Tuesday, March 21, 2017

ለሚኒስትሮች፣ጀነራሎች፣የደህንነት ሹሞች፣ዲፕሎማቶች በሙስና ለቤት መሥሪያ የተሠጠ መሬትና ቤት ይመለስ source zhabesha


ክፀ/ት ፂዩን ዘ/ማርያም

‹‹ምላሳዊው መንግሥት በ12 ዓመታት ውስጥ ቤት ሠርቶ ያስረከበው ለ175,000 ሰዎች ብቻ ሲሆን ለተመዘገቡት 800 ሽህ ሰዎች ለማዳረስ 55 ዓመታት ይፈጅበታል!!!››

‹‹በአዲስ አበባ በ1997ዓ/ም እና በ2005ዓ/ም 800 ሽህ በተደረጉ ሁለት የጋራ መኖሪያ ቤት ምዝገባዎች ከ800 መቶ ሽህ በላይ የከተማ ነዋሪዎች ቤት ለማግኘት ተመዝግበው እድላቸውን እየተጠባበቁ ነው፡፡ የህወሓት የቤት ልማት ፕሮጀክት ፕሮግራም ከጀመረ 12 ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤት ሠርቶ ያስረከበው ለ175,000 ሰዎች ብቻ ነው፡፡ የቤት ግንባታ በዚህ ፍጥነት ከቀጠለ የተመዘገበውን ከ800 ሽህ የሚልቅ ነዋሪ የቤት ባለቤት ለማድረግ 55 ዓመታት ይፈጃል ማለት ነው፡፡›› የካቲት 22 ቀን አዲስ ዘመን ጋዜጣ
በከተሞች ከሚኖረው ህዝብ መካከል ከ50 እስከ 60 በመቶ ቤት አልባ መሆኑ፣ የቤት ፈላጊ ቁጥርም በዓመቱ በ150 ሽህ እየጨመረ መምጣቱና የህወሓት የጦር አበጋዞች መንግሥት ቤቶች የመገንባት ፍጥነት አዝጋሚ መሆን መጪውን ጊዜ አስፈሪ ድቅድቅ ጨለማ እንደሚያደርገው የዘርፉ ባለሙያዎች ጥናት ይመሠክራል፡፡
መንግሥት በቅንጅት ምርጫ በተሸነፈ ማግስት የአዲስ አበባ ህዝብን ለማማለልና ድጋፍ ለማግኘት በ1997 ዓ/ም የመኖሪያ ቤትን እጥረት ለመቅረፍ መንግስት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ይፋ አደረገ፡፡ በአዲስ አበባ  400 ሽህ ተመዝጋቢዎች ቤት ልማት ፕሮጀክት ፕሮግራም ከጀመረ 12 ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤት ሠርቶ ያስረከበው ለ140,000 ሰዎች ብቻ ነው፡፡
ኮንዶሚኒየም ቤቶች
የአዲስ አበባ ቤቶች ፕሮጀክት ቢሮ 335,000 ቤቶች በሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ማለትም በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት አቅዶል፡፡ ቢሮው 6.3 ቢሊዩን ብር በአመታ ለቤቶች ግንባታ በመመደብ ለተመዘገበው 860 ሽህ ህዝብ ቤት ማዳረስ አቅዶል፡፡ የቤቶች ኤጀንሲ 25 ቢሊዩን ብር ከኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ ገቢ ለመሰብስብ አቅዶል፡፡ በአጠቃላይ በሁለተኛው እድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ 750,000 ኮንዶሚኒየም ቤቶች በመላ ሃገሪቱ ለመሥራት ታቅዶል፡፡ በሁለተኛው እቅድ ዘመን 190,000 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ለነዋሪዎች ለማስተላለፍ ከዚህም ውስጥ ለልማት ተነሽዎች 50,000 ነዋሪዎች ድርሻ አላቸው፡፡
በ2005 ዓ/ም መኖሪያ ቤትን እጥረት ለመቅረፍ  መንግስት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ለሁለተኛ ግዜ ምዝገባ ይፋ አደረገ፡፡ በ10/90፣ በ20/80 እና በ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ተመዝጋቢዎች እንደየአቅማቸው ማለትም በ10/90፣የተመዘገበ የቤቱን ግንባታ ወጪ 10 በመቶ መቆጠብ ሲሆርበት 90 በመቶውን ከኢትዩጵያ ንግድ ባንክ ብድር ተመቻችቶለት በየወሩ በመክፈል የቤት ባለቤት ይሆናል፡፡ በ20/80 ተመዘገበ 20 በመቶ በመቆጠብና 80 በመቶውን ብድር ባንክ ይሸፍንለታል እንዲሁም  በ40/60 የተመዘገበ 40 በመቶ መቆጠብ ሲኖርበት 60 በመቶ ከባንክ ብድር በማግኘት የቤት ባለቤት ይሆናል፡፡ በቤታቸው ውስጥ እየኖሩ በየወሩ እንደ ቤት ኪራይ ለባንክ በመክፈል ሲጨርሱ የቤት ባለቤት ካርታ ይወስዳሉ ነበር የተባለው፡፡ አንድ ሰው በ100/100 ከከፈለ በዚህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ውስጥ አይካተትም ሙሉውን የከፈሉ ሰዎች ከባንክ ጋር ምንም ብድር ስለማይሹ በዚህ ፕሮግራም ሊጠቃለሉ አይገባም፡፡ ለነዚህ ሰዎች አስተዳደሩ በ100/100 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት መዝግቦ ቦታ በመስጠት ልዩ  መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት መንደፍ አለበት፡፡
