Tuesday, March 21, 2017

የአማራ ህዝብ የሚፈልገው ቅሪላ የሚጠልዝበት ሜዳ ሳይሆን ዳቦ የሚያስገኝለት ፋብሪካ ነው (ቬሮኒካ መላኩ) 


 






ለዚህ ፅሁፍ የተጠቀምኩት ርእስ ሞገደኛና ስፖርትን ጠል ሊያስመስልብኝ ይችላል። እውነታው እሱ አይደለም። እኔ ራሴ ስፖርት የምወድና ስፖርት ለአንድ ህዝብ የሚያበረክተውን አስተዋፅኦ የምገነዘብ ነኝ። ለዚህ ፅሁፌ መነሻ የሆነኝ ብአዴን ሰሞኑን በአማራ ክልል ውስጥ 12 የኳስ ሜዳ ለመገንባት ቃል እንደገባ በመሃበራዊ ሚዲያ ማንበቤ ነው ።
ህውሃት በከባድ በፋብሪካ ቁንጣን በምትሰቃየው ብይ በምታክለው ትግራይ ክልል ኢንዱስትሪዎችን ለመገንባት እቅድ ሲይዝ ። ኦህዴድ ” የኢኮኖሚ አቢዮት ” በሚል መሪ ቃል ለክልሉ ወጣት ስራ የሚያስገኝ የመአድን ማውጫ እና ሰርቪስ ሴክተሮችን ለመገንባት እቅድ ይዞ ሲተገብር ሎሌው ብአዴን የአማራ ወጣት በባዶ ሆዱ ስራ ፈትቶ ኳስ የሚጠልዝበት 12 ስታዴየም እሰራለሁ እያለ ነው።

የብአዴን ነገር ይገርመኛል። ብአዴን አንድ “ታዋቂ ” መዝሙር አለው። ” ያልተንበረከክነው! ” ይባላል  :) በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ታሪክ ውስጥ እንደ ብአዴን ተንበርካኪና ለአሽከርነት የተመቼ ድርጅት የትም አይገኝም ። ብአዴን መንበርከክ ብቻ ሳይሆን በትከሻው የህውሃትን የአንባሻ ዱቄት ተሸክሞ በእንብርክኩ የሚሄድ ድርጅት ነው።

የህውሃት የፖለቲካ ሃሊዮት በፖለቲካው ለዘመናት የበላይነትን ለመቆየት ኢኮኖሚውን እና ሚሊቴሪውን መቆጣጠር የሚል ነው። ይሄን ሃሊዮት ተግባራዊ ለማድረግ ባለፉት 25 አመታት ፍትሃዊ ያልሆነ የሃብት ማግበስበስ ላይ ሲሰማሩ ሌላውን ደግሞ በተለይም አማራውን በድህነት ይማቅቅ ዘንድ የሚችሉትን ሁሉ አድርገዋል እያደረጉም ነው ።

CSA (የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታስቲክ ኤጀንሲ) በቅርቡ ባወጣው መረጃ ትግራይ ላይ እስካሁን 300 ከፍተኛ ፣ከባድና መካከለኛና ኢንዱስትሪዎች (Medium & Large Scale Industries) የተገነቡ ሲሆን፤ በአማራ ክልል ግን 100 መካከለኛና ዝቅተኛ ኢንዱስትሪዎች (Medium & small scale Industries ) ብቻ ተከፍተዋል። ነገር ግን የአማራ ህዝብ የትግራይን ህዝብ ከ7 እጥፍ በላይ የሚበልጥ ከመሆኑም በተጨማሪ በጥሬ ዕቃ አቅርቦትም ሆነ ለኢንዱስትሪ ቦታ ምቹነት አማራ ክልል ከትግራይ እጅግ በላቀ መልኩ ተመራጭ የሚያደርጉ ብዙ ሁኔታዎች አሉት፡፡

ለምን እንዲህ ሆነ ተብለው ሲጠየቁ “በኦሮሚያ ክልል እኮ ከትግራይ የበለጠ 320 ኢንዱስትሪዎች ተሰርተዋል” ብለው ይነግሩናል::
ይገርማል! ብይ የምታክለውን ትግራይን ቋጥኝ ከሚያካክሉ ክልሎች አስበልጦና ነፋፍቶ በማሳየት ፍትሐዊ ባልሆነ መልኩ ያገሪቱን ሐብት ለክልላቸው ብቻ ያጋብሳሉ፡፡
አስቡት እስኪ የትግራይን 7 እጥፍ የሚበልጠው ኦሮሚያ 320 ስላለው፤ 7 እጥፍ ያነሰችው ትግራይ ላይ 300 መከፈቱ ፍትሐዊ ነው ብሎ ግግም ማለት ምን አይነት ደረቅነት እና ስግብግብነት ነው ?!

