Wednesday, March 15, 2017

ለሥልጠና ወደ አድዋ የተወሰዱ የወልቃይት ዐማሮች በድብደባ ጉዳት ደረሰባቸው ከሙሉቀን ተስፋው source zhabesha


ከሙሉቀን ተስፋው
የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን የጨረሱ የወልቃይት ወጣቶችን አሰልጥኜ ሥራ አስይዛችኋለሁ በማለት ነበር ሕወሓት ወደ አድዋ የወሰዳቸው፡፡ ከወልቃይትና ጠገዴ አካባቢዎች ተመልምለው የተወሰዱ ወጣቶች አድዋ ሲደርሱ ግን የጠበቁትን ሥልጠና አላገኙም፡፡
አብረዋቸው በሚማሩ የትግራይ ተማሪዎችና አስተማሪዎች ‹‹ስለምን ዐማራ ነን አላችሁ፤ ትግሬ የተጠላው በእናንተ ምክንያት ነው!›› የሚል ወከባና ጥያቄ ይደርስባቸዋል፡፡ ከዚያ ወጣቶቹ ‹‹ታዲያ ምን ልንል ነው፤ እኛ እኮ ዐማራ ነን›› የሚል የማያወላዳ ምላሽ ይሰጣሉ፡፡
ትናንት መጋቢት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ለሥልጠና የሔዱት ሁሉም ወጣቶች ያለምንም ረዳት በሰው አገር የተደበደቡ ሲሆን ሐጂ የተባለ ወጣት ከፍተኛ የአከርካሪ ጉዳት ደርሶበታል ተብሏል፡፡ በድብደባው ጉዳት የደረሰባቸው ዐማሮች እስካሁን ምንም ዓይነት ሕክምና ካለማግኘታቸውም በተጨማሪ ወደ ወልቃይት እንዳይመለሱ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገባቸው ነው ተብሏል፡፡ ወደ ወልቃይት ከተመለሱ ለበለጠ አደጋ እንደሚጋለጡና እንደሚታሰሩም ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡

No comments:

Post a Comment