‹‹በ10/90፣ በ20/80 እና በ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ከ800,000 (ስምንት መቶ ሽህ ) በላይ ቤት ፈላጊዎች ተመዘገቡ፡፡ በዚህ ፕሮግራም በድምሩ 317,863 ቤቶችን የገነባና እየገነባ በ653.3 ሄክታር መሬት ከሊዝ ነፃ ማቅረቡንና 17.5 ቢሊዩን ብር ቀጥታ ድጎማ ማድረጉን ከንቲባው ገልጧል፡፡››
 Approximately 860,000 people are registered across the three housing schemes – 10/90, 20/80 and 40/60 In addition to the ongoing construction of low cost houses, the Addis Abeba Saving Houses Development Enterprise (AASHDE) has embarked on the construction of new condominium houses at a cost of more than one billion Birr, Fortune learnt
‹‹More than 862,000 residents open special saving accounts for housing፡- ADDIS ABABA, June 28, 2013-A total of 862,216  Addis Ababa residents opened special saving  accounts for 10/90 and 20/80 housing schemes at the Commercial Bank of Ethiopia. The CBE will finance from 80% to 90% of the total cost of the houses while the rest will be covered by residents as down payment. ››
የ40/60  የጋራ መኖሪያ ቤቶች
  • በ2005 ዓ/ም የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተመዝጋቢዎች 160,000 (መቶ ስልሳ ሽህ) ሲሆኑ ለባለአንዱ መኝታ ቤት 162,000 ብር፣ለባለሁለት መኝታ ቤት 250,000 ብር እና ለባለሦስት መኝታ ቤት 386,000 ብር ዋጋ ተተምነዋል፡፡ ከመቶ ስልሳ ሽህ ተመዝጋቢ ሰዎች 154 ሥህ ሰዎች በየወሩ በባንክ ተቀማጭ ገንዘብ ያደርጋሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ 29 ሽህ ሰዎች ወይም 40 በመቶው የኮንዶሚኒየም ቤቱን የግንባታ ውጪ ከፍለዋል እንዲሁም 13 ሽህ ሰዎች ሙሉውን ክፍያ ፈፅሟል፡፡
  • የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ግባታቸው በመጠናቀቅ ላይ ሚገኙት በአቃቂ ክራውን ሆቴልና በሠንጋ ተራ በተገነቡት 1,292 ቤቶች ተገነቡ፡፡ 96.12 በመቶ ተጠናቀዋለወ፡፡ አስተዳደሩ የገነባውን ቤቶች ለኢትጵያ ንግድ ባንክ ያስረክባል፡፡
የ10/90 እና 20/80  የጋራ መኖሪያ ቤቶች
  • በ2005 ዓ/ም የ10/90 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተመዝጋቢዎች 700,000 (ሳባት መቶ ሽህ) ሲሆኑ ለባለአንዱ ፣ለባለሁለት እና ለባለሦስት መኝታ ቤት ለመገንባት ተመዝግበዋል፡፡
  • የ10/90 እና 20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት በአራት ኣመታት ውስጥ ግንባታቸው የተጠናቀቁ  39,249 ቤቶች ብቻ ናቸው፡፡ ይህም  6 በመቶ ተጠናቀዋል ማለት ነው፡፡ አስተዳደሩ የገነባውን ቤቶች ለኢትጵያ ንግድ ባንክ ያስረክባል፡፡የአዲስ አበባ ቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ ኃላፊ ኃይሌ ቀንአ ለዋልታ ሬዲዩ እንደገለፁት፡፡