ባለፈው ጆሯችንን እስኪታመም እና አይናችን ሊጠፋ እስኪደርስ በየሚዲያው METEC (የብረታብረት ኮርፖሬሽን) ውቅሮ ላይ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ትራክተርን ሙሉ በሙሉ የሚፈበርክ ፋብሪካ ሲከፍት፤ ደብረ-ብርሐን ላይ ደግሞ መገጣጠሚያውን በመክፈት ሜቴክም በበኩሉ ፍትሀዊነት ሰብኮልናል፡፡ እናወዳድርስ ብንል አቅልጦ ማምረትንና የተመረተው መገጣጠም ምን አገናኘው? እንኳን ሊወዳደር የደብረ ብርሐኑ፤ ፋብሪካ ተብሎ ሊጠራ እንኳን አይገባውም!
ያው እንደተለመደው ከትግራይ ፊት concave mirror ደቅነን፤ ከአማራ ፊት ደግሞ convex mirror በማስቀመጥ በአብየታዊ ዲሞክራሲ ወልጋዳ ሚዛን ፍትሃዊነቱን እንድናደንቅ እንገደዳለህ፡፡

ህውሃት የሚመራው መንግስት አላማው አገሪቱንና ህዝቡን በኢኮኖሚ ለማሳደግ ቢሆን ኖሮ እንደ አማራ ክልል ለኢንደስትሪ አመች የሆነ ክልል የትም አይገኝም ነበር ። ለማንኛውም ከባድ ኢንደስትሪ የደም ስር የሚባለው የኤሌክትሪክ ሃይልን ብንመለከት ክልሉ እምቅ ሃይል ያለው ነው ። በአባይ ዋናው ወንዝ ላይ ብቻ 12 ግድቦችና በድምር ወደ 50,000 ሜጋ ዋት የሚደርስ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት አቅም ያለው ክልል ነው ።
ኢትዮጵያ 27 የመስኖና አነስተኛ የኤሌክትሪህ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በአባይ ገባር ወንዞች ላይ በመገንባት 2 ሚሊዩን ሄ/ር መሬት በመስኖ ማልማትና ተጨማሪ ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ በማመንጨት ይቻላል።

እውነታው ከላይ የተጠቀሰው ሆኖ እያለ በወያኔ ግልፅ የአፓርታይድ ፖሊሲና በአሽከሩ በብአዴን አስፈፃሚነት የአማራ ህዝብ ከድህነት እንድወጣ አይፈለግም። ህውሃት ከሮም እና ከሌሎች የጣሊያን ከተማ ላይብረሪዎች ፋሽስት ጣሊያን ትከተለው የነበረውን ፖሊሲ ከሸልፍ እያወረደች መተግበር ከቆየች 25 አመታት አለፋት ።

ወያኔ ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ ያደረገው ነገር ከሁሉም ክልል ተመርጠው ወደ ስልጣን እንድመጡ የሚደረጉት መመዘኛቸው በአማራው ላይ ከፍተኛ ጥላቻ ያላቸው በመሆናቸው እና ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር መኖር እና ያለመኖር ደንታ የማይሰጣቸው ሰዎች በመሆናቸው ብቻ ነው።
ብአዴንም ውስጥ ወደ ስልጣን እንድመጣ የሚፈለገው ” በአማራው ላይ ጥላቻ አለው ወይ? ” የሚል ፈተና ከተሰጠው በኋላ ያንን ፈተና ማለፍ ከቻለ በኋላ ነው። አሁን በተግባር እንደሚታየው አለምነው መኮንን የተባለ አሳማ ወደ ስልጣን እንድመጣ የሚደረገው ትግል ይሄን መመዘኛ በመቶ ፐርሰንት ስለሚያሟላ ነው ።

ከአሻንጉሊቱ እና በኢትዮጵያውያን ” ጠ/ሚ አቡሽ ” የሚል ቅፅል ስም በተሰጠው ሃይለማርያም ደሳለኝ ጀምሮ በሁሉም ክልል ያሉት በኦሮሞ በጋንቤላ በሱማሌ በትግራይ በቤንሻንጉል በደቡብ ክልል ያሉት የኢሃዴግ ኣመራሮች ምርጫ በኣማራ ላይ ባላቸው ጥላቻ ብቻ የተመረጡ ናቸው እስካሁን ድረስም ቢሆን ያ አሰራር ቀጥሏል በየትኛውም ክልል በኣማራውም ቢሆን ለአማራው ቀና ኣመለካከት ያለው ሰው ወደ ስልጣን በፍጹም ሊመጣ አይችልም።

አሁን የሚታየው የተቀነባበረና በፖሊሲ የታገዘ አማራውን አንገት የማስደፋት ፖሊሲ ለ40 አመታት በደንብ የተሰራበት ነው። አንድ ሁሉም ግንዛቤ ሊወስድበት የሚገባው የአማራ ህዝብ ይህንን በደሉን ለመርሳት/ ለመተው ቢቸገር እና ቀኑ ሲደርስ ሂሳብ ላወራርድ ቢል ሰው እንጂ መልዓክ አለመሆኑን ማወቅ አለባችሁ ።

No comments:

Post a Comment