Sunday, July 31, 2016

የወያኔ የጎሳ ፖለቲካና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የተዋረደበት ህዝቡ አገዛዙን መጥላቱን ሕዝብ ያስመሰከረበት ሰልፍ ተካሄ

እናቶች በሰልፋ ለደከሙ ወጣቶች ውኃ እያቀረቡ ነው፤ የሃይማኖት አባቶች ተጋድሏችንን እየባረኩ ነው! አማራነት እኮ እንዲህ ነው! እቴጌ ባአድዋ ያደረጉትን አስታውሱ!
የወያኔ የጎሳ ፖለቲካና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የተዋረደበት ኣገዛዙን መጥላቱን ሕዝብ የመሰከረበት ሰልፍ


Minilik Salsawi – mereja.com ፖለቲከኞችን ያሳፈረው ሕዝብን ያነገሰው ዛሬ በጎንደር የተካሄደው ሰልፍ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ትግል ሂደት ውስጥ ራሱን የቻለ ጫና እንዳለው ያረጋግጣል።ሕዝብ በራሱ ያሰናዳውና የተሳካ ታላቅ ሰልፍ በጎንደር ደሞቆ ውሏል።ሕዝባዊ ኣንድነት ጎልቶ የታየበት የወያኔ የጎሳ ፖለቲካና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ የተዋረደበት ኣገዛዙን መጥላቱን ሕዝብ የመሰከረበት ሰልፍ ነበር፤የሕወሓት ኣገዛዝ በቃኽን የተባለበትም ሰልፍ ነው፥ ሚሊዮኖች ኣደባባይ ወጥተው ወያኔን ልክ እንደሚያስገቡት ነግረውታል።
Minilik Salsawi's photo.
ሕዝብን በሃይማኖት ለመከፋፈል ሞከሩ ኣልተሳካም። ሕዝቡ ሃይማኖታችንን እንደያዘን የሌላውን ኣክብረን ቤታችን በታቸው ሆኖ የኣንዱ ደስታና ሃዘን የኣንዳችን ሆኖ በተሳሰረ የኢትዮጵያዊነት ሰንሰለት ላይፈታ ታስሯል ብሎ በተደጋጋሚ እያረጋገጠ ነው። የብሄረሰብ መብት ሽፋን በሚል ኣንዱን ጨቋኝ ሌላውን ተጨቋኝ ኣድርጎ ለማቅረብ ቢሞክርም ሰሚ ጆሮ ኣላገኘም ወያኔከኦሮሞ ሕዝብ ጎን መቆሙን ኣማራው በተግባር በሚሊዮኖች ድምጹ ኣረጋግጧል፤ በሕዝብ ዘንድ ጥላቻና ዘረኝነት እንዳሌለ የጎንደሩ ሰልፍ ለገዢዎች ኣሳይቷል። ችግሩ ወያኔና ፖለቲከኞቹ እንደሆኑ እንጂ በሕዝቦች መካከል ችግር እንደሌለ ኢትዮጵያዊነት እንዳስተሳሰረ በተግባር ከመመስከሩም በላይ የወያኔን ባንድራ ተቀባይነት እንዳሌለው ታይቷል በጎንደሩ ሰልፍ።

...


No comments:

Post a Comment