  • የልማታዊው መንግሥት የቤት ግንባታ በዚህ የቀንድ አውጣ ፍጥነት መጎዝ ከቀጠለ የተመዘገበውን 700 ሽህ ነዋሪዎች የቤት ባለቤት ለማድረግ ግማሽ ክፍለ ዘመን 55 ዓመታት በላይ ዓመታት ይፈጃል ማለት ነው፡፡
ማጠቃለያ
በአዲስ አበባ በ2005ዓ/ም 860 ሽህ የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች ቤት ለማግኘት ተመዝግበው እድላቸውን እየተጠባበቁ ነው፡፡ የህወሓት የጦር አበጋዞች መንግሥት ቤት ልማት ፕሮጀክት ፕሮግራም ከጀመረ 4 ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በእነዚህ 4 ዓመታት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ40/60  የጋራ መኖሪያ ቤቶች 1,292 እንዲሁም የ10/90 እና 20/80 ቤቶች 39,249 በድምሩ  40,541 ኮንዶሚኒየም ቤቶች ወይም 4.7 በመቶ ብቻ  ተገንብቶል ማለት ነው፡፡የልማታዊው መንግሥት የቤት ግንባታ በዚህ የቀንድ አውጣ  ፍጥነት መጎዝ ከቀጠለ የተመዘገበውን 860 ሽህ ነዋሪዎች የቤት ባለቤት ለማድረግ ብዙ ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ይፈጃል ማለት ነው፡፡
በአዲስአበባ ከተማ ከተማው ነዋሪዎች አንገብጋቢ መኖሪ ፍላጎት ከአቅርቦቱ ጋር ሊጣጣም አልቻለም፡፡ በዚህም ተነሳ ከፍተኛ የሆነ የመኖሪያ ቤት እጥረት መኖሩ ይታወቃል፡፡ ዜጎች የመኖሪያ ቤቱን ዋጋ 10 በመቶ፣ 20 በመቶ 40 በመቶ መቆጠባቸውን፣ ቅድመ ሁኔታዎችን ማሞላታቸውን፣ ለብድር ብቁ መሆናውን እንዲሁም  ሂሳባቸውን በባንክ ማስቀመጣቸው ሲረጋገጥ ባንኩ የሚያቀርበው ብድር የመኖሪያ ቤቱን ዋጋ  90 በመቶ፣ 80  በመቶና 60 በመቶ ብድር ያዘጋጃል፣ብድሩንም ባንኩ ይፈቅዳል፡፡
ዜጎች የመኖሪያ ቤቱን ዋጋ 10 በመቶ፣ 20 በመቶ 40 በመቶ ቆጥበው ልክ ዕጣው ሲደርሳቸው የ10፣20 እና 40 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ መክፈል ግዴታ አለባቸው፡፡ከምግብ፣ ከልብስ፣ከልጆች ትምህርት ቤትና ከሌሎች ተጨማሪ ወጪዎች ባሻገር ማለት ነው፡፡
‹‹ሆኖም በዋጋ ግሽበት ወይንም በውጭ ምንዛሪ ልዩነትና በሌሎች በማንኛውም ምክንያት በቤቱ መነሻ ዋጋ ላይ የሚመጣ የዋጋ ጭማሪ 40 በመቶ ቁጠባውን ተጠቃሚው የሚሸፍን ሲሆን 60 በመቶ ተመጣጣኝ ብድር ባንኩ ይሸፍናል፡፡››….‹‹ለብድሩም 7.5 በመቶ የብድር ወለድ በዓመት ይታሰባል፣ሆኖም የወለድ ስሌቱ በኢትዩጵያ ንግድ ባንክ የተመን ክለሳ ሊያደርግበት ይችላል፡፡›› ይላል፡፡
ኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ የዋጋ ንረት ተሸካሚው ማን ነው መንግሥት በዚህ ዋጋ ኮንዶሚኒየም ቤት በሁለት አመት ሠርቼ አስረክባለሁ ብሎ ብዙ አመታት ከፈጀበት ጥፋቱና የዋጋ ግሽበቱ ተጠያቂ የሚሆነው ማን ነው፡፡
‹‹However, due to inflation of construction material, labor costs and design changes, the prices had to be increased to an unspecified amount.››. The price for each condominium unit will increase by an unknown amount. According to Addis Ababa housing enterprise official Ato Yidnekachew Walelign, the 40/60 condominium lottery will be handled by Commercial Bank of Ethiopia.››
‹‹Currently, 38,709 condominium units are under construction on 12 sites around Addis Abeba. However, most of the projects are behind schedule which has brought serious backlash from people saving money.
