Wednesday, January 18, 2017

በስናይፐር የታጄበ ጥምቀት በጎንደር ቆንጅት ስጦታው



በስናይፐር የታጄበ ጥምቀት በጎንደር
( የጎህ ጋዜጠኛ ዞብል)
ከጎንደር ታቦቱን ከመቅደሱ ገብተው መሼከም እስኪቀራቼው ድረስ የመንግስት ወታደሮች ካህናቱን ቶሎ በሉ፣ ቶሎ በሉ እያሉ ያጣድፏቼው ነበር።
ታቦት በራሳቼው ላይ የተሼከሙ አባቶች ሁለት እጆቻቼው ታቦቱን ቢደግፉም እንባዎቻቼው በጎንደር
አስፋልት ላይ ጠብ፣ ጠብ፣ እያሉ ሲፈሱ ከበርካታ ካህናት አይኖቼ ቀረብ ብዮ አስተውያለሁ፣ መስቀል ኃይልነ ብላ የምታምን ቤተክርስቲያን ዛሬ ስናይፐር ኃይልነ የሚል መንግስት በስናይፐር የጎንደር ታቦቶች እንዲታጄቡ አደረገ። ድሮ በኦሞ መንገዱ ታጥቦ ምንጣፍ እየተነጠፈ እላዩ ላይ የሰላም ምልክት ቄጠማ የሚጎዘጉዙት ወጣቶች ዛሬ በብአሉ ስፍራ የሉም። በምትካቼው ካህናተ እግዚአብሔርን በግልምጫ እና
በስድብ የሚያዋርድ ሰራዊት ከህዝቡ በላይ ተገኝቷል። ታቦት ተሼካሚውን ካህን ተጎንብሶ አንድ ባለ ስናይፐር
“ቶሎ ቶሎ ሒድ ምን ይገትርሐል ” በማለት ሲናገር የተመለከቱ አንዲት መነኩሲት ምነው የአባቶቻችን አምላክ እንዲህ ፈጽሞ ረሰን ፣ አርባ አራቱ ታቦቶቻችን ከመዋረዳቸዉ በፊት ምን አለበት እኛን በሞት ቢጠራን በማለት ጮክ ብለው በመናገር ምርር ብለው ሲያለቅሱ ብዙ እናቶች በዋይታ አጄበዋቼው ነበር። “የምን ለቅሶ ነው ዝም በይ” ተብለው እኒህ እናት በታጣቂ ሲንገላቱ ህዝቡ መሀል ገብቶ ከባለ መሳሪያው አስለቅቋቼዋል።
ጎንደር ከወትሮው በተለየ መልኩ የጥምቀት ባዕል ሳይሆን ዘመድ አልባ አስከሬን የሚሼኝ በሚመስል መልኩ ፀጥ እረጭ ብላ በዓለ ጥምቀቱን በግዳጁ ስታከብር ፣ ታቦታቱን ወደ ማደሪያው በፌደራል፣ በመከላከያና በወያኔ ካድሬ ተከቦ በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከተማዋ ነዎሪዋቾን በተፈጥሮ አደጋ የተነጠቀች እስኪመስል በዓለ ጥምቀቱ የሰው ድርቅ መትቶት በደበዘዘ መልኩ አልፉል። ባከታሪኩ ጄግናው የጎንደር ህዝብም የተማማለበትን ጥምቀተን እንደወትሮው በድምቀት አናከብርም ያለውን ቃሉን በሚገባ አክብሯል!!!!

No comments:

Post a Comment