ከሙሉቀን ተስፋው
በአቶ ማሙሸት አማረ የሚመራው የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ ወልደሃና መጋቢት 6 ቀን 2009 ዓም ከቤቱ በደኅንነት ታፍኖ ተወስዷል። በደብረ ብርሃን ከተማ ጠባሴ አካባባቢ የፍቅረ ሰላም ሆቴል ባለቤት የሆኑ ባለሀብት ባካባቢው በመገኘታቸው አብረው ታስረዋል። በደኅንነቶችና በፖሊስ አባላት ድብደባ እንደደረሰባቸው ታዛቢዎች የገለጹ ሲሆን ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸውን ዛሬ ለማወቅ ችለናል።
አቶ ለገሰ ወ/ሃና ከፓርቲ ሥራው በተጨማሪ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ በመሰንዘርና መረጃ በማድረስ የታወቀ ነው። በተለይ በሸዋ አካባቢ ያለውን የዐማራ ተጋድሎ ለሕዝብ ሳያሳልስ የሚያቀርብ ታታሪ ፖለቲከኛ ነው።
No comments:
Post a Comment