Tuesday, June 6, 2017

ጥብቅ ማስጠንቀቂያ… source zhabesha

ከልዑል ዓለሜ
ከሽሬ ግንባር ለተመዘዛችሁ የህዝባዊ ትግራይ ወያኔ ሐርነት ብርጌድ አባላት እና የ25ተኛ ክ/ጦር አዲስ ምልምል ሐይል ማዘዣ ልዩ ሐይልና በ24ተኛ ክ/ጦር የወታደራዊ ስምሪት እንዲሁም ለጸረ ሽምቅና ለ31ኛ መለስተኛ እግረኛ፣ ከአዲስ አበባ ለተንቀሳቀሳችሁ የመካከለኛዉ እዝ ወታደር ተብዮዎች፣ለአካባቢ ሚሊሻ ለሲቪል ፖሊስ የመረጃ ሰንኮፎች እና ለወታደራዊ ደህንነቶች በሙሉ።
(ፎቶ ከፋይል)
በህዝብ ላይ ከፍተኛ ወረራ ለመፈጸም ከአለቆቻችሁ ትእዛዝ ተቀብላችሁ ወደ አርማጭሆ ጀንበር፣ ቀበሌ እንዲሁም ገደብዬ፣ ዳባትና ጭላ ቀበሌ፣ ሶርቃ፣ ኡማህጅርና ኡመራ፣ ሳንጃ፣ ተከዜ ግንባር ድረስ ለመንቀሳቀስ መዘጋጀታችሁን ተንተርሶ ከዉስጣችሁ የሚገኙ የህዝብ አርበኞች የመከላከያ ሰራዊት አባላት ይህን ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል።
በማንኛዉም ወቅት እና ሰሐት ላይ በየትኛዉም ዘመን በተነሱ የህዝብ መነቃቃቶች ህዝብ እንጂ ገዢ አሸንፎ አያዉቅም ይህንንም ምክንያታዊ በማድረግ ይህ ገድሎ አይጠግብ የህወሃት ሰራዊት በህዝባችን ላይ እንዲህ ያለ መጠነ ሰፊ ጥቃት ለመፈጸም ሲዘጋጅ ዝም ብለን ለመመልከት ፈጽመን አንደፍርም በመሆኑም የጥይት ሐሩሩ ከዉስጥም እንደሚንቦለቦል በማወቅ ከህዝብ ጋር እንድትቆሙ ማስጠንቀቂያ እንሰጣለን!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

No comments:

Post a Comment