Saturday, July 30, 2016

በጎንደር የሚካሄደውን ሰልፍ ለማደናቀፍ ሕወሓት እየተሯሯጠ ነው። ሕወሓት ተሸብሮ ሕዝብን ለማሸበር አየተንደፋደፈ ነው

በጎንደር የሚካሄደውን ሰልፍ ለማደናቀፍ ሕወሓት እየተሯሯጠ ነው። ሕወሓት ተሸብሮ ሕዝብን ለማሸበር አየተንደፋደፈ ነው።
በጎንደር ተሰማርቶ የሚገኘዉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የልዩ ሐይልና የአካባቢ ሚሊሻ ባጠቃላይ ነገ የሚካሄደዉን የጎንደርን ሰልፍ ተነተርሶ የተሰጣቸዉን ሰላማዊ ሰልፍ የማክሸፍ ሴራ ያለማቀበላቸዉን የሚጠቁሙ መረጃዎች ደርሰዉናል።
በወልቃይት የዐማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴዎች ላይ የሚደርሰውን አፈናና ግድያ እንዲቆም የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በጎንደር ከተማ እሁድ ሐምሌ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. መላው አማራ ታሪካዊ ሰልፍ ያደርጋል ፡፡ በጎንደር የሚካሄደውን ሰልፍ ለማደናቀፍ ሕወሓት እየተሯሯጠ ነው።ሕወሓት ተሸብሮ ሕዝብን ለማሸበር አየተንደፋደፈ ነው። ነገ እሁድ ሃምሌ 24 2008 በጎንደር ከተማ የሚደረገው ሕዝባዊ ተቃውሞ እንዳይደረግ የሕወሓት ኣገዛዝ በከፍተኛ ደረጃ እየሰራ መሆኑን የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል። ምንጮቹ እንዳሉት በዚህ ሳምንት ሕዝቡን በስብሰባ ለማታለል ቢሞክሩም በፍጹም ሊበገርላቸው ስላልቻለ ያለው እድል የሕወሓት ሰራዊትና የኣማራ ክልል ፖሊስን በጋራ በጎንደር ከተማ ማስፈርና ወደ ከተማዋ የሚያስገቡ መንገዶችን መዝጋት ነው።
Minilik Salsawi's photo.
በዚህም መሰረት በክልሉ የፖሊስ ከፍተኛ ባለስልጣናት የተመራ ኣንድ የግብረ ሃይል ቡድን በስሩ 8 ቲሞችን በማዋቀር ከባህር ዳር ተነስቶ ጎንደር የገባ ሲሆን ይህ የኣማራ ክልል የፖሊስ ቡድንን ከጀርባው ሆኖ ለመንቀሳቀስ ከኣይከል ሳርባ ወታደራዊ ካምፕ የሕወሓት ሰራዊቶች ጎንደር ከተማ የገቡ ሲሆን በጎንደር ዙሪያ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ ፍተሻ የሚካሄድ ሲሆን ከከሰኣት በኋላ ጀምሮ በተለያየ ምክንያት ወደ ጎንደር የሚገቡ መኪኖች እንዳይገቡ እንዲደረግ ለሕወሓት ሰራዊቶች ትእዛዝ ተሰጥቷል።ይህ የሚያሳየው የሕወሓት ኣገዛዝ ከፍተኛ ሽብር ውስጥ እንደገባና ህዝብን እያሸበረ እንደሆነ ነው። በጎንደር ይካሄዳል የተባለው ሰልፍ ለኣምባገነኖች ታላቅ ሽብር መፍጠሩ በየሚዲያዎቻቸው እየለፈፉ የሚገኙት ፕሮፓጋንዳ በቂ ማረጋገጫ ነው።እሁድ ሐምሌ 24 ቀን 2008 በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ መላው አማራ ታሪካዊ ሰልፍ ያደርጋል::
http://www.mereja.com/amharic/505163
እኔም ጎንደሬ ነኝ !!! እኔም ወልቃይቴ ነኝ !!!!!!!!!

No comments:

Post a Comment