“የብዙ ኪሎ ሜትር ጉዞ በአንድ እርምጃ ይጀመራል” ጉዞውን ለማስካት ደግሞ የጉዞ አቅጣጫውን መያዝ ግድ ይላል። ነፃነታችንን ለማስመለስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ በአስቸኳይ ታዋቂ ፖለቲከኞችን ምሁራንን የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን የሚዲያ ሰዎችን በህብረተሰቡ ተደማጭ የሆኑ ታዋቂ ሰዎችን ያካተተ ቡድን ተመስርቶ ትግሉ ሊመራ ግድ ይላል መከፋፈል ይቁም የአብዛኛው የትግል እንንቅስቃሴ ነፃነታችንን ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶቻችንን ማስከበርና ተከባብረን በሰላም የምንኖርባት ሉዓላዊነቷ የተከበረ ሀገር እንድትኖረን ነው።
የአባቶቻችንን ክብር እንዉረስ ተዋርደናልና ክብራችንን እናስመልስ ! ሀገር እያለን ባይተዋር ሆነናልና እንተባበር ! ይህንን ከጫፍ ጫፍ ያለ ህዝባዊ እንቢተኝነት ተባብረንና ተከባብረን እንምራው ልዩነቶች ካሉ ከድል በኋላ በሰለጠነ መንገድ በአግባብ በጠረንጴዛ ዙሪያ ተወያይተን እንፍታ እርስ በእርስ ተጋጭተን ሀገራችንን አደጋ ላይ እንዳንጥል በማስተዋል እንራመድ።
ከአዲስ አበባ ወጣቶች የተላከ መልእክት
ከአዲስ አበባ ወጣቶች የተላከ መልእክት
No comments:
Post a Comment