Monday, August 7, 2017

ባህርዳር የቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማው በተሳካ ሁኔታ ተጀመረ | ንግድ ሱቆች ዝግ ናቸው | የከፈተ እርምጃ ይወሰድበታል እየተባለ ነው source zehabesha


(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት መንግስት የዛሬ ዓመት ነሐሴ 1 የገደላቸውን ከ50 በላይ ንጹሃን የባህርዳር ነዋሪዎችን ለማሰብ በዛሬው ዕለት የተጠራው ከቤት ያለመውጣት አድማ በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ መጀመሩን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ::
የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከባህርዳር እንደገለጹት ሕዝብ ቤቱ ቁጭ ያለ ሲሆን ዛሬ በአድማ እንደሚውል ገልጸዋል:: ሱቆቻቸውን አንዳንዶች ከፍተው የነበረ ቢሆንም ማስጠንቀቂያ ሲደርሳቸው ወዲያው ዘግተው እንደሄዱም ከባህርዳር የመጣልን መረጃ ይጠቁማል::

No comments:

Post a Comment