Tuesday, March 14, 2017

በአምቦ የጥይት ማምረቻ ፋብሪካ ውስጥ የሚፈፀም በደል ተጋለጠ source zhabesha ከሙሉነህ ዮሐንስ


ከሙሉነህ ዮሐንስ
በእውነት ምስክርነት የተዘበ ነውና በጥሞና አንብባችሁ እራሳችንን ለትግል አናዘጋጅ። ቢያንስ እንኳ እግዚአብሔር ይህን ድብቅ ያጋልጥ ብላቹህ ፀልዩ።
በጥይት ማምረቻው ውስጥ እውነት እላቹሃለሁ አንድ አንኳ የትግራይ ሰው በዕለት የማምረት ተግባሩ ውስጥ የሉበትም፡፡ ነገር ግን በሰው ኃይል ምደባ ተቆጣጣሪነት ..ወዘተ ድርሻ እነሱ እና እነሱ ብቻ ናቸው፡፡ ለምን ጥይት በማምረቱ ስራ ትግሬዎቹ የሉም? ለምትሉ መልሱ እና እውነታው ይኸውላችሁ፡-
፨፨፨ ጥይትን ለማምረት የሚጠቅመው የፖታስየም ናይትሬት ኮምፓውንድ(KNO3) /ውህድ እጅግ በጣም ለካንሰር የሚያጋልጥ በርካቶችንም ከዚህ በፊት ለሞት እና ለመካንነት የዳረገ ነው፡፡ በምሬት አንድ ወታደር ያለችኝም ይህ የማምረቱን ስራ የምንሰራው ሁላችንም ሴቶች ነን በቀን እስከ 15 ካርቶን እያንዳንዳችን እናመርታለን፡፡
አንድም የትግራይ ሴቶች የሉም። በአብዛኛው የአማራ ሴቶች ሲሆኑ ቀጥሎ የኦሮሚያና የደቡብ ናቸው፡፡ እጅግ በጣም የሚያሳዝነው ግን እያለቀሰች የነገረችኝ፦
እኔ ባጋጣሚ የትግል አጋሬን አግብቸ አንድ ሴት ልጅ ወደ ዚህ ከመግባቴ በፊት ወልጃለሁ ከቤተሰቦቸ ጋርም ትኖራለች፡፡ ሌሎች ግን የወሊድ ምርመራ ያውም በግል ሲመረመሩ ከ11 ጓደኞቸ 9ኙ በጥይት ማምረቻው የተለያዩ ኬሚካሎች ምክንያት መክነዋል። ጡቶቻቸው አካባቢ ሙሉ በሙሉ ጥላሸት/ማድያት የሚመስል መልክ አንደወጣባቸው በለቅሶ ያስረዳሉ፡፡ ምክንያቱም የሚሰሩት ያለ ሴፈቲ/የአዳጋ መከላከያ አልባሳትና ትጥቅ ስለሆነ፡፡ የሚሰጥ ወተት አንኳ ካቆመ ቆየ በማለት የአረመኔ ተግባራቸውን ሀገር ይስማው ብለው አስረድተዋል ፡፡
ለደህንነታቸው ሲባልም ነው ስማቸውንና ጠቋሚ መረጃ ያልጠቀስኩት፡፡ ታድያ ትግራዮች እውን ኢትዮጲያዊ ስሜት አላቸው፡፡ የውጭ ሀገር ዜጎች እንኳ በዚህ መልኩ የረቀቀ ዘር የማጥፋት ዘመቻ አልሰሩብንም፡፡ ወገን ስለዚህ አባባሉ የሚለው ማወቅ ስለሰዎች መኖር ነው ይላል፡፡ ስለዚህ ካወቅን የአቅማችንን ሁላችንም ወደ ትግል መግፋት አለብን፡፡ ቢያንስ እነሱን በድርጊታቸው እንኳ ልንጥላቸው ይገባል።
ቋሚ አምደኛችንን ከልብ እናመሰግናለን።

No comments:

Post a Comment