁት፡፡
 በ2007 ዓ.ም በመተከል በአንድ ቀን ሌሊት 160 በላይ ዐማሮች ታርደው ሲያደሩ የተባለ ነገር የለም፤
 በ2007 ዓ.ም በጎንደር ማረሚያ ቤት ከ70 በላይ ሰዎች በእሳት ሲቃጠሉ ምን ተባለ! ምንም፡፡
 በ2008/9 ከ300 በላይ ዐማሮች በጎንደርና በጎጃም በጥይት ተደፍተዋል፤ ገዥው ቡድን ምን አለ! ምንም፡፡
 በደብረዘይት በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተጠቅጥቀው ሲሞቱ እንኳ ከተከዜ ማዶ አሸንዳ ሲጨፈር ነበር፡፡
ምኑን ተናግረን ምኑን መተው እንችላለን? ከተከዜ በታች ያለን ዜጎች ኑሮ እንዲህ ነው፡፡ በእኛ ላይ ይህ ሁሉ ሲሆን ከተከዜ ማዶ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ምን መቅሰፍት ደርሶ ይሆን ብየ አሰብኩ፤ ምንም!
ደግነቱ ጊዜ ፈራጅ ነው፤ የሚያለቅሱ የሚስቁበት ጊዜ የሚስቁም የሚያለቅሱበት ዘመን ብዙ ሩቅ አይደለም፡፡

No comments:

Post a Comment