Sunday, January 22, 2017

ብርቱ ሚስጥር በጋምቤላ ፍጅት ሲጋለጥ! የጋምቤላ ታጋች ህፃናት ለፖለቲካ ፎጆታ እየሆኑ ነው! ሙሉነህ ዮሃንስ



ብርቱ ሚስጥር በጋምቤላ ፍጅት ሲጋለጥ!
የጋምቤላ ታጋች ህፃናት ለፖለቲካ ፎጆታ እየሆኑ ነው!
ህፃናቶቻቸውን እና እንስሶችን እንደፈለጉ የደቡብ ሱዳን የሙርሌ ጎሳ አባላት የሚነጥቁባቸው ዞን ውስጥ ከፍተኛ ሹመኛ የሆነ ሰው ነው ያደረሰን።
ሚስጥሩን በደረስኩበት መረጃ መሠረት ገና ከዚህ በላይ የወረዳው ሰው ሁሉ ሊወሰድ ይችላል ይላል፡፡ ምክንያቶቹን እንዲህ ዘርዝሮ ልኮታል፡-
1. ለም የእርሻ መሬት ከእኛ እስከ አጎራባች አለ ይህን በሚያርሱ የወያኔ ኢንቨስተሮች ለበርካታ አመታት ከህይወት እስከ ንብረት መስዋትነት አስከፍሏቸዋል።
2. #ወያኔን ሊያሰጋ የሚችል ሁሉ እስካሁን በሙሉ ሃይል በየቦታው ባይንቀሳቀስም በወታደራዊ ጥናታቸው መሰረት ያሰጋልና ስለሚሉ እስከዛው እኛም የስጋት ምንጭ ተደርገን ስለምንቆጠርና ለጥቃትም በቀላሉ ተጋላጭ ስለሆንን ዘራችን የሚጠፋበት አደጋ ውስጥ ገብተናል።
3. ከደቡብ ሱዳን ውሎገብ የፈለግነውን የጦር መሳርያና የእለት ፍጆታ ሸቀጥ ያለስጋት እናስገባ ነበር። ያንንም ለማስቀረትና እኛል ለመፍጀት ነው።
4. የወያኔ ሴረኛ ቡድን ከደቡብ ሱዳን ጋር በጥበብ በመመሳጠር በግጦሽ በማመሳሰል ምንም የማያውቀውን ህዝቡን እያስገደለ ነው።
5. ለወረዳው ቅርብ በሆነ ሁኔታ የሠፈረው በትግራይ ኃላፊዎች ብቻ እንደፈለጉ የሚያዙት ልዮ ኃይል፣ ፌደራል ፖሊስ፣ ሽምቆች እንዲሁም መከላከያም አለ። የመጀመርያዋ ጥይት ሳትጮህ ለመከላከያ አዛዡ ተደውሎ ነበር እንደርሳለን ብለው አውቀው የውሃ ሽታ ሆነው ቀሩ፡፡
6. ቢያንስ በቅርብ ርቀት አስተማማኝ የአየር ኃይል አለ። ታድያ በትንሽ ደቂቃ ብቻ እስከ ወረዳው መድረስ ይችል ነበር ግን አልሆነም። ለምን አትበሉ። ዘር ፍጅቱ በወያኔ የተቀነባበረ ነው።
7. መሬታችንን ያለግብር የሚያርሱት የትግራይ ዜጎች ቢሆኑ ኖሮ የተጠቁት 57ቱ ወገኖቻችን ሳይመለሱ ተጨማሪ 16 ህፃናት መወሰዳቸው ሌሎችም ሊሞቱ ቀርቶ ደቡብ ሱዳንን በጨፈለቀ ነበረ፡፡
8. #በመጨረሻም የሱማሊያን አልሻባብ ተሻግሮ ለመግጠም ሰራዊት የሚልክ እንዲሁም አልፎ ላይቤርያና ሱዳን ሄዶ ሰላም አስከብራለሁ እያለ ኃይል የሚገብር የወንጀለኞች ጥርቅም ለራሳችን ዜጎች መሆን ሳይችል ይብስ ብሎ በአስቸኳይ አዋጅ ስም ሰላማዊ ህዝብ ሲያሸብርና ሲጨፈጭፍ ማየት እጅግ ያማል።
9. አሁን እኛም በስለናል። በተለይ የእኛን ወጣቶች በገፍ ለውትድርና የማያውቁትን ገጠራማው አካባቢ የሚመለምለው እንዳይሳካ ተግተን እየሰራን ነው። ለነፃነታችን መከበር ደቡብ ሱዳንን ሣይሆን ህዋህትን/ወያኔን ከአጋሮች ጋር ተደራጅተን እንታገላለን፡፡
ድል ለጭቁኑ ህዝብ! በማለት ይህን ብርቱ ሚስጥር ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለአለም እንዲታወቅ በአስቸኳይ ይድረስልን ብሏል።
ማሳሰቢያ፡-
ይህን ወደእንግሊዝኛና ወደተለያዪ ቋንቋወች በመተርጎም በቶሎ ስራ ልትጋሩ የምትችሉ በፍጥነት በውስጥ መስመር አግኙኝና የህዝባችንን ብሶት እናስተጋባ ለጋምቤላ ወገኖቻችን እንድረስላቸው።
አሁንስ ያማል!
ሙሉነህ ዮሃንስ

No comments:

Post a Comment