ችግሮች
  • የመንግስት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት መንግስት ባጀት እየመደበና ዜጎችም እየቆጠቡ ከፍተኛ መዋለነዋይ የሚፈስባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች በጣም አዝጋሚ በሆነውና አቅም በሌለው የመንግስት ቢሮክራሲ መከናወን አይችልም፡፡ የመንግስት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት እየተገነቡ ያሉት ቤቶች ጥራት አጠያያቂ ሆኖል፡፡ ሥራ ተቆራቾችና አማካሪ ድርጅቶች በህጉ መሠረት ኃላፊነታቸውን አልተወጡም፡፡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች አሠጣጥ ግልፅነት የጎደለውና አድሎዊ መሆኑ የአደባባይ ሚስጢር ነው፡፡ ለፖለቲካ ካድሬዎች፣ ለመከላከያና ለፖሊስ ሠራዊት፣ለደህንነት አባሎችና እንዲሁም በዘር ላይ የተመሠረተ መጠቃቀምያ፣ በአጠቃላይ የአፓርታይድ ስርዓት መዘርጋቱን ዜጎች በማስረጃ ይመሠክራሉ አሊያም ይህን ሙስና ጊዜ ያወጣዋል፡፡
  • መንግሥት ‹‹በልማት ስም!›› የዜጎችን መሬት በመንጠቅ በጨረታ መሬቱን በመሸጥ ዜጎቹን ንብረት የማፍራት መብት ህገ-መንግስታዊ መብት በመግፈፍ፣ ነባር የመኖሪ መንደሮች ‹‹በልማት ምክንያት›› በሚፈናቀሉ ዜጎች ሁኔታውንና የቤት ችግሩን ይበልጥ አባብሶታል፡፡
  • በፊዴራል ደረጃ ካሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች መካከል 77 ቢሮዎች፣ የራሳቸው ቢሮዎች/ህንፃ የሌላቸው ስለሆነ የግለሰብ ህንፃን እንደ ቢሮዎች ተከራይተው 380 ሚሊዩን ብር በዓመት ይከፍላሉ፡፡ መንግሥት የራሱን ቢሮዎች ሳይሰራ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት አከናውናለሁ ማለት ውሃ አይቆጥርም፡፡
  • የህወሓት መንግሥት ለዝቅተኛው ህብረተሰብ የኮንዶሚኒየም የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሳያመቻች ለመካከለኛና ለኃብታሞች የሪል እስቴት የቤቶች ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ ነድፎ የህዝቡን መሬት በመንጠቅ ለእነዚህ የሪል እስቴት ዲቨሎፐርስ ሽርካነት በሙስና የሸጠ መንግሥት ነው፡፡
  • የቤቶችና ቁጠባ ባንክ፣(ሞርጌጅ ባንክ) መክሰርና ወደ ንግድ ባንክ ጋር መዋሃድ የህወሓት መንግሥት በባንኩ ብዙ ሚሊዩን ብር ተበድረው ባለመክፈል ባንኩ የደረሰበት ኪሳራና ታላቅ ሴራ ጊዜ ያወጣዋል፡፡
ሞርጌጅ ባንክ (የቤቶችና ቁጠባ ባንክ)
በኢትዩጵያ  ውስጥ የመኖሪያ ቤቶች እጥረትና ችግር በዜጎች በቅድሚያ ከሚነሱት ችግሮች መካከል ናቸው፡፡የቤቶችና ቁጠባ ባንክ፣(ሞርጌጅ ባንክ) ለህብረተሰቡ በረጅም ጊዜ የሚከፈል የብድር አቅርቦት ተደራሽ በማድረግና የህብረተሰቡን የገንዘብ ቁጠባ ባህል ለማሻሻል፣ ዜጎች በግላቸው ተደራጅተው ያለአንዳች አድሎ በግልፅነት፣ ሁሉም ባለድርሻ አከላት ማለትም የቤት ገንቢዎች ገንዘብ በመቆጠብ፣የቤቶችና ቁጠባ ባንክ ብድር በማመቻቸት፣ መንግስታዊ የከተማ አስተዳደር መሬት በማመቻቸት ሁሉም በተሳተፉበት የመኖሪያ ቤቶች ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ ነድፎ የተሠራበት ወርቃማ ጊዜ ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ፣የቤት ኪራይ ዋጋ አንድ ተከራይ ከሚያገኘው ገቢ ከ40 እስከ 50 በመቶ ደርሶል፡፡ በከተማ የሚኖሩ ዜጎች ለምግብ ፍጆታ 55 በመቶ ከገቢያቸው ያወጣሉ፡፡ እንዲህም ሆኖ አንድ መኖሪያ ቤት ለማግኘት የተመዘገበ ዜጋ በየወሩ ከሚያገኘው ላይ መቆጠብ አለበት፡፡ ይህ ሁሉ መሥዋትነት የከፈሉ ዜጎች ገንዘባቸውን ቆጥበው ቤቶቹ ሳይሠሩ በትንሹ ከ4 እስከ 12 ዓመታት በቤት ኪራይ ችግርና በቁጠባ ሲሰቃዩ ምን ዓይነት በሙስና የተጨማለቀ መንግሥት እንዳለን መረዳቱ አያዳግትም፡፡

የቤቶችና ቁጠባ ባንክ ዓላማዎች
  • ዝቅተኛ ኑሮ ደረጃ ያላቸው ዜጎች በማህበር ተደራጅተው፣ ከገቢያቸው ፣በዝግ አካውንት በየወሩ ገንዘብ በመቆጠብ፣ በረዥም ጊዜ ሞርጌጅ ቤቶች እንዲገነቡ ማድረግ
  • መካከለኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በማህበር ተደራጅተው፣ ከገቢያቸው፣በዝግ አካውንት በየወሩ ገንዘብ በመቆጠብ፣ በማህበር ተደራጅተው እንዲገነቡ ማድረግ
  • ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በማህበር ተደራጅተው፣ ከገቢያቸው፣በዝግ አካውንት በየወሩ ገንዘብ በመቆጠብ፣ በማህበር ተደራጅተው እንዲገነቡ ማድረግ
  • ባንኩ ለቤት አልሚዎች ብርድ በማመቻቸት ለተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች እንደ ገቢአቸው መጠን የረዥም ጊዜ ብድር በማበደር ከተበደሩበት ዓመት እስከ ጡረታ ሊወጡ አንድ አመት እስኪቀራቸው ድረስ ማለትም በትንሹ ከ25 እስከ 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሚከፈል ብድር ያመቻች ነበር፡፡ የባንኩ ዋነኛ ዓለማ ህብረተሰቡ ካለው ገቢ ቆጥቦ ቤት እንዲሰራ ሁሉንም ነገር ማመጫቸት ነበር፡፡
  • የባንኩ ተበዳሪ ማሳወቅ ያለበት ወርሃዊ ገቢውን የደሞዙን አንድ አራተኛ በወር እየከፈለ በቡዙ አመታት ውስጥ የሚከፈል ብድር ማመቻቸት ነው፡፡ የባንኩ ደንበኛ የህይወት ኢንሹራንስና የእሳት ኢንሹራንስ እንዲገባ ባንኩ ያደርጋል፡፡ የወለድ ምጣኔው 4 በመቶ ነበር፡፡ወያኔ ዛሬ 7.5 በመቶ የወለድ ምጣኔ ይጠይቃል፡፡
  • መንግስት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ለመቅረፍ የፖሊሲና የስትራቴጂ ለውጥ ማድረግ ይጠበቅበታል ማለትም ሞርጌጅ ባንክን ማፍረስ አልነበረበትም፡፡ የቤቶችና ገንዘብ ቁጠባ ባንክ ከ15 እስ 30 ዓመታት ለሚደርስ ጊዜ በማበደር በአለማችን አሥራሩ ይታወቃል፡፡ የንግድ ባንክ ለንግድና ለማኑፋክቸሪንግ ሥራዎች ከ5 እስከ 10 ዓመታት ጊዜ የሚቆይ ብድር ለደንበኞቹ ያመቻቻል፡፡
  • የቤት አልሚዎች መጠነ ሠፊ ተሳትፎ የነበራቸው በመሆኑ ግልፅ አሠራር፣ ተጠያቂነት፣ የባለቤትነት ስሜትና ከቤቱ ግንባታ ጀምሮ እስከ ፍፃሜው ድረስ በጋራ ቤቶች ግንባታ ሥራ ላይ ይሰማሩ ነበር፡፡ እንደዛሬው ግልፅ ያልሆነ ለአድሎ በር ከፋች የሆነ ሎተሪ ብሎ ጨዋታ የለም፡፡ ቤት ሠሪው ተጀምሮ እስከሚጨረስ መብትና ግዴታውን ያውቃል፡፡
  • ሞርጌጅ ባንክ (የቤቶችና ቁጠባ ባንክ) በሃገሪቱ ያለውን የቤት ልማት ችግርን ለመቅረፍ መልሶ ማቆቆም ብቸኛው ዋነኛ መፍትሄ ነው፡፡ የቤቶችና ገንዘብ ቁጠባ ባንክ ሠራተኞች ምስክርነታቸውን ይስጡበት፡፡
የቤቶች አቅርቦትና ፍላጎት፡- (Housing Supply and Demand)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤት ሠርቶ ያስረከበው ለ175,000 ሰዎች ብቻ ነው የቤት ልማት ፕሮጀክት ፕሮግራም ከተጀመረ 12 ዓመታት ተቆጥረዋል፣በሃገሪቱ በየአመቱ 150,000 (መቶ ኃምሳ ሽህ) የቤት ፈላጊዎች አሉ፡፡ የወያኔ መንግስት እየሄደበት ያለው መንገድ የቤት ችግርን በፍጽም አይፈታውም፡፡ የህብረተሰቡን የቤት ፍላጎት ከማሞላት አንጻር ጉዞው የዔሊ ነው፡፡ የቤት ግንባታ ፕሮጀክቶቹ በሁለት ዓመት ለማጠናቀቅ የታቀደ ግንባታ አራት ዓመታት ይፈጃል፣ የግንባታ ሂደቱም ሙያዊ ያልሆነ ቢሮክራሲ የበዛበት ነው፡፡ አሁን ባለው ግንባታ ሂደት ከቀጠለ የህዝቡን የቤት ፍላጎት በፍጽም ማርካት አይቻለውም፡፡ ማለትም የዜጎችን የቤት ፍላጎት ከመፍታት አንጻር በጣም ቀርፋፋ ነው፡፡ ለዚህም ዋነኛ ማስረጃ በሃገሪቱ የከተማና የገጠር ከተሞች የህዝብ ብዛት ያገናዘበ የቤቶች ልማት ጥናት ባለመኖሩ የቤት ፈላጊዎች ቁጥር ፍላጎትና አቅርቦት ሰማና ምድር መሆኑ እሙን ነው፡፡የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፈላጊዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቆም በየዓመቱ ከ100,000 ሽህ በላይ ተመራቂዎች ይወጣሉ፡፡ መንግሥት ሌላ ዙር ምዝገባ ቢያካሂድ የቤት ፈላጊው ቁጥር የትዬለሌ በመሆኑ ሌላ ምዝገባ እንደማይካሄድ ከንቲባ ድሪባ ኩማ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ሆኖም የቤት ግንባታ ፕሮግራም ለሥራ ዕድል ፈጠራ ስኬት ማምጣቱና የአገር ውስጥ የግንባታ አቅምን ከመፍጠር አንፃር በጎ ጎኖች አሉት፡፡
አማራጭ መፍትሄዎች፣- መንግሥት አሁን እየተጎዘ ባለበት ረዥም መንገድ የተለየ አጭር አቆራጭ አማራጭ መንገድ ካልፈለገ የቤት ችግሩ በአጭር ጊዜ አይፈታም፡፡
  • ሞርጌጅ ባንክ፣-ለዝቅተኛ ገቢ ላላቸውና፣ መካከለኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ቤት እንዲያለሙ ፣አቅም ላላቸው የአገር ውስጥ ሥራ ተቆራጮችና አማካሪ ድርጅቶችን ሙሉ ለሙሉ ኮንትራት ሰጥቶ እየተከታተለ ቤቱ እንዲገነባ ማድረግ
  • ሞርጌጅ ባንክ በኩል መንግሥት ለሪል እስቴት አልሚዎች መሬት በዝቅተኛ የሊዝ ዋጋ በማቅረብና፣ መሠረተ ልማት መንገድ መብራት፣ውኃ የመሳሰሉትን በማሞላት፣ከሞርጌጅ ባንክ ጋር ትስስር በመፍጠር አልምተው ሲያበቁ በተተመነላቸው ዋጋ ቤቶቹን ሞርጌጅ ባንክ ለደንበኞቹ እንዲያስረክብ ማድረግ፣
  • ሞርጌጅ ባንክ፣ የአገር ውስጥና የውጭ ተቆራጮችና የሪል እስቴት አልሚዎች በተናጥል ወይም በሽርክና እንዲሠሩ ማነጋገርና መጋበዝ፣አለበት እንላለን፡፡
ኮልፌ ቀራንዩ ክፍለ ከተማ የቁሻሻ መጣያ አደጋ፡-ወረዳ አንድ ላለፉት 50 ዓመታት በተከለለው 37 ሄክታር የደረቅ ቁሻሻ መጣያ፣ ከፍታው 13 ሜትር፣ ጥልቀቱ 40 ሜትር ተደርምሶ የ113 ዜጎች ህይወት ቀጥፎል፡፡  ይህ የቁሻሻ መጣያ አደጋ ሊያስከትል ይችላል በሚል ስጋት አገልግሎት እንዳይሰጥ ታሽጎ ነበር፡፡መንግሥት ሰንዳፋ የቁሻሻ ማስወገጃ በ1 ቢሊዩን ብር አስገንብቶ በኦሮሚያ ህዝባዊ እንቢተኝነት ትግል ህዝቡ በመከልከሉ ቆሞል፡፡ ከዛም በበፊቱ ቦታ በድጋሚ ቁሻሻ መጣል ተጀመረ፡፡
የምዕራብ አፍሪካ ሃረራቶች ከፍተኛ የከተማ ነዋሪዎች እድገት፣ በከተማ መሬት ይዞታ ፖሊሲና የከተማ አስተዳደራዊ ጥገናዊ ለውጥ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አስከትሎል፡፡ የከተማ ነዋሪዎች ቁጥር መጨመር፣የገጠር የከተሞች ነዋሪዎች ቁጥር  እድገትና፣የገጠር ነዋሪዎች ህዝብ ቁጥር እንዲጨምር አድርጎል፡፡ በአብዛኛው የከተማዎች እድገት ዋነኛ ምክንያት ከገጠር ወደ ከተማ የሚፈልሠው ህዝብ ቁጥር ማሻቀብን አስከትሎል፡፡ መንግሥታት በአጭርና በረዥም ጊዜ የከተማ መሬት ይዞታ ፖሊሲ መንደፍና  የገጠር ነዋሪዎች የመሬት ይዞታ ፖሊሲ መንደፍ  ችግር ለመቅረፍ ዋነኛ መፍትሄ ነው፡፡
Table 4: Urban Slums in Eastern Africa
CountrySlum Annual Growth RatePopulation Slum 1990(‘000s)Population Slum 2001(‘000s)
Ethiopia4.85,98412,315
Kenya5.93,9859,620
Madagascar5.32,5625,696
Sudan5.25,70812,441
Tanzania6.25,60114,113
Source: Habitat (2006).
አብዛኛው የምዕራብ አፍሪካ ሃረራቶች የከተማ ነዋሪዎች የሚኖሩት በቁሻሻ ሥፍራች (Slums Areas) ማለትም በከተማው ውስጥ በሚገኙ የማይፈለጉ ለሰው ልጆች መኖሪያነት የማይመቹ የተለያዩ ቁሻሻ ሥፍራዎች ነው፡፡ የከተማ ደሃ ነዋሪዎች በነዚህ ቁሻሻ ቦታዎች ላይ ሠፍረው ይኖራሉ፡፡ ቦታዎቹ በመንግሥትና በሃብታም ግለሰቦች የማይፈለጉ ገደላማ፣ወንዞች  ዳር፣ረግራጋ ሥፍራዎች በመሆናቸው የፋብሪካዎች ኬሜካሎች ዝቃጭ መፍሰሻ ሥፍራ፣የቁሻሻ መጣያ ቦታዎች በመሆናቸው ለጤና ተስማሚ ስላልሆኑ ነዋሪዎቹ በተለያየ በሽታ ተጠቂዎች ናቸው፡፡  በቁሻሻ ሥፍራዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች አመታዊ ዕድገት ምጣኔ ከአመት አመት በመጨመር ላይ ይገኛል፡፡ ከሰንጠረዡ መረዳት እንደሚቻለው በኢትጵያ  በቁሻሻ ሥፍራዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች አመታዊ ዕድገት ምጣኔ 4.8 በመቶ ሲሆን በ1990 እኤአ አምስት ሚሊዩን 984 ሽህ ሰዎች ይኖሩ ነበር፡፡ በ2001 እኤአ አስራ ሁለት ሚሊዩን 315 ሽህ ሰዎች  በቁሻሻ ሥፍራዎች እንደሚኖሩ በጥናት ተረጋግጦል፡፡ ከ1990 እኤአ እስከ  2001እኤአ ባለው አስራ አንድ አመታት ውስጥ በ48.6 በመቶ የነዋሪዎች ቁጥር ጨምሮል፡፡ በ2017 እኤአ ምን ያህል ሊደርስ እንደሚችል በግምት ስናሰላው የትየለሌ ስለሚሆን የከተማ መሬት ይዞታ ፖሊሲና የከተማ አስተዳደር ይህን ችግር ለመቅረፍ እውቀትም፣አቅምም፣ ብቃትም የለውም፡፡  በኮልፌ ቀራኒዬ የቁሻሻ ሥፍራ የሚኖሩ 113 ነዋሪዎች ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱ በከተማው አስተዳደርና መንግሥት ንዝህላልነትና ለዜጎቹ ደንታ እንደሌለው ያሳያል፡፡ ሥራቸው በየግዜው የከተማ መሬት ከህዝብ እየነጠቁ በጨረታ በመሸጥ ላይ ያተኮሩ ስው ሰው ያልሸተተ የከተማ ልማት ፖሊሲ ያላቸው በመሆኑ ነው፡፡ አሁንም ገደል ስር ቤቶች ሠርተው የሚኖሩ አደዋ አደባባይ ወደ ሃያ ሁለት መሄጃ ኮንጎ ሠፈር ነዋሪዎች ህይወት ትኩረት ሊሠጠው ይገባል፡፡ እንዲሁም በግንፍሌ፣ ቀበናና ቡልቡላ ወንዞች ዳርቻ ቤት ቀልሰው የሚኖሩ ዜጎች በአደጋ ላይ መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ የከተማ አስተዳደሩና ከንቲባ በአዲስ አበባ የሚገኙ በፈንጅ ወረዳ ላይ በሚኖሩ ዜጎች ህይወትን ከአሁኑ መታደግ ኃላፊነት አለባቸው፡፡
ለሞች ቤተሰቦች መፅናናትን እንመኛለን!!!
ሥርዓቱ ካልተለወጠ የቤቶች ችግር አይፈታም!!!
ለሚኒስትሮች፣ጀነራሎች፣የደህንነት ሹሞች፣ዲፕሎማቶች በሙስና ለቤት መሥሪያ የተሠጠ መሬትና ቤት ይመለስ!!!
የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ!!! አስቸኮይ ጊዜ አዋጁ ይነሳ!!!

No comments:

Post a